Negarit - ነጋሪት

Negarit - ነጋሪት Negarit is a digital social media platform, providing news, information, insiders leaks and analysis for Ethiopian people.
(3)

Negarit is an independent and non partisan digital social media platform designed to inform, inspire and engage the people of Ethiopia. Reaching people through high-standard, high-quality and high impact multimedia content available in different formats such as youtube, facebook, twitter and other social media formats. Negarit recognizes and appreciates the efforts that citizens make each day in b

uilding a better Ethiopia for all people. Negarit strives to empower disadvantaged groups such as women, youth and people with disabilities etc. Working within collaboration of all people to enlighten, educate and strengthen citizens in order to expose corruption and to create unity between neighboring countries.

በኢራን በአንድ ታዳጊ ላይ የግብረሰዶም ተግባር የፈጸሙ ሁለት ግለሰቦች በስቅላት ተቀጡ።በኢራን፣ ቆርቬህ ከተማ ውስጥ በአንድ የ14 ዓመት ወንድ ታዳጊ ላይ የግብረሰዶም ተግባር የፈጸሙ ሁለት ...
05/06/2026

በኢራን በአንድ ታዳጊ ላይ የግብረሰዶም ተግባር የፈጸሙ ሁለት ግለሰቦች በስቅላት ተቀጡ።

በኢራን፣ ቆርቬህ ከተማ ውስጥ በአንድ የ14 ዓመት ወንድ ታዳጊ ላይ የግብረሰዶም ተግባር የፈጸሙ ሁለት ግለሰቦች፣ በተፈረደባቸው የሞት ፍርድ መሠረት ባለፈው ሰኞ ጎህ ሲቀድ በከተማው በሚገኝ ቆርቬህ ማረሚያ ቤት ውስጥ በስቅላት እንዲሞቱ ተደርገዋል።

የሞት ቅጣት የተፈጸመባቸው ግለሰቦች የ52 ዓመቱ ታህማሴቢ እና የ37 ዓመቱ ኩህያር አባሲ የሚባሉ የከተማው ነዋሪዎች ናቸው።

ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት በነሐሴ 2024 ዓ.ም ሲሆን በሞት የተቀጡት ፈሪድ ሳዴጊ የተባለ የ14 ዓመት ታዳጊ ላይ የግብረሰዶም ተግባር በመፈጸምና በቪድዮ በመቅረጽ በማስፈራራት እና ገንዘብ በመቀበል ወንጀል ተከሰው ነው።

ታዳጊው ከደረሰበት ከፍተኛ ጥቃት እና የስነ-ልቦና ጉዳት የተነሳ ነሐሴ 12 ቀን 2024 ዓ.ም ህይወቱን በገዛ እጁ ማጥፋቱን ሄንጋው የተባለ በሰብዓዊ መብት ላይ የሚሰራ ድርጅት ገልጿል።

(ቲክቫህ ኢትዮጵያ)

ዘሪሁን ኑሪ{ከሞቃዲሾ} በሞቃዲሾ ዩኒቨርሲቲ አቅራቢያ ውሃ የምትቀዳውን 10 ቶን ቦቲ መኪና ለማጀብ በብረት ለበስ ኤፒሲ ተሽከርካሪ ሄድን።እንደደረስን የኤፒሲዋን መድብተኞች ጥበቃ ላይ ትተናቸ...
05/06/2026

ዘሪሁን ኑሪ{ከሞቃዲሾ}

በሞቃዲሾ ዩኒቨርሲቲ አቅራቢያ ውሃ የምትቀዳውን 10 ቶን ቦቲ መኪና ለማጀብ በብረት ለበስ ኤፒሲ ተሽከርካሪ ሄድን።እንደደረስን የኤፒሲዋን መድብተኞች ጥበቃ ላይ ትተናቸው ቦቲዋ እስክትሞላ እኔና አብዲ (ሶማሌው) በዛ አካባቢ ባሉ ቤቶች መካከል ዞር ዞር ማለት ጀመርን።በቤቶቹ መካከል ስንሸራሸርም ዛሬም ድረስ ከህሊናዬ የማይጠፋ ነገር አየሁ!

በግምት አንድ የአራት ዓመት ህፃን በወፍራም ገመድ አንድ እግሩ ታስሮ ከቤት ደጃፍ ቆሟል።ሲያየን ፈራን መሰለኝ ደንግጦ ወደ ውስጥ ሊሮጥ ሲል ታስሮበት የነበረው ገመድ ወደኋላ ስቦ አስቀረው።አብዲ እያባበለ ከኪሱ አውጥቶ ብስኩት ሰጠው።በዚህ መሃል የህፃኑ እናት ከቤት ወጣች።ከአብዲ ጋር በሱማሊኛ ቋንቋ ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ ስለ ልጁ መታሰር ጠየቃት።እናቲቱ በከባድ የሃዘን ስሜት ታወራው ጀመር።እኔ ጎንበስ ብዬ ያንን ገመዱ የበላውን የልጁን እግር በእጄ አየዳሰስኩ ነበር።

በዚህ መሃል የምድብተኞቹ ቲም መሪ በወታደራዊ መገናኛ አይኮም ወደ ሶማሌው ሬዲዮ "ሰባ ሰባት" እያለ መጣራት ጀመረ።ሶማሌው ሬዲዮኑን አንስቶ "አቤት"ሲል ከወዲያኛው ያለው ድምፅ "ኤሊዋ ጨርሳለች" አለው።አብዲ የሶማሊያ ሽልንጎች ሰጥቶ ሴትየዋን ተሰናበታት።እኔም የተወሰነ ሽልንግ ጨምሬላት ወደ መኪናችን መመለስ ጀመርን።

ሁኔታው ለማወቅ በጣም በመሻቴ በመንገዳችን ላይ አብዲ ሴቲየዋ የልጁን መታሰር ምክንያት የነገረቺውን እንዲነግረኝ ጠየኩት።እንዲህ ሲል አጫወተኝ።

"ባሏ በሰው እጅ ከሞተባት በኋላ ቂጣ እና ሻይ እየሸጠች ሁለት ልጆቿን ታሳድግ ነበር።ከአመታት በፊት ግን እኛ የምንቀዳበትን የውሃ ቦታ ለመቆጣጠር በመንግስትና በአልሸባብ መሃከል ከባድ ተኩስ ይከፈታል።የሰባት ዓመት ትልቁ ልጇ የተኩሱን ድምፅ ሰምቶ ሲጫወት ከነበረበት ወደ ቤት ሲሮጥ ተባራሪ ጥይት ጭንቅላቱን መትቶት ከበራፉ ላይ ወድቆ ነው የሞተባት።አሁን ይሄኛው ታናሽ ልጇም እሷ ስራ ስትይዝ እየወጣ ከሰፈር በመራቅ ሲያስቸግራት 'እንደ ትልቁ ልጄ እንዳላጣው ብዬ ስራ ስይዝ እግሩን አስሬው ለመዋል ተገደደኩ...' አለችኝ።"አለኘ አብዲ! ይህንን አውርቶ ሲጨርስ ሁለታችንም ሳናስበው የሃዘን እንባ ፊታችንን አርሶት ነበር።

ይቺ እናት እና እግሩ በገመድ የታሰረው ህፃን የዛሬዋ ሶማሊያ ህያው ማሳያ ናቸው።

አንድ ወቅት ሶማሊያ በራሷ መከላከያ የምትኮራ በባህር ዳርቻዋ ውበትና በከብት ሀብቷ የናጠጠች ባለፀጋ ነበረች። ይሁንና ከመሬቷ በላይ የከብት መዓት ከባህሯ በታች የዓሳ በረከት ከመሬቷ ስር ደግሞ የነዳጅ ክምችት ተኝቶ ሳለ ህዝቧ መከራ የሚጋተው ግን በአንድ ነገር እጥረት ብቻ ነው።በሰላም ማጣት!!!!

በጎጥ ስሜትና በሀሰት ጩህት አእምሮው የደነዘዘው ወጣት የወደፊት መጠለያውን በገዛ እጁ አፈረሰው።በማግስቱም ያገኘው ነፃነት ሳይሆን የሀገር መበታተን እና በሀብታም ምድሩ ላይ መራብና የባዕድ ሀገር ስደት ብቻ ሆነ።

በገዛ እጅ ያፈረሱትን ሀገር መልሶ ለመስራት ሙሉ እድሜም አይበቃም።ሀገር አንዴ ከፈረሰ መከራው ማለቂያ የለውምና ሰላማችንን እንደ ዋዛ አንጣው!'መልዕክቴ ነው።

የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ከሰባት ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሰሜን ኮሪያ ሊያቀኑ መሆኑ ተገለጠ ! የቻይናው መሪ ሺ ጂንፒንግ በሚቀጥለው ሳምንት በሰሜን ኮሪያ ይፋዊ የሥራ ጉብ...
05/06/2026

የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ከሰባት ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሰሜን ኮሪያ ሊያቀኑ መሆኑ ተገለጠ !

የቻይናው መሪ ሺ ጂንፒንግ በሚቀጥለው ሳምንት በሰሜን ኮሪያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ሁለቱ አገራት በጋራ አስታውቀዋል።

ይህ ጉብኝት ፕሬዚዳንት ሺ ከሰባት ዓመታት ገደማ በኋላ ወደ ፒዮንግያንግ የሚያደርጉት የመጀመሪያው የጉዞ መርሐ-ግብር በመሆኑ በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ ትኩረትን ስቧል።

የሁለቱ አገራት የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ባወጡት ይፋዊ መግለጫ መሠረት፣ የሺ ጂንፒንግ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን በተደረገላቸው ልዩ ግብዣ መሠረት የተዘጋጀ ነው። ፕሬዚዳንቱ ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ሰሜን ኮሪያ ተጉዘው የነበረው እ.ኤ.አ. በሰኔ 2019 ዓ.ም. እንደነበር ይታወሳል።

ይህ ጉብኝት የፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ የ2026 ዓ.ም. የመጀመሪያው የውጭ አገር ጉዞ ሲሆን፣ መሪው በቤጂንግ ከአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ንግግር ካደረጉ በኋላ የተሰማ አዲስ መደመር በመሆኑ በቀጣናው የጂኦፖለቲካ ሚዛን ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

(መናኸሪያ ሬዲዮ)

05/06/2026
04/06/2026

♦️በተተኮሠበት ጥይት ተመቶ ህይወቱ ባለፈው የቀድሞ አትሌት ይሄይስ ታደለው ዙሪያ የተጠናከረ ልዩ ዘገባ

♦️በአትሌቶች መካከል ያለውን የአጉል ባህልና ዕምነት፣የመጠራጠርና የመጠፋፋት ባህል እንደወረርሽኝ ተዛምቶ ለተጨማሪ አደጋ ከመጋለጣችን በፊት ይታሰብበት

✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)

♦️የሟችና በገዳይነት የተጠረጠረው አትሌት ማንነት

በሚያሳዝን ሁኔታ ሁለቱም የነገ ውጤታማ አትሌቶች ይሆናሉ ተብሎ ተስፋ የተጣለባቸው ወጣቶች ነበሩ፤ጉዳዩ በህግ የተያዘ በመሆኑና በማስረጃ የተረጋገጠ ነገር ባይኖርም ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች በተለይ ለሀትሪክ እንደገለፁት በገዳይነት ተጠርጥሮ በህግ ቁጥጥር ስር የሚገኘው አትሌት ደረሠ ረታ ከደብረብርሃን የተገኘ በመቀጠል በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አሁን በመጨረሻ ደግሞ ለፌዴራል ፖሊስ የሚሮጥ አትሌት ሲሆን በጣም ትልቅ ተስፋ የተጣለበት አትሌት እንደነበረም ነው ለአትሌቱ ቅርበት ያላቸው ወገኖች የሚናገሩት።እንደ እነዚሁ ምንጮቻችን አገላለፅ አትሌቱ ከአንድ ዓመት በፊት በጉያንግ በተካሄደው ውድድር 2:12:00 በሆነ ሠዓት በመግባት የተሻለ ሠዓትና ደረጃ ይዞ ያጠናቀቀ ሲሆን የቅርብ ምርጥ ሠዓቱም 2:13:00 እንደሆነ ነው የሚሠማው።

በተተኮሠበት ጥይት ህይወቱ ያለፈው አትሌት ይሄይስ ታደለው በበኩሉ ከአማራ ክልል (ሠሜን ሸዋ)የተገኘ አትሌት ሲሆን በጉዳት ምክንያት ከውድድር ርቆ ባለቤቱን አትሌት ወርቅነሽ ዓለሙን እንደ አሠልጣኝ ሆኖ ከማሠራት ውጪ በአሁን ሠዓት በአትሌትነት እየሮጠ አይደለም።

♦️እስከመገዳደል ያደረሳቸው ምን ይሆን?

ሁለቱን ከአንድ ክልል የመጡ አትሌቶችን እስከመገዳደል ያበቃቸውን ትክክለኛውን ከእነሱና ከፈጣሪ ውጪ የሚያውቅ ሠው ፈልጎ ማግኘት አይቻልም፤ነገር በመካከላቸው ለገላጋይ ያስቸገረ አለመግባባትሴላቸው ከአሠልጣኝቻቸውና በቤተሠቦቻቸው እኔዲሁም አትሌት በሆኑት ሚስቶቻቸው ጭምር ይታወቃል።የፀባቸውን መነሻ በትክክል መግለፅ ባይቻልም ከአጉል ባህል ወይም አምልኮ ጋር ተያይዞ "ባለቤቴና እኔ ላይ ይሄን አስደርገሃል" የሚለው ዋነኛው የግጭታቸውና እስከመገዳደል ያደረሠ ችግር እንደሆነ በዙሪያ ያሉ ሠዎች ይናገራሉ፤ይህ ከድሮም ጀምሮ በአትሌቶች ዙሪያ የሚሠማው አጉል ባህል ወይም የአምልኮ ነገር ዛሬ ወደ አዲሶቹ ትውልዶችም ተሸጋግሮ አብሮ ልምምድ ያለመስራት፣አብሮ በሆቴል እንደ ጓደኛ አትሌት ክፍል ያለመጋራት፣አብሮ ያለመብላትና አብሮ በአንድ አውሮፕላን አልሄድም እስከማለት አስፈሪ ውሳኔ ላይ ተደርሶ የቡድን ስሜት ከአትሌቲክሱ እንዲጠፋ ምክንያት ሆኗል።

♦️ለሽማግሌና ለአስታራቂዎች ያስቸገሩት ሟችና ገዳይ

በሁለቱ አትሌትች መካከል ያለውን አለመግባባት ለመፍታት ያልመጣ አስታራቂ ሽማግሌ የለም፥ የሁለቱም አሠልጣኞች ፍቅሩና ኢማና መርጊያን ጨምሮ፣የቅርብ ጓደኛ በመጨረሻም ቤተሠቦች የሁለቱንም አለመግባባት ለመፍታት ዳገት ቢወጡ ቁልቁል ቢወርዱ ሊሳካ አልቻለም፤አሠልጣኞችም ነገሩ ከብዷቸው ሁለቱም አትሌቶች በተለያየ አሠልጣኝ የተለያየ ቦታ እንዲሠሩ እሰከማድረግ ደርሠዋል፤በውስጥ የተቋጠረው ቂም በሽማግሌም፣በገላጋይ አልፈታም ብሎ በመጨረሻም ድምዳሜው የአንደኛው ህይወት በአንደኛው እጅ መጥፋት ሆኗል።

♦️የአትሌቱ ህይወት ስላለፈበት አጋጣሚ

ገዳይ እንዴትና የት፣በምን ሁኔታ የሟችን ህይወት ነጠቀ የሚለው ብዙዎች ለማወቅና እርግጠኛ መሆን የሚፈልጉት ጥያቄ ነው፤በገዳይነት የተጠረጠረው አትሌት ደረሠ ረታ በውስጡ በተፈጠረ አንዳች ስሜት ተነሳስቶ ወደ ሠንዳፋ የልምምድ ቦታ ድንገት አመራ፤በዛች ቀን የተደገሠለትን ድግስና ከሞት ጋር ቀጠሮ እንዳለው ለሠከንድም ቢሆን ያላሠበው የቀድሞ አትሌት ይሄይስ ታደለው ባለቤቱን አትሌት ወርቅነሽ ዓለሙን ከፊት ሆኖ እያሠራ እያለ በድንገት በተተኮሠበት ጥይት ይህቺን ዓለም ዳግም ላይመለስባት ለዘለዓለሙ አሸልቧል።ከፊቱ በርካታ የአትሌቲክስ የስኬት ዓመታት እንዳሉት የሚነገርለት በግድያ የተጠረጠረው አትሌት ደረሠ ረታ ከግድያው በኋላ ራሱን ለማሸሽ ጥረት ቢያደርግም በአካባቢው በነበሩ አርሶ አደሮች ጥረት ተይዞ አሁን ሠንዳፋ በሚገኘው ማረሚያ ቤት በህግ ጥላ ስር ውሎ ጉዳዩን እየተከታተለ ይገኛል።

♦️"በጣም ተፈታተነኝ፣በጣም ታገለኝ" የሚል አጭር ቃል የተነፈሠው ገዳይ

በግድያ ተጠርጥሮ በህግ ጥላ ስር የሚገኘው አትሌት ደረሠ ረታ ከግድያው በኋላ በተለይ ዛሬ ከሟች አትሌት ይሄይስ ታደለው የቀብር ስነ-ስርዓቱ ከተፈፀመ በኋላ የቅርብ ወዳጆቹ ለምን እንደዚህ አይነት ውሳኔ እንደወሠነ ጠይቀውት ከገጠመው ያልታሠበ ፈተና ውስጥ የወደቀው አትሌቱ በፀፀት ውስጥ ሆኖ "በጣም ተፈታተነኝ፣በጣም ታገለኝ"የሚል አጭር ቃል ከመናገር የዘለለ መተንፈስ እንዳልቻለ ገልፀዋል።

♦️የአትሌት ይሄይስ ታደለው የመጨረሻ ስንብት

የአትሌት ይሄይስ ታደለው የቀብር ስነ-ስርዓቱና የአስከሬን ሽኝት ዛሬ ከቀኑ በ6:00 በሚኖሩበት ሠንዳፋ በኬ ማርያም ቤተክርስቲያን የአትሌቱ ቤተሠቦች፣ጓደኞች፣አሠልጣኞች፣አትሌቶችና የስፖርት ቤተሠቦች በተገኙበት በክብር አርፏል።በጉዳት ምክንያት ከአትሌቲክስ ርቆ ባለቤቱን በማሠራት የሚያሳልፈው አትሌት ይሄይስ ታደለው እንደዋዛ ይህቺን ዓለምና አትሌቲክሱንም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተሠናብቷል።

ፎቶ:ስፖርት ኮርነር ኢትዮጵያ

ኬንያ በበጀት እጥረት ምክንያት የአፍሪካ ልማት ባንክ ድርሻዋን አጣች ኬንያ በአፍሪካ ልማት ባንክ  ውስጥ መክፈል የነበረባትን የ10 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ዓመታዊ ክፍያ ባለመፈጸሟ ምክንያት 9...
04/06/2026

ኬንያ በበጀት እጥረት ምክንያት የአፍሪካ ልማት ባንክ ድርሻዋን አጣች

ኬንያ በአፍሪካ ልማት ባንክ ውስጥ መክፈል የነበረባትን የ10 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ዓመታዊ ክፍያ ባለመፈጸሟ ምክንያት 92 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣውን የባንኩን የአክሲዮን ድርሻ አጥታለች። የባንኩ ይፋዊ መግለጫ እንደሚያሳየው፣ በዚህ የበጀት እጥረት ምክንያት ሀገሪቱ 6,715 አክሲዮኖችን ያጣች ሲሆን፣ በባንኩ ውስጥ የነበራት የባለቤትነት ድርሻም ከ1.16 በመቶ ወደ 1.034 በመቶ ዝቅ ብሏል። እነዚህን ክፍት የሆኑ አክሲዮኖች አሁን ሌሎች አባል ሀገራት ሊገዟቸው እንደሚችሉ ተገልጿል።

ይህ የባለቤትነት ድርሻ መቀነስ የመጣበት ወቅት ለናይሮቢ እጅግ አሳሳቢ ሆኗል፤ ምክንያቱም ኬንያ ከባንኩ የምትወስደው የብድር መጠን በከፍተኛ ሁኔታ በጨመረበት ወቅት የተከሰተ ነው። ሀገሪቱ ናይጄሪያን ጭምር በመብለጥ ከባንኩ ከፍተኛ የብድር ስርጭት የተደረገላቸው ሀገራት ተርታ ውስጥ በሦስተኛ ደረጃ ላይ ብትቀመጥም፣ በአንጻሩ በባንኩ ላይ ያላት የባለቤትነት ይዞታና የድምፅ ክብደት እየቀነሰ መምጣቱ ተሰሚነቷን ያዳክመዋል ተብሎ ተሰግቷል።

Capital-

ዘሪሁን ኑሪ ከሞቃዲሾ ባካራ!በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ ውስጥ ከባድ የተኩስ ልውውጥ ተካሂዷል።ፍልሚያው የተካሄደው በመንግስት ጦር እና ከተቃዋሚዎች ጋር በተሰለፉ ሚሊሻዎች መካከል ነው። ለዚህ ግ...
04/06/2026

ዘሪሁን ኑሪ ከሞቃዲሾ ባካራ!

በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ ውስጥ ከባድ የተኩስ ልውውጥ ተካሂዷል።ፍልሚያው የተካሄደው በመንግስት ጦር እና ከተቃዋሚዎች ጋር በተሰለፉ ሚሊሻዎች መካከል ነው።

ለዚህ ግጭት ዋነኛ መነሻ የሆነው የፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ የስልጣን ዘመን ባለፈው ወር ማብቃቱ ነው።ይሁንና ፓርላማው ባደረገው የሕገ-መንግስት ማሻሺያ ምክንያት ፕሬዝዳንቱ በወንበራቸው ላይ ለመቆየት ወስነዋል።

የፕሬዝዳንቱን ውሳኔ የተቃወሙት እነ ሸሪፍ ሼክ አህመድ እና ሐሰን አሊ ሀይሬ ዛሬ ትልቅ ሰልፍ አቅደው ነበር።ሰልፉ ሳይጀመር ግን የመንግስት ኃይሎች መኖሪያ ቤቶቻቸውን ከበው ጥቃት እንደሰነዘሩባቸው ተቃዋሚዎቹ ተናግረዋል።በጥቃቱም ድሮኖች እና ከባድ ፀረ-ታንክ መሣሪያዎች ጥቅም ላይ መዋላቸው አስታውቀዋል።

የውስጥ የፖለቲካ ፍልሚያ ሶማሊያን እያደማት ባለበት በአሁኑ ወቅት ከኢትዮጵያ ጋር ያላት የዲፕሎማሲ ግንኙነትም አሁንም በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ነው የሚገኘው።

ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር የተፈራረመችውን የባሕር በር ስምምነት ተከትሎ የሶማሊያ መንግስት ግንኙነቱን አሻክሮ የኢትዮጵያን ሰራዊት ለማስወጣት እየጣረ እንደነበር ይታወቃል።አሁን ግን የገጠማት ይሄ የውስጥ ቀውስ ውሳኔዋን ትልቅ ጥያቄ ውስጥ ጥሎታል።ምክንያቱም የመንግስቱ ኃይሎች ትኩረታቸውን ወደ ወንበር ሽኩቻ ሲያዞሩ ሀገሪቱን ለሁለት አስርት ዓመታት ሲያደማ የቆየው አል-ሸባብ የደህንነት ክፍተቱን ተጠቅሞ ጥቃት ሊሰነዝር ይችላል የሚል ትልቅ ስጋት አለ።ይህ ደግሞ ለአጠቃላይ ቀጠናው በተለይም ለኢትዮጵያ ቀጥተኛ የፀጥታ ስጋት መሆኑ አይቀሬ ነው።

የተፃፈው በ Zerihun Nuri Abote ከመቅደሾ ሶማሊያ

ከሳተላይት የተገኘው አስገራሚ ምስጢር፡ ቻይና በባህር ስር ፍፁም ድብቅ የሆነ አዲስ የቴክኖሎጂ አብዮት ፈጠረች! 🛰🌊በጂያንግናን የመርከብ ግንባታ ማዕከል (Jiangnan Shipyard) በሳተ...
04/06/2026

ከሳተላይት የተገኘው አስገራሚ ምስጢር፡ ቻይና በባህር ስር ፍፁም ድብቅ የሆነ አዲስ የቴክኖሎጂ አብዮት ፈጠረች! 🛰🌊

በጂያንግናን የመርከብ ግንባታ ማዕከል (Jiangnan Shipyard) በሳተላይት ምስል አማካኝነት የተገኘው አዲሱ የቻይና ሰርጓጅ መርከብ፣ በዓለም አቀፉ የባህር ኃይል መድረክ ላይ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። ይፋዊ ስሙና የተመደበበት ተልዕኮ እስካሁን በውል ባይታወቅም፣ መርከቡ በአሁኑ ዘመን ባሉ የባህር ሰርጓጅ መርከቦች ላይ የተለመደውን የላይኛውን ጎልቶ የሚወጣ የቁጥጥር ማማ ወይም (Sail) ሙሉ በሙሉ ያስቀረ ለውጥ አምጪ ንድፍ ይዟል። ይህ ፍጹም ልሙጥ ገጽታው መርከቡን ከተለመዱት ወታደራዊ ባህር ሰርጓጅ መርከቦች የተለየና እጅግ ዘመናዊ ያደርገዋል።

ይህ አዲስ የቴክኖሎጂ ውጤት በግዝፈቱም ቢሆን ቀላል የሚባል አይደለም። የባህር ኃይል ጉዳዮችን በቅርበት የሚከታተለው ‘ኔቫል ኒውስ’ (Naval News) እንደገለጸው፣ መርከቡ 120 ሜትር ርዝመትና እስከ 11 ሜትር የሚደርስ ስፋት አለው። ይህም ቻይና በአሁኑ ወቅት በስራ ላይ ካሰማራቻቸው ‘ታይፕ 093’ የኒውክሌር ጥቃት ሰርጓጅ መርከቦች እጅግ የሚበልጥ ከመሆኑም በላይ፣ ለአሜሪካ ባህር ኃይል የጀርባ አጥንት ከሚባሉት የ‘ቨርጂኒያ ክላስ’ ሰርጓጅ መርከቦች እንኳ በትንሹ ይረዝማል። ይህ ንድፍ ቻይና እ.ኤ.አ. በ2018 ከሞከረችው አነስተኛ የቴክኖሎጂ ማሳያና በ2024 በዙሃይ የዓየር ትዕይንት ላይ ይፋ ካደረገችው ግዙፍ ሰው-አልባ የውሃ ውስጥ ተሽከርካሪ (UUV) ፅንሰ-ሀሳብ የበሰለ ውጤት መሆኑ ይገመታል።

ቻይና ይህንን "ሸራ-አልባ" ንድፍ የመረጠችበት ዋና ምክንያት የውሃ ውስጥ ድብቅነቷን እና ወታደራዊ አቅሟን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ነው። የቁጥጥር ማማው መቅረት በውሃ ውስጥ የሚፈጠረውን የመቋቋም ግጭት በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀንስ በመሆኑ፣ መርከቡ እጅግ ፈጣንና በቀላሉ የሚቀናበር የመንቀሳቀስ ብቃት እንዲኖረው ያስችለዋል። ከሁሉም በላይ ደግሞ፣ መርከቡ በከፍተኛ ፍጥነት በሚጓዝበት ወቅት እንኳ የሚፈጥረው የድምፅ ሞገድ (Acoustic signature) አነስተኛ በመሆኑ፣ በጠላት ሶናርና የራዳር መፈለጊያዎች ሳይታወቅ ረጅም ርቀት የመጓዝ ድብቅ አቅም ይሰጠዋል። ይህ ዓይነቱ አወቃቀር መርከቡ ወደ ውሃው ወለል ላይ ብቅ ማለት ሳያስፈልገው፣ በትኩረት በጥልቅ ባህርና በውቅያኖስ ወለል ላይ ለሚሰሩ ተልዕኮዎች የተገነባ መሆኑን ያመላክታል ተብሏል።

ከዚህም በተጨማሪ መርከቡ እ.ኤ.አ. በ2024 በቻይና የባህር ኃይል ላይ መታየት የጀመረውንና ከቀጣዩ ትውልድ ‘ታይፕ 095’ የማጥቂያ ሰርጓጅ መርከቦች ጋር የሚገናኘውን የ‘X’ ቅርጽ መሪ (Rudder) ይዟል። የድምፅ መከላከያ ሽፋን ያለው ዘመናዊ የፈሳሽ ኃይል ማመንጫ (Pump-jet propulsor) የተገጠመለት መሆኑም ይገመታል። ይሁን እንጂ ይህ ግዙፍ መርከብ በኒውክሌር ኃይል የሚሰራ ይሁን፣ በሰው የሚነዳ ወይም በከፊል ራሱን ችሎ የሚንቀሳቀስ (Autonomous) መሆኑ እስካሁን አልተረጋገጠም። የባህር ላይ አደኞችን የማደን፣ የልዩ ዘመቻዎች ድጋፍ የመስጠት ወይም አዲስ ስትራቴጂካዊ ተልዕኮ የተሰጠው መሆኑን ለማወቅ የዓለም ኃያላን አሁንም ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተሉ ይገኛሉ።

 : የየመኑ ሁቲ ታጣቂ ቡድን አሜሪካን አስጠነቀቀ ! ሰይድ አብዱልማሊክ አል-ሐውቲ በቀጣናው አዲስ የጦርነት ቀውስ ለመቀስቀስ እየተደረገ ስላለው የአሜሪካ ሙከራ ማስጠንቀቂያ  አስተላልፏል።​...
04/06/2026

: የየመኑ ሁቲ ታጣቂ ቡድን አሜሪካን አስጠነቀቀ !

ሰይድ አብዱልማሊክ አል-ሐውቲ በቀጣናው አዲስ የጦርነት ቀውስ ለመቀስቀስ እየተደረገ ስላለው የአሜሪካ ሙከራ ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል።

​የየመኑ አንሳሩላህ ንቅናቄ መሪ ሰይድ አብዱልማሊክ አል-ሐውቲ አሜሪካ በሊባኖስና በፍልስጤም ያለውን ነባራዊ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በቀጣናው የሚገኙ ሃይሎችን ለእስራኤል ፍላጎት ማስፈጸሚያነት ወደ አጠቃላይ ጦርነት ለመሳብ ጥረት እያደረገች ነው ሲሉ ከሷል።

​የንቅናቄው መሪ በሰጡት መግለጫ ዋሽንግተን በቀጣናው የሚገኙ የተለያዩ አካላትንና ኃይሎችን በማነጋገር የእስራኤላውያንን ጥቅም ወደሚያገለግል ሰፊና አጠቃላይ የጦርነት አዙሪት ውስጥ እንዲገቡ ለማድረግ በስፋት እየተንቀሳቀሰች መሆኑን አጋልጠዋል።

​ቡድኑ በማንኛውም መልኩ በአሜሪካውያን ግፊትና ቀስቃሽነት ለእስራኤል ጠላት መጠቀሚያ ወደሚሆን የጋራ ውጊያ ውስጥ እንዳይገቡ በቀጣናው ለሚገኙ ኃይሎችና ፓርቲዎች ጥብቅ ምክርና ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።

​በሊባኖስና በፍልስጤም እየተከሰቱ ባሉ ወቅታዊ ጉዳዮች እንዲሁም አሜሪካ እየወሰደቻቸው ባሉ ኢ-ፍትሃዊ እርምጃዎችን ለመከላከል ከአጋሮቻቸው ጋር ሙሉ የጋራ ቅንጅትና ትብብር እንዳላቸው በድጋሚ አረጋግጠዋል።

​ንቅናቄው አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ከጠላቶች በኩል የሚሰነዘርን ማንኛውንም አይነት ጦርነት ወይም ድንገተኛ ጥቃት ፊት ለፊት ለመጋፈጥና ለመመከት ፍጹም ዝግጁ መሆኑን አስታውቀዋል።

Address

Addis Ababa
00000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Negarit - ነጋሪት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Negarit - ነጋሪት:

Share