02/06/2026
ኤስ ዲ ኤስ ሴፍቲ ኤንድ ድራይቪንግ ጋ/የት /የግ/ማኅበር 2016 ጀምሮ ነው የችግር ጠኔውን ለማስታገስ የግል ጥቅሙን ለማጋበስ የሚደርሰው የትራፊክ አደጋ ዕረፍት የነሳው በመምሰል የላባደሩን ወዝ መዝብሮ ለመክበር አሲሮ ብቅ ያለው።
በሀገራችን ትልቅ ችግር የሆነው ፕሮጀክት ቀረፅን ለወገን ለሀገር አሰብን ብለው ግን ፕሮፖዛላቸው መዳረሻው ሆነ ውጤቱ የራሳቸውን ኪስ ማድለብ የሌሎችን ገንዘብ ማለም ማለብ አሳቢ መስሎ በመታየት የራስን ሀብት ማካበት እየሆነ ነው።
የመንግስት ሹሞችም ደጋፊ ሆነው በዚህ መልኩ ሀሳብ ይዛችሁ ፕሮጀክት ቀርፃችሁ ኑ እኛ እናፀድቀዋለን ከሚል የምዝበራ ስልት እስከ ኮሚሽን ድርሻ በጓዳ እየጨረሱ እንዲህ ያሉ መዝባሪወች ጋር ድግስ ደግሰው ብቅ የሚሉበት ሂደት ለሀገር ውድቀትን የሚያላብስ ነው።
ይህ ድርጅት የሚመራው ግለሰብ የመንጃ ፈቃድ መምህር ድርሻውን ወስዶ ቢወጣም የመንጃ ፈቃድ ትምህርት ቤት የነበረው ሰው ነው ራሱ መምህር ሆኖ እያስተማረ ብቁ ነው እያለ ወደ መመዘኛ መፈተኛ ተቋማት ሲልክ የኖረ ትምህርት ቤት ከፍቶ ሲሸቅል የኖረ ድርሻውን ሸጦ የለቀቀ ነው ያኔ ነበር ትምህርት አሰጣጡ ላይ ችግር ካለ መሞገት ለምን በዚህ ካሪኩለም አላስተምርም ማለት ያለበት ድሮ ነበር።
ዛሬ ይህ ወደል ትናንት አስተምሮ ብቁ ነው እያለ በእርሱ ፊርማ ወደ መፈተኛ ተቋማት ሲልክ የኖር ግለሰብ ተመለሶ ብቃት ልመዝን ሲል ፍላጎቱ ገንዘብ መሆኑን እናይበታለን።
ይህ ግለሰብ ትናንት እርሱ ካስተማረው ትምህርት የተለየ በመንጃ ፈቃድ ትምህርት ቤቶች ምን አለ ?? ትናንት በኮምፒዩተር ጥያቄ ቀርቦልን ኮምፒዩተሩ ላይ ሰርተን አልፈናል ካሜራ በተገጠመለት ግቢ ከሰው ነፃ ሆነን የተግባር ፈተናን ወስደናል ከዚህ የተለየ ሌላ ምንም የመፈተኛ ሂደት በሌለበት ዘመናዊ አፈታተን ሌላ ምናምን አሰለጣጠን ብሎ የላብ አደሩን ኪስ ለማራቆት ተደራጅቶ መምጣት ሀጥያት ነው
Ministry of Transport and Logistics - Ethiopiaለአሽከርካሪው የግንዛቤ ማስጨበጥ ስልጠና መስጠት ካስፈለገው በድቾቶ ተርሚናል በቢጋዱስ መቆሚያ በመናኸሪያ ግቢወች አሽከርካሪወች በብዛት በሚገኝባቸው አካባቢወች ያለምንም ክፍያ ባለሙያችሁን ልካችሁ የአጭር ሰአት ስልጠናን መስጠት ትችላላችሁ። ከዛ ውጭ ትናንት ከተማርነው የተሻሻለ ትምህርት በሌለበት የተለየ አፈታተን ባልተዘረጋበት ኑ ድጋሜ ተማሩ ማለት ምክንያት ፈጥሮ የግል ሀብት ለማፍራት የሚደረግ ጥረት ነው።
መፈተሽ ካለባችሁ የምትሰጡትን መንጃ ፈቃድ ካርዱን አዘምናችሁ በአንድ ኔትወርክ አስተሳስራችሁ ፎርጅድ ከኦርጅናል የሚለይበት ቀላል አሰራርን ዘርጉ። እሳቤያችሁ ችግር መፍታት ሳይሆን ምክንያት ፈጥሮ መዝብሮ ሀብት ማፍራት ስለሆነ ትክክለኛ ችግር ፈች ቦታወች እና ሀሳቦች ላይ አትገኙም።