ወቅታዊ መረጃዎች

ወቅታዊ መረጃዎች Broadcasting and Media Network

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር  ከኢራን አቻቸው ጋር ከተገናኙ በኋላ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ሁኔታ መባባስ ለመርዳት ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል::"የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች"የኛን ሀገር...
24/10/2024

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ከኢራን አቻቸው ጋር ከተገናኙ በኋላ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ሁኔታ መባባስ ለመርዳት ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል::"የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች"የኛን ሀገር መባባስ ማን ይዘግበው?
Conflict zone ዘግቧል

ሩሲያን ለመነጠል የምዕራባውያኑ ጫና እየሠራ እንዳልሆነ በብሪክስ እያሳዩ ያሉት ፑቲንምዕራባውያን በዩክሬን ወረራ ምክንያት ሩሲያ ከዓለም የኢኮኖሚ ሰንሰለት እንድትነጠል ለማድረግ ሌት ተቀን እ...
24/10/2024

ሩሲያን ለመነጠል የምዕራባውያኑ ጫና እየሠራ እንዳልሆነ በብሪክስ እያሳዩ ያሉት ፑቲን

ምዕራባውያን በዩክሬን ወረራ ምክንያት ሩሲያ ከዓለም የኢኮኖሚ ሰንሰለት እንድትነጠል ለማድረግ ሌት ተቀን እየሠሩ ይገኛል።

ማዕቀቦችን በመጣል የአገሪቱ ምጣኔ ሀብትን ከዓለም አቀፉ ገበያ ጋር ያለውን ትስስር እንዲቋረጥ ለማድረግ ሞክረዋል።

ከዚህም በተጨማሪ ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት በጦር ወንጀል ክሶች የእስር ማዘዣ በሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ አውጥቶባቸዋል። የምዕራቡ ዓለም ጫና እና ግፊት እየሠራ ይሆን? ጊዜ የሚፈታው ይሆናል።

ጫናውን መቋቋም እንደሚችሉ የሚናገሩት ፑቲን ከሰሞኑ የብሪክስ ጉባኤን በአገራቸው እያስተናገዱ ነው።

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ ከጥቅምት 12 -14/2017 ዓ.ም. በተካሄደው የብሪክስ ጉባኤ በሩሲያዋ ካዛን ከተማ ተሰብስበዋል።

የቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ፣ የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ እና የኢራን ፕሬዚዳንት ማስዑድ ፔዜሽኪያን እና በፈጣን ዕድገት የሚገኙ ከ20 በላይ አገራት መሪዎች በዚህ ጉባኤ ላይ ይታደማሉ።

ክሬምሊን በሩሲያ ከተደረጉ “ታላላቅ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ክስተቶች አንዱ” ሲል ነው ጉባኤውን የጠራው።

በዚህ ጉባኤ “ማስተላላፍ የተፈለገው ግልጹ መልዕክት ሩሲያን ለማግለል የተደረገው ሙከራ አልተሳካም የሚል ነው” ይላሉ በጂኦ ፖለቲካ እና ፖሊሲ ላይ የሚያተኩረው ማክሮ አድቫይዘሪ የተሰኘው ድርጅት መሥራች ክሪስ ዌፈር።

“ሩሲያ ማዕቀቦችን ተቋቁማ አይበገሬነትዋን እያሳየች እንደሆነ ከክሬምሊን የተላከ ትልቅ መልዕክት ነው። ከውጭ እንደሚታየው ሳይሆን በአገሪቷ ውስጥ ከባድ ስንጥቆች እንዳሉ እናውቃለን። ነገር ግን በጂኦፖለቲካዊ ዕይታ ሩሲያ ወዳጆች እንዳሏት ማሳያ ነው። እነዚህም የሩሲያ አጋሮች ይሆናሉ” ይላሉ።
BBC

ሰላም እንዴት ናችሁ ወንድም እህቶቼ ❤ያፌት ካሳሁን ይባላል ሁለቱም ሳንባሆቹ ፌል አድርገውበት ላፉት 5 አመታት ሐዋሳ  ሪፈራል ሆስፒታል በማሽን እየተነፈሰ ይገኛል። አውን ላይ ለህክምና የሚ...
02/09/2022

ሰላም እንዴት ናችሁ ወንድም እህቶቼ ❤

ያፌት ካሳሁን ይባላል ሁለቱም ሳንባሆቹ ፌል አድርገውበት ላፉት 5 አመታት ሐዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል በማሽን እየተነፈሰ ይገኛል።
አውን ላይ ለህክምና የሚያስፈልገውን ገንዘብ 95% ተሰብስቧል የሚቀረው የህክምናው ፕሮሰስ እና የ ፕሌን ትኬት ስፖንሰር የሚያደርግው ወይንም እድሉን የሚያመቻችለት። ያለመተንፈሻ ማሽን መንቀሳቀስ ስለማይችል ከሐዋሳ ጀምሮ መተንፈሻ ማሽኑ በፕሌን ተጭኖ ነው መሄድ ያለበት
ስለዚ ሁላችንም ያቅማችንን እናድርግ


የባንክ አካውንት
1000019303059 (ያለምዘርፍ አስራት) =ንግድ ባንክ
ስልክ
0901551224 (አባቱ )
0913988088 (እናቱ)
ሼር ማድረግ ትልቅ ዋጋ ስላለው ሼር ያድርጉ አቅሙ ላላቸው ስዎች የማድረስ አቅም ስላለው እናመሰግናለን!!!
🙏❤🙏

ጦርነት ምን እንደሆነ እኔ እና ያለሁበት ማህበረሰብ በፌስቡክ ሳይሆን በአካል እናውቀዋለን ። በቴሌቭዥን ሳይሆን በአይናችን አይተነዋል ።አካባቢያችንን ተወረን አይተነዋል ፤ቤታችንን ተነጥቀን ...
30/08/2022

ጦርነት ምን እንደሆነ እኔ እና ያለሁበት ማህበረሰብ በፌስቡክ ሳይሆን በአካል እናውቀዋለን ። በቴሌቭዥን ሳይሆን በአይናችን አይተነዋል ።አካባቢያችንን ተወረን አይተነዋል ፤ቤታችንን ተነጥቀን አይተነዋል፤ ሀብት ንብረታችን ተዘርፎ አይተነዋል ፤እርሀብ እንግልቱን አይተነዋል፤ ተራራ ገደል ቁልቁለት መውጣት መውረዱን አይተነዋል፤ ስቃይ መከፋት መበሳቆልን አይተነዋል፤ መሞትን የሚስመኝ ቀን አልፈን አይተነዋል ።ዛሬ ላይ እድለኛ ሆነን የተረፍን ሰዎች ድጋሚ ለዚህ ሁላ ስቃይ እንድንዘጋጅለት እና ያባልልስልጣናቱን ወንበር እንድናስጠብቅ ጥሪ የሚያደረግልን ...እስኪ ልጠይቅህ ከጦርነቱ ማግስት፥ መንግስት ኢኮኖሚውን አሳልጦልን ነውን? ከመንግስት ጎን የምንቆመው ?የአስር ብር ሳሙና 40 ብር ስለገዛን፣ የ300 ብር ዘይት 1000 ብር ስለገዛን፤ የ3ብር እንቁላል 12 ብር ስለገዛን፤ ወይስ የ 20 ብር ሽንኩርት 80 ብር ስለገዛን ነው ፤ወይስ 15 ስንገዛ የነበረው ሙዝ 70 ብር ስለገባ ወይስ 23 ብር የቀዳነው ነዳጅ 49 ብር ስለገባልን ፤ከመንግስት ጎን የምንቆመው ??ነው አስተማማኝ ሰላማችንን ስላረጋገጠልን? በወለጋ እና በኦሮምያ ክልል በቀን ከ600 እስክ 1000 ሺ ሰው ስለሚገደል? ወይስ በአማራ ክልል ባሉ የኦሮሞ ልዩ ዞን በወር 2 እና 3 ጊዜ በሚነሳ ብጥብጥ 20 ሰላሳ ሰው ስለሚገደል? ነው ወይስ መንግስ ት እንደፈለክ በነፃነት ተንቀሳቅሰህ የመስራት መብትህን ጠብቆልህ እንደልብህ አዲስ አበባ እንኳን መግባት ስላልቻልክ? ወይስ የአፊሪካ መዲና የምትባለውን የሁላችንም የሆነችውን ዋና ከተማ ጥቅልሎ ለኦሮሞ ስለሰጠልን ነው ፤ከመንግሥት ጎን የምንቆመው ?ነው ወይስ ለኦሮሞማው ኦነጋዊ ስርአት ላዳነች አብቤ እና ለሽመልስ ውይስ ለአብይ እና ታከለ ነው ግንባሬን ለጥይት የምሰጠው እስኪ ይሄን ማነው ሚመልስልኝ እና ግንባር ገብቼ እንድዘምት የሚሳምን ምክንያት የሚያቀርብልኝ??

ለኢንጅነር ልዋም እንድረስላት!! ይህች አንጀት የምትበላ እህታችን የ26 ዓመት ወጣት ነች!የደረሰባትን ስቃይ እንዲህ ትገልፃለች:-ልዋም ክንፈ እባላለሁ!! በትግራይ አድዋ ከተማ ተወልጄ ዓዲሀ...
29/08/2022

ለኢንጅነር ልዋም እንድረስላት!!
ይህች አንጀት የምትበላ እህታችን የ26 ዓመት ወጣት ነች!የደረሰባትን ስቃይ እንዲህ ትገልፃለች:-

ልዋም ክንፈ እባላለሁ!! በትግራይ አድዋ ከተማ ተወልጄ ዓዲሀቂ ት/ቤት ተምሬ በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ኤሌክትሪካልና ኮምፒዩተር ኢንጅነሪንግ ተመርቄያለሁ።

ለአንድ አመት በስራ ላይ እያለው እንደአለመታደል ሆኖ በአንጀት ካንሰር ተይዤ አልጋ ላይ እገኛለሁ::

ለመትረፍ ህክምና ቢያስፈልገኝም እንደምታውቁት ህክምናው አድካሚ እና ብዙ ወጪ የሚጠይቅ ነው።

ቤተሰቦቼ ጦርነቱ በሚካሄድባት ትግራይ ውስጥ ስላሉ የምፈልገውን እርዳታ ለማግኘት ተቸግሬያለሁ::

ከቅርብ ጓደኞቼ የማገኝው ድጋፍ የኑሮ እና የህክምና ወጪን የሚሸፍን አይደለምና እባካችሁን እርዱኝ🙏
ድኜ ወደ ስራዬ እንድመለስ ራሴን እንድችል አግዙኝ።
ሼር በማድረግ ተባበሩኝ
🙏 በፀሎታችሁ አስቡኝ!
"ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም"

አካውንት፦
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000349517829 -ልዋም ክንፈ
ስልክ
0925427388-ልዋም
0922874936-ራህዋ
0928574649-መቅደላዊት

https://youtu.be/ZOfXvVKQ2U0ዛሬ ፀሐይን ከባ የታየችው ቀስተ ዳመናቀን 29/07/2014 ዓም አዲስ አበባ ላይ እሔን ትመስል ነበር
07/04/2022

https://youtu.be/ZOfXvVKQ2U0
ዛሬ ፀሐይን ከባ የታየችው ቀስተ ዳመና
ቀን 29/07/2014 ዓም
አዲስ አበባ ላይ እሔን ትመስል ነበር

በአሜሪካን አገር ተሰሚነት ያለው የአማራ የመብት ታጋይ ይህን ብሏል "በ HR6600 ረቂቅ መሰረት በአማራ ላይ የዘር ፍጅት የፈፀሙ አካላት በሙሉ ተጠያቂ እንዲሆኑ ይደረጋል።" ይህን ያሉት የ...
24/03/2022

በአሜሪካን አገር ተሰሚነት ያለው የአማራ የመብት ታጋይ ይህን ብሏል
"በ HR6600 ረቂቅ መሰረት በአማራ ላይ የዘር ፍጅት የፈፀሙ አካላት በሙሉ ተጠያቂ እንዲሆኑ ይደረጋል።" ይህን ያሉት የአማራ ማህበራት በሰሜን አሜሪካ ሰብሳቢ ቴዎድሮስ ትርፌ ናቸው። በጉዳዩ ዙሪያ ከእንግሊዘኛ ወደ አማርኛ የተተረጎመው ንግግራቸው ቀጥሎ ቀርቧል።
~~
1. "ረቂቁን ተቃወሙ" የሚሉ ባለስልጣናት ጭንቀታቸው ኢትዮጵታያ እንዳትጎዳ ሳይሆን በሰሩት ወንጀል ልክ ተጠያቂ እንዳይሆኑ ነው፤ የኢትዮጵያ መጎዳት ቢያሳስባቸው ኖሮ ከ HR6600 ይልቅ ሀገሪቱ ውስጥ የሚፈሰው ደም ያስጨንቃቸው ነበር።
2. የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ሉዓላዊነት ትዝ የሚላቸው ስለ ማዕቀብና ቅጣት ሲሰሙ ነው ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ለተፈፀሙ ግድያዎች ተጠያቂ ላለመሆን በሀገር ሉዓላዊነት ስም ለመደበቅ ይሞክራሉ።
3. የዘር ማጥፋትን የሚፈፅም መንግስት የሚቀጣው አካል ሊኖር ይገባል፤ እንደ HR6600 አይነት ረቂቆች የማይኖሩ ከሆነ ያለ ጠያቂ የሚፈፀመው የአማራ ህዝብ መፈናቀልና ጅምላ ግድያ ይቀጥላል ማለት ነዉ። ስለዚህ የግድ አሳሪ ረቂቅ ተግባራዊ መደረግ አለበት።
4. የኢትዮጵያ መንግስት የ HR6600 ን መፅደቅ በድጋፍ መቋረጥ ስም ማስፈራሪያ አድርጎ ለመጠቀም ይሞክራል፤ እውነታው ግን ከውጪ የሚላኩ ድጋፎች የካድሬ ምሳና ራት ከመሆን አልዘለሉም። ዛሬ ድረስ የተፈናቀሉ ወገኖች በከፍተኛ ርሃብ ውስጥ ናቸውና። ስለዚህ ድጋፎች ባይቋረጡም ለአማራ ህዝብ አይደርሱም፤ ቢቋረጡም የተለዬ ነገር አይኖርም፤ የተለዬ ነገር ካለም ለካድሬው፣ ለጆሮ ጠቢውና ለገዳዩ የሚከፈል ገንዘብ እጥረት ነው።
5. HR6600 ረቂቅ ጉዳቱን ብቻ የማጉላት አዝማሚያ ይታያል። ከአማራ ህዝብ አንፃር ካየነው ከHR6600 ረቂቅ ይልቅ የአብይ አስተዳደር የሚፈፅመው ግፍ አውዳሚ ነው።
6. እኛ HR6600 የአማራን ህዝብ በማይጎዳ እና በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ፍጅት የፈፀሙ አካላትን ተጠያቂ በሚያደርግ መልኩ ተፈፃሚ እንዲሆን እየሰራን ነው።
7. የHR6600 ረቂቅ የኢትዮጵያ መንግስትን ያዳክመዋል፤ ብሄር ለይቶ የሚጨፈጭፍ መንግስት መዳከሙ እንጂ መጠናከሩ ምን ይጠቅማል? መሳሪያ ያጣል? ይጣ፤ መሳሪያ ኖሮት የትኛውን ህዝብ ከየትኛው ግድያ አዳነ?
8. ሌላው የባለስልጣናቱ ጭንቀት መንስኤ የHR6600 በዘር ፍጅት ወንጀል የሚከሰሱ ባለስልጣናት ክስ የሚመሰርት መሆኑ ነው፤ ይሄንን ነው "አሜሪካ ሉዓላዊነታችንን ተዳፈረች፣ እጅ ጠመዘዘች" እያሉ የሌለ ምስል ለመፍጠር የሚሞክሩት።
9. ያም ሆነ ይህ በአማራ ህዝብ ላይ የሚደረግ ግድያ፣ መፈናቀልና መገፋት በማንኛውም መንገድ መቆም አለበት፤ ይህንን የአብይ አስተዳደር ሊያደርገው ስላልቻለ የሚገደድበትን መንገድ ማዘጋጀት ግድ ነው፤ ከዛ መንገድ ውስጥ አንዱ HR6600 ነው።

ጠላት 350 ኪ.ሜ በሚሸፍን የአፋር አካባቢ ላይ በሙሉ አቅሙ ወረራ በማድረግ አዲስ የጦር ግንባሮችን ከፍቶ ከፍተኛ ጦርነት እየተከሄደ ነዉ። ይህንን የጠላት ወረራ መመከት ለአፋር ሚሊሻ ብቻ ...
24/01/2022

ጠላት 350 ኪ.ሜ በሚሸፍን የአፋር አካባቢ ላይ በሙሉ አቅሙ ወረራ በማድረግ አዲስ የጦር ግንባሮችን ከፍቶ ከፍተኛ ጦርነት እየተከሄደ ነዉ። ይህንን የጠላት ወረራ መመከት ለአፋር ሚሊሻ ብቻ የተተወ ይመስላል። እስካሁን ድረስ ባለን መረጃ መሠረት አንድም መከላከያ አልገባም። ታድያ ይህ ጉዳይ የኢትዮጵያ መንግስትን አይመለከትም ማለት ነዉን?

ሔኖክ ዓለሙ እና ጌዴዎን ልዑልሰገድ ይባላሉ። ለበዓለ ጥምቀት የገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ አጥቢያ ባዘጋጀው ቅርጽ የተነሣ ታስረዋል። "ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ታደርሳለች" የሚለውን...
24/01/2022

ሔኖክ ዓለሙ እና ጌዴዎን ልዑልሰገድ ይባላሉ። ለበዓለ ጥምቀት የገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ አጥቢያ ባዘጋጀው ቅርጽ የተነሣ ታስረዋል።

"ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ታደርሳለች" የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል በእጅ ጥበብ ቀርጸው በመሥራታቸው መንግሥት ምኑ እንደተነካ ባይገለጥልንም የማሳደጃ ምክንያት አድርጎታል። በዕለቱ ቅርጹን አፈረሰ ከዚያም ወጣቶቹን አሰረ።

ከአኖሌ ጋር አያይዘው ተርጉመውት ይኾናል። ያ ተስፋዬ ሠራሽ ይህ እግዚአብሔር ሠራሽ። የትና የት?

ለመነሣት የሚኾን ብዙ ምክንያት አለን።

እባካችሁ በፍጥነት #አዛምቱ ( )Dewol

25ቱ ለኢትዮጲያ ብሄራዊ ውይይት አመቻች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት አብላጫ ድምፅ ያገኙ እጩዎች▬▬▬▬▬▬▬▬▬1-ዶ/ር ሰሚር ዩሱፍ 2-ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም (በኢትዮጲያ የኦሮሚያ መጅሊስ ፕሬዘደንትና...
22/01/2022

25ቱ ለኢትዮጲያ ብሄራዊ ውይይት አመቻች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት አብላጫ ድምፅ ያገኙ እጩዎች
▬▬▬▬▬▬▬▬▬

1-ዶ/ር ሰሚር ዩሱፍ
2-ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም (በኢትዮጲያ የኦሮሚያ መጅሊስ ፕሬዘደንትና የሀገር ሽማግሌ)
3-መጋቢ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ(ከኦርቶዶክ ተዋህዶ ቤ/ህ መምህር)
4-ፕ/ር ሙሐመድ ሐቢብ
5-አቶ ለማ መገርሳ
6-አቶ ሐቢብ ሙሀመድ ያዮ(የቀድሞ የአሰብ ራስገዝ የመከላከያ አስተዳድር መምሪያ ኋላፊ የሱልጧን ሙሀመድ ያዮ ልጅ)
7-ዶ/ር አሚር አማን-(የቀድሞ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር)
8-ረ/ፕ አደም ካሚል
9-አባገዳ በየነ ሰንበቶ
10-የትነበርሽ ንጉሴ(በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ እና የአካል ጉዳተኛ መብትቶች ተሟጋች ናት)
11-ጠበቃ ተማም አባቡልጉ
12-አቶ አብዱልዋሲዕ አመንዲድ(የዩኒቨርስቲ መምህርና የተለያዩ ኮሌጆችና ት/ቤ ፕሬዝደንት)
13-አትሌት ደራርቱ ቱሉ
14-አቶ ዑመር አብዱረዛቅ(የሕዝበ ሙስሊሙ መፍትሔ አፈላላጊ አባል)
15-አቶ ጀማል አህመድ (የሜድሮክ ዋና ስራ አስፈጻሚ)
16-ዶ/ር ፋዒዝ ሙሀመድ ቃሲም(የዩኒቨርስቲ መምህር፣ ተመራማሪና አሰልጣኝ)
17-አቶ መሕዲ አህመድ ገዲድ(በጃፓን፣ በኢንዶኖዢያ፣ ፊሊፒንስ አምባሳደር፤ የዩኒቨርስቲ መምህር፣ በአፍሪካ የውጪ ጉዳይና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አማካሪ...)
18-ወ/ሮ መዓዛ ብሩ
19- ፕ/ር ያዕቆም ኃ/ማ
20-ሐጅ ሁሴን ላለምዳ ሀምዛ (በተለያዩ ጊዜያት የሀገር ሽማግሌ በመሆን ያገለገሉ።)
21-ኡስታዝ አህመዲን ጀበል
22- አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ
23-አርቲስት አበበ ባልቻ
24-ጋዜጠኛ ሰይድ ኪያር
25-አቶ በለጠ ባሹ(የሀገር ሽማግሌ)

H.D Hekena

ይሄ ባንዲራ ጣሊያንን አዋርዷልበአባቶቻችን ክንድ ክፉኛ ተደቁሷልነገር ግን አበበ ቢቂላ ሮም ላይ በባዶ እግሩ ሮጦ ሲያሸንፍ ይኽን ባንዲራ ለብሷል!!ዛሬም የጥምቀት በዓል በጣሊያን ግዛት ሲከበ...
22/01/2022

ይሄ ባንዲራ ጣሊያንን አዋርዷል
በአባቶቻችን ክንድ ክፉኛ ተደቁሷል
ነገር ግን አበበ ቢቂላ ሮም ላይ በባዶ እግሩ ሮጦ ሲያሸንፍ ይኽን ባንዲራ ለብሷል!!
ዛሬም የጥምቀት በዓል በጣሊያን ግዛት ሲከበር ኦርቶዶክሳውያን ውለብልበውታል!!
ነገር ግን ጣሊያን ምንም አላለችም ከነሱ በላይ ባንዲራን ለመጥላት ምክንያት ያለው ሀገር የለም ነገር ግን ምንም ብለው አያውቁም

የኛሆቹ ግን የባንዲራ ፎቢያ አለቀቃቸውም
👇👇👇👇👇👇👇 ይነበብ👇👇👇
በአሌልቱ ከተማ የታሰሩ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶች
ቁጥራቸው ከሃያ ስድስት በላይ ደርሷል!

በዚሁ በዘንድሮ የጥምቀት በዓል ላይ የቃና ዘገሊላ በዓል የቅዱስ ሚካኤልን ታቦት ይዘው ወደ ቤተ ክርስቲያን እየገቡ ሳለ የአሌልቱ ከተማ ላይ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል እነዚኸን ኦርቶዶክሳዊያን የተዋህዶ ልጆች በለበሱት ልብስ ምክንያት አስሯቸዋል ።

ከሃያ ስድስት በላይ የታሰሩ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶች ታቦት አጅበው ክርስቶስን በማምለካቸው ሳቢያ አሁን ላይ በአሌልቱ ከተማ እንደታሰሩ ታውቋል ። በፍጥነት እነዚኸን ወጣቶች ፍቱ! ...

የልጆቹ ጥፋት ኢትዮጵያ የሚል ጽሁፍ ያለበት አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለም ያለው ልብስ መልበሳቸው ብቻ ነው ። ይኸ ደግሞ መብታቸው ነው ። ለእናት አገራቸውም ሆነ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያላቸውን ፍቅር የሚገልጹበት መንገድ እእከሆነ ድረስ የመረጡትን መንገድ ማክበር የሁላችንም ግዴታ ነው ።


ዘካርያስ ኪሮስ

የወይ ብላ ማርያምን ታቦት ወደ መንበሯ እንዳትመለስ ፖሊስ ከለከለ። የሺ ደበሌ አካባቢ የምትገኘውን የወይ ብላ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ዛሬ ወደ መንበሯ ስትመለስ ፖሊስና በአካባቢው ያሉ ወጣቶ...
20/01/2022

የወይ ብላ ማርያምን ታቦት ወደ መንበሯ እንዳትመለስ ፖሊስ ከለከለ።
የሺ ደበሌ አካባቢ የምትገኘውን የወይ ብላ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ዛሬ ወደ መንበሯ ስትመለስ ፖሊስና በአካባቢው ያሉ ወጣቶች በፈጠሩት ግርግር ሰላምን የሚያደፈርስ ችግር በመከሠቱ ታቦቱ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እንዳያልፍ ተደርጓል። በመሆኑም አሁን ወደ ኋላ ተመልሶ በቀራንዮ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን እንዲገባ ተደርጓል።
በሥፍራው ከነበሩ የዐይን እማኞች ምስክርነት ማወቅ እንደተቻለው ፖሊስ በአንገታቸው እና በክንዳቸው ላይ ባሠሯቸው፣ በቲሸርት መልክ ያሰፉትን አረንጓዴ ቢጫበ ቀይ ቀለም ያላቸውን ነገሮች ሁሉ ካላወለቃችሁ አታልፉም በማለት ፖሊስና ፖሊስ ያደራጃቸው ያካባቢው ወጣቶች በፈጠሩት ማዋከብ ነው ችግሩ የተከሰተው። የቤተ ክርስቲያን አርማ ያለበትን ሰንደቅ እንጂ ሌላ ነገር ያልያዙት ታቦት የሚያጅቡ ምእመናን ወደ ኦሮሚያ ክልል ማለፍ የምትችሉት የለበሳችሁትን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቲ ሸርት ካውልቃችሁ ብቻ ነው የሚለውን የፖሊስ ሕገ ወጥ ትእዛዝ በመቃወማቸው ለድብደባ ተዳርገዋል። ፖሊስ በምእመናንን ላይ አስለቃሽ ጭስ ተኩሷል። የተጎዱ አገልጋዮች እና ምእመናን እንዳሉም የዐይን እማኞቹ ተናግረዋል።

ጴጥሮሳውያን የቤተ ክርስቲያን ክብርና መብት አስጠባቂ ኅብረት

Address

Addis Ababa
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ወቅታዊ መረጃዎች posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share