22/02/2026
🇺🇸/🇮🇷 የኢራን ፕሬዝዳንት መስኡድ ፔዜሽኪያን፡-
"ኢራን በአካባቢው ሰላምና መረጋጋት እንዲኖር ቁርጠኛ ነች። በቅርብ ጊዜ የተደረጉ ድርድሮች ተግባራዊ ሀሳቦችን መለዋወጥን የሚያካትቱ ሲሆን አበረታች ምልክቶችንም አስገኝተዋል።
ሆኖም!! የአሜሪካን እርምጃዎች በቅርበት መከታተላችንን እንቀጥላለን እና ለማንኛውም ሊከሰት ለሚችል ሁኔታ አስፈላጊውን ዝግጅት ሁሉ አድርገናል።"
በተያያዘ መረጃ የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ አገሪቱ ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጋር ለሚደረገው ጦርነት ስትዘጋጅ ለብሔራዊ ደህንነት ኃላፊ አሊ ላሪጃኒ ከፍተኛ ሥልጣን መስጠታቸው ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል።
የኢራን ብሄራዊ ድህንነት ምክር ቤት ዋና ፀሃፊ አሊ ላሪጃኒ በአሁን ወቅት ቁልፍ የደህንነት፣ ወታደራዊ እና የዲፕሎማሲ ስራዎችን ውጤታማ በሆነ መንገድ እየመራ ይገኛል።
ጠቅላይ መሪው እራሳቸውን ጨምሮ ከፍተኛ መሪዎች ቢገደሉ በርካታ ደረጃዎችን ያቀፈ ሰፊ የአደጋ ጊዜ እቅድ እንዲዘጋጅ አድርገዋል።
ኢራን ወታደራዊ ኃይሏን በከፍተኛ ጥንቃቄ ላይ አድርጋለች፣ የሚሳኤል ሲስተሞችን ወደ ስትራቴጂካዊ ቦታዎች አዛውራለች፣ በጦርነት ወቅት አለመረጋጋትን ለመግታት የሀገር ውስጥ የደህንነት ኃይሎችን በከፍተኛ ደረጃ አዘጋጅታለች።
ለተጨማሪ የቪዲዮ መረጃዎች ቴሌግራም
👇👇👇
t.me/Etmusliminsider