30/01/2026
follow us. https://web.facebook.com/story.php?story_fbid=122112153387175713&id=61585271393204&rdid=Bd4GScnkCFlVB54m #
የሕወሓት ጦር አሰላለፍ እና አመራር መረጃ ተገኘ.
ወያኔ መገንጠልን ግቡ ላደረገ ጦርነት በአራት አቅጣጫ ጦሩን እያንቀሳቀሰ ነው።
ከጥር 18 ቀን ጀምሮ አፍላ ውጊያ ከተነሳባቸው የምስራቅና ምዕራብ ጠለምት አካባቢዎች በተጨማሪ በሌሎች ወሳኝ ግንባሮች full-scale war ለመክፈት የሰው ኃይል፣ ሎጀስቲክና የመረጃ ቅንጅቶችን እያደረገ ነው።
በጠለምት ቀጠናዎች እስካሁን በታወቀ መረጃ 3 "አርሚ" አስገብቷል። (አርሚ 11፣ 13፣ 35) ቁጥሩ ከዚህም ሊበልጥ ይችላል። ከዋልድባ መድሐኒዓለም ታችኛውን ገፅ፣ የወልቃይት አናት እና የጠገዴ መሻገሪያ የአርማ ደጋ ወሳኝ በር ትላንት ይዘዋል።
ይህኛው ኃይል ወደወልቃይት እና ወደ ጠገዴ ወሳኝ ክፍሎች ሰብሮ ለመግባት የተዘጋጀ ነው።
በሽራሮ በኩል ተከዜን ተሻግሮ ወደቃፍታ ሁመራ፣ በደደቢት ወደ ቆራሪት አቅጣጫ በ human wave attack ለመግባት አስቧል።
ከሽሬ ሲንቀሳቀስ ያደረው የሰው ኃይል ለዚህ አብነት ነው።
በሱዳን ያለው ታጣቂ ኃይል ከመቼውም ጊዜ በላይ የትጥቅ አቅም ፈጥሯል። "አርሚ 70" በ3 ኮሮችና አንድ ኮማንዶ ክፍለጦር ከመዋቀሩ ባሻገር ለዚሁ ዘመቻ ሌሎች ስልጠናዎችን ሲሰጥ ቆይቷል። ይህን የወልቃይት አስተዳደር ጠንቅቆ ያውቃል!
- ድንበር አካባቢ ሸረሪና ላይ ያለው ኮር 701 አዛዡም ኮ/ል ፀጋይ ኃይል እንዲጨመረው ተደርጓል።
- መሃል ሱዳንና ዋድ መደኒ ላይ ሆነው የአልቡርሃንን ጦር ደግፈው ሲዋጉ የቆዩት በዮሐንስ እና በመብራህቶም የሚመሩት ኮር 702 እና ኮር 703 ተንቀሳቅሰዋል።
- ወዲ ነጮ ተብሎ የሚጠራው 1 ክፍለጦር ኮማንዶም በተመሳሳይ ከ ዋድ መደኒ ወደ ጠረፍ ኃይል እንዲያንቀሳቅስ ተደርጓል።
- የአርሚ 70 ከፍተኛ አመራሮች
1. ጄኔራል ሙዘይ መኮንን አዛዥ
2. ግደይ ሃይሉ (ወዲ ፊውዳል) ምክትል
3. ምሩፅ - መረጃ
4. ተወልደ - ሎጀስቲክስ
ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሚወስዱት በነ ፍስሐ ማንጁስ ከሚመራው አዲሱ ኮማንድ ነው።
የህወሓት ቡድን ለታጣቂ ኃይሉ ለዚሁ ዘመቻ ዝግጅት ያደረገው የአመራር ምደባ ፦
የሕወሓት ታጣቂ ዋና አዛዥ ብርጋዴየር ጀኔራል ኃይለ ሥላሴ ግርማይ (ወዲ እምበይተይ)፣
የዘመቻ መምፈሪያ ኃላፊው ደግሞ ሜጀር ጀኔራል ዩሓንስ ወልደጊዮርጊስ (ጆን መዲድ)፣
የስልጠና ኃላፊ ብርጋዴየር ጀኔራል ምገበይ ኃይሌ ሲሆኑ፤
የሕወሓት ወታደራዊ መረጃ ኃላፊ በመሆን የተመደቡት ደግሞ ሜጀር ጀኔራል ማሾ በየነ ናቸው፡፡
ሌተናል ጀኔራል ፍስሃ ኪዳኑ (ፍስሐ ማንጁስ) የጊዜዊ አስተዳደሩን ሀብት፣ የውጭ ክፍልና የውጭ ግንኙነት በሀብት፣ በመረጃና በግንኙነት የመምራት ኃላፊነት ይዟል።
እነዚህ ለአብነት የተጠቀሱ ወታደራዊ አመራሮች የውጊያ ዝግጁነትን ከማረጋገጥ ባለፈ የውጊያ ጭንቅላት ሆነው እንደሚያገለግሉ በፖለቲካ አመራሩ ዘንድ ታምኖባቸዋል፡፡
በእስካሁኑ አሰራር የታጣቂ ቡድኑ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ታደሰ ወረደ እንደሆነ ቢታወቅም፣ ይህ አዲሱ ኮማንድ ታደሰን ያንሳፈፈ ሆኗል፡፡ በኮሚቴ ይወሰኑ ከነበሩ አሰራሮች ሰውየውን ማሸሽ ከጀመሩ ሰነባብቷል።
በሌላ በኩል የጦርነቱ ቅድመ ዝግጅት ቁልፍ ጉዳይ የሆነው፣ የሕወሓት ጀኔራሎች የጦርነት ወታደራዊ ኮማንድ ማዕከል ሆና የተመረጠችው ቦታ አዲ ፀፀር (ሽራሮ አካባቢ) ነች።
በተጨማሪም፣ ከባባድ መሳሪያዎቻቸውንም ከቦታ ወደ ቦታ እያንቀሳቀሷቸው እንደሆነ ተጠቁሟል። ቡድኑ ቀላል ሮኬቶችን ጨምሮ መድፎችንና ታንኮችን አንቀሳቅሷል።
ወደ አዲ ፀፀር እና የጭላ ወስዶ ያከማቻቸው ከባድ መሳሪያዎችም አሉ።
የጦርነቱ ዋና ዓላማ መገንጠልን ግቡ ያደረገ እንደሆነ ይህም የአማራ ታሪካዊ ርስቶች በመውረር ለማሳካት እንደታሰበ ከዝግጅታቸው መረዳት ይቻላል፡፡
በሱዳን ባለው የሰው ኃይል ስምሪት ገብረሂወት ( ወዲ ዝራብእ ) ፣ ሃጎስ እና አረጋዊ የሚባሉት ስማቸው በተደጋጋሚ የሚነሳ የተዋረድ አመራሮች ናቸው።
አርሚ 70 ሱዳን ውስጥ በሶስቱም ማሰልጠኛዎቹ ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ታጣቂዎችን ዝግጁ አድርጓል። ወያኔ በሱዳን በኩል ውጊያ ለመክፈት የሚጠብቀው አገዛዙ በጉዳዩ ላይ የሚሰጠውን መግለጫና ይዘት ነው። ቀጣናዊ ሁኔታዎችንና ተለዋጭ ክስተቶችን አጢኖ ከዛ በፊትም ሊጀምረው ይችላል።