13/12/2025
⛔️የከባድ መኪና ሹፌሮች "የቸርች ማሰርያ ኩፖን" በግዳጅ እንዲገዙ እየተደረገ መሆኑ ተዘገበ
~~~~~~~~
የከባድ መኪና ሹፌሮች በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተለያዩ በደሎች እየደረሱባቸው መሆኑን በከፍተኛ ምሬት እየተናገሩ ቆይተዋል፡፡ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ለሚመለከተው አካል አቤት ቢሉም መንግስት ምንም እንኳን የምችለዉን ማሻሻያ ለማድረግ እየሰራሁ ነው ቢልም እስካሁን ድረስ መፍትሄዎችን እንዳላገኙና ለመስራትም እጅግ እየተቸገሩ መሆኑን ፣ይህንንም ተከትሎ በራሳቸዉና በቤተሰቦቻቸው ህይወት ላይ ከፍተኛ አደጋ መደቀኑን ይገልጻሉ፡፡
እነዚህ የከባድ መኪና ሹፌሮች ከሚያነሷቸው ችግሮች መሃል የደህንነት ስጋቶች፣ የስራ ክብደት እና የደሞዝ አለመመጣጠን፤ የመሰረተ ልማት አለመሟላትና ያንንም ተከትሎ የጉዞ መስተጓጎል፣ አስተዳደራዊ በደሎች የሚጠቀሱ ሲሆኑ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በየአርቴፊሻል ኬላው በአንድ ጉዞ ዉስጥ ብቻ በተደጋጋሚ በሚጠየቁት ገደብ አልባ ገንዘብ እጅግ መማረራቸዉን ሲገልጹ ይሰማሉ፡፡ ይህ በእንዲሁ እያለ እነሆ አሁን ደግሞ የፕሮቴስታንቶችን ቸርች ማሰርያ እየተባሉ በግዳጅ ኩፖን እንዲገዙ እየተደረጉ መሆኑን የ የተሰኘውና ሹፌሮች የሚደርስባቸዉን በደሎች የሚያጋልጠው ገጽ ከእነማስረጃው ለጥፎት እንዲህ ይነበባል!👇
_____________
"ትናንት ከሰበታ እና ቱሉቦሎ መሀል ያለወ ወረዳ ላይ ማለትም ኢሉ ወረዳ ወይንም ተጂ ከተማ ላይ የጴ'''''ንጤ ቸርች ማሰሪያ እያሉ ትራፊኮችና መንገድ ትራንስፖርቶች የ500 ብር ኩፖን ካልገዛቹ ብለው እያስቆሙ የግድ እየተቀበሉን ነው የሚል መልዕክት ደርሶናል ብለን ስላጋራን ብዙዎች ጉዳዩ መፈፀሙ ሳታውቁ ስትዘልፉን ነበር። ለማንኛውም ኩፖኑ ይሄው ያኔ ያላጋራነው ጉዳዩን አይተው እንዲታረሙ ነበር ለማንኛውም ማንም በግዳጅ የሚያደርገውን ነገር የማውገዝ የማሳወቅ የማሳየት ግዴታ ስላለብን እንዲህ ያለውንም አናልፍም። ማውገዝ ካለባችሁ እኛን ችግሩን ያሳየነውን ሳይሆን ችግሩን የፈጠረውን አካል ነው። በግዴታ መሆኑን ነው ልክ አይደለም ያልን መዋጮውን አይደለም። እንመዝን"