05/06/2026
በኢራን በአንድ ታዳጊ ላይ የግብረሰዶም ተግባር የፈጸሙ ሁለት ግለሰቦች በስቅላት ተቀጡ።
በኢራን፣ ቆርቬህ ከተማ ውስጥ በአንድ የ14 ዓመት ወንድ ታዳጊ ላይ የግብረሰዶም ተግባር የፈጸሙ ሁለት ግለሰቦች፣ በተፈረደባቸው የሞት ፍርድ መሠረት ባለፈው ሰኞ ጎህ ሲቀድ በከተማው በሚገኝ ቆርቬህ ማረሚያ ቤት ውስጥ በስቅላት እንዲሞቱ ተደርገዋል።
የሞት ቅጣት የተፈጸመባቸው ግለሰቦች የ52 ዓመቱ ታህማሴቢ እና የ37 ዓመቱ ኩህያር አባሲ የሚባሉ የከተማው ነዋሪዎች ናቸው።
ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት በነሐሴ 2024 ዓ.ም ሲሆን በሞት የተቀጡት ፈሪድ ሳዴጊ የተባለ የ14 ዓመት ታዳጊ ላይ የግብረሰዶም ተግባር በመፈጸምና በቪድዮ በመቅረጽ በማስፈራራት እና ገንዘብ በመቀበል ወንጀል ተከሰው ነው።
ታዳጊው ከደረሰበት ከፍተኛ ጥቃት እና የስነ-ልቦና ጉዳት የተነሳ ነሐሴ 12 ቀን 2024 ዓ.ም ህይወቱን በገዛ እጁ ማጥፋቱን ሄንጋው የተባለ በሰብዓዊ መብት ላይ የሚሰራ ድርጅት ገልጿል።
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ)