CNN Ethiopia

CNN Ethiopia Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from CNN Ethiopia, Media Agency, Addis Ababa.

ሰበር  የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ምክትል አዛዥ፣ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል ወታደራዊ አዛዥ ኮ/ል ማነገረዉ መለስ መዘዞ ከተማ  እጁን ለመንግሥት የፀጥታ ሃይሎች ። ግለሰቡ በቡድኑ ዉስጥ ከፍ...
17/03/2026

ሰበር

የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ምክትል አዛዥ፣ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል ወታደራዊ አዛዥ ኮ/ል ማነገረዉ መለስ መዘዞ ከተማ እጁን ለመንግሥት የፀጥታ ሃይሎች ።

ግለሰቡ በቡድኑ ዉስጥ ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጣሪ የነበረ ቡድኑንም ከመሰረቱ ዋነኛዉ የነበር።

በአሁኑ ሰዓት በጣርማ በር ወረዳ ጣርማ በር ዋሻዉ ላይ ለጀግናው መከላከያ ሰራዊት እጅ ሰጧል።

ሕወሓት አሁንም ለዳግም ጦርነት እየተዘጋጀ ነው=======ሕወሓት ለዳግም የጦርነት ቅድመ ዝግጅት ተግባራት ማስታወቂያ የሚከተለውን ማስታወቂያ አውጥቷል።       "ማስታወቂያ ከአሁን በፊት በ...
11/03/2026

ሕወሓት አሁንም ለዳግም ጦርነት እየተዘጋጀ ነው
=======
ሕወሓት ለዳግም የጦርነት ቅድመ ዝግጅት ተግባራት ማስታወቂያ የሚከተለውን ማስታወቂያ አውጥቷል።

"ማስታወቂያ

ከአሁን በፊት በትግራይ ጄኖሳይዳዊ ጦርነት ለመመከት ትግል ላይ የነበራችሁ፦

1.ግዳጃችሁ ፈፅማችሁ በክብር የተመለሳችሁ ወደ ነበራችሁበት አሃዱ እንድትመለሱ፤

2.በተለያየ ምክንያት ከአሃዱ ተንጠባጥባችሁ የተመለሳችሁ፤

3.አርሚ ማሰልጠኛዎች ባለማወቅ የተመለሳችሁ

4.መከላከያ ሰራዊት የነበራችሁ በማንነታችሁ በእስር የቆያችሁ፤

5. ወደ ስልጠና ማዕከላት በመግባት ስልጠና መውሰድ የምትፈልጉ ወጣቶች ጥሪ ተደርጎላችኋል።

በዚህ መሰረት መመዝገብ የምትፈልጉ ከዛሬ ቀን መጋቢት 01/2018 ዓ/ም ከነሰቅገ ወረዳ አስተዳደር የመጣችሁ እንድትመዘገቡ ጥሪ እናስተላልፋን

ከሰላምታ ጋር
ነቅሰገ ወረዳ አስተዳደር"

የምዕራብ ጎጃም ዞን የአስተዳደር መቀመጫ የሆነችው ፍኖተ ሰላም ከተማ===የኢትዮጵያ ከተሞች በኮሪደር ልማት መልክና ገጽታቸው እየተቀየረ ነው። ወበታቸው እየተገለጠ ዘመናዊነትን እየተላበሱ ነው...
03/01/2026

የምዕራብ ጎጃም ዞን የአስተዳደር መቀመጫ የሆነችው ፍኖተ ሰላም ከተማ
===
የኢትዮጵያ ከተሞች በኮሪደር ልማት መልክና ገጽታቸው እየተቀየረ ነው። ወበታቸው እየተገለጠ ዘመናዊነትን እየተላበሱ ነው።

በአማራ ክልል የምዕራብ ጎጃም ዞን አስተዳደር መቀመጫ የሆነችው ፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ከተማዋን ለማስዋብ የኮሪደር ልማት ዲዛይን አዘጋጅቶ በቅርቡ ወደ ለመግባት እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል።

የኮሪደር ልማት የከተሞችን ተወዳዳሪነት ያሳድጋል፤ ከተሞች ለነዋሪዎች ተመራጭ እና ስልጡን ከተማ በመፍጠር እረገድ አይተኬ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።

በባሕርዳር 27 ነጋዴዎች ታሰሩ××××ש×××××በባሕርዳር ከተማ ተመሳጥረው በዘይት ምርት ላይ ዋጋ የጨመሩ ነጋዴዎች ታሰሩበባሕርዳር ከተማ አሳማኝ ምክንያት በሌለበት ተመሳጥረው በዘይት ምርት...
03/11/2025

በባሕርዳር 27 ነጋዴዎች ታሰሩ
××××ש×××××
በባሕርዳር ከተማ ተመሳጥረው በዘይት ምርት ላይ ዋጋ የጨመሩ ነጋዴዎች ታሰሩ

በባሕርዳር ከተማ አሳማኝ ምክንያት በሌለበት ተመሳጥረው በዘይት ምርት ላይ የዋጋ ጭማሪ ያደረጉ 27 ነጋዴዎች መታሰራቸውን የከተማ አስተዳደሩ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አስታውቋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ 221 ድርጅቶች እና 8 ስቶሮችን በማሸግ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱም ተገልጿል።

በከተማው ዘይትን ጨምሮ የኢንዱስትሪ ምርቶች ላይ የታየውን የዋጋ ጭማሪ እና ምርት ስወራ አስተመልክቶ የባሕርዳር ከተማ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አደራ ጋሼ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

ለመንግስት ሠራተኞች የተደረገውን የደሞዝ ማሻሻያ ተከትሎ በግብይት ላይ እየተፈጠረ ያለውን ጭማሪ ለመግታት እየተሰራ መሆኑ በመግለጫው ተመላክቷል።

ጭማሪው በኢንደስትሪ ምርቶች ላይ በተለይም ስኳርና ዘይት ላይ መታየቱን ገልጸው፤ በተለይ የዘይት ምርት ላይ የታየው ጭማሪ ቀድሞ በገበያው ከነበረበት ከ80 እስከ 100 ብር የሚደርስ ጭማሪ ማሳየቱ ነው የተጠቀሰው።

በዘይት ምርቶች ላይ የሀገርውስጥ የዘይት ምርት አከፋፋዮች ጭማሪ አድርገው መልሰው ወደ ነበረበት ማውረዳቸውን አስተውለናል ያሉት ኃላፊው፤ ከጭማሪ ባለፈ ምርት የመደበቅ እንቅስቃሴ ታይቷል ብለዋል፡፡

በአንፃሩ የግብርና ምርቶች የተረጋጋ ዋጋ ላይ ይገኛሉ ሲሉ ገልጸዋል።

በገበያ በምርቶች ላይ ከታየው ጭማሪ ባለፈ፣ በቤት ኪራይ ላይ ተስተውሏል የተባለውን የዋጋ ጭማሪ በመመርመር ላይ መሆናቸውን ኃላፊው አንስተዋል።

ለዚህም ከደሞዝ ማሻሻያው በፊት ከነበረው ዋጋ የተለየ ጭማሪ የተደረገባቸው ግለሰቦች በክፍለ ከተሞች መበቅረብ ጥቆማ መስጠት እንደሚኖርባቸው ገልጸዋል፡፡

ገበያው ላይ የታየው ንረት ህዝብን በማማረር ከመንግስት ሀሳብ የመነጠል ፍላጎት ነውያሉት ኃላፊው፤ ለሕግ ተገዥና ምስጉን ነጋዴዎች፣ የመንግስት ሠራተኛው መላ ማህበረሰቡ እና የፀጥታ አካላት ለሕግ ማስከበር ተግባሩ ስኬታማነት በጋራ እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ፑቲን በታላቁ  ህዳሴ ግድብ የምረቃ መርሃ ግብር ላይ ሊጋበዙ ይችላሉ   በኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን እንዲገኙ የኢትዮጵያ መንግሥት  ግብዣ...
06/07/2025

ፑቲን በታላቁ ህዳሴ ግድብ የምረቃ መርሃ ግብር ላይ ሊጋበዙ ይችላሉ

በኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን እንዲገኙ የኢትዮጵያ መንግሥት ግብዣ ሊልክ እንደሚችል ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡

ባለፈው ሳምንት በፓርላማ ተገኝተው ለህዝብ ተወካይ ም/ቤት አባላት ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፣ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ክረምቱ እንደወጣ በመስከረም ላይ እንደሚመረቅና በዚህ ታላቅ በዓል ላይ የግብጽና ሱዳን ባለሥልጣት እንዲገኙ በይፋ መጋበዛቸው ይታወሳል፡፡

በሌላ በኩል፣ የግብጽ ውሃና መስኖ ሚኒስትር፤ ‹‹የግብፅን ውሀ መብት በመቀነስ የኢትዮጵያን ልማት ለማምጣት የሚደረግ ማናቸውንም ጥረት አንቀበልም›› ሲሉ መናገራቸው ተዘግቧል፡፡

የግብፅ ውሀና መስኖ ሚኒስትር ዶ/ር ሀኒ ስዊላም ይህን ያሉት፣ ዛሬ ከአገራቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በመሆን በውጭ አገራት ለተሾሙ አዳዲስ አምባሳደሮች የስራ መመሪያ በሰጡበት ወቅት ነው ተብሏል፡፡

አል-ፋሽጋ ዳግም በኢትዮጵያውያን እጅ ገባለዘመናት የኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች የእርሻና የኑሮ መሰረት የነበረው ለም መሬት፣ አል-ፋሽጋ፣ ዳግም ወደ ህጋዊ ባለቤቶቹ ተመልሷል። የኢትዮጵያ ፌ...
06/07/2025

አል-ፋሽጋ ዳግም በኢትዮጵያውያን እጅ ገባ

ለዘመናት የኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች የእርሻና የኑሮ መሰረት የነበረው ለም መሬት፣ አል-ፋሽጋ፣ ዳግም ወደ ህጋዊ ባለቤቶቹ ተመልሷል።

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ መንግስት በትግራይ ክልል የህግ ማስከበር ዘመቻ ላይ በነበረበት ወቅት የተፈጠረውን ክፍተት በመጠቀም፣በሱዳን ጦር ተወርሮ የነበረው ሰፊና ለም መሬት፣ አሁን በጀግኖች ኢትዮጵያውያን ገበሬዎችና ሚሊሻዎች ቁጥጥር ስር ውሏል።

የሱዳን ጦር የኢትዮጵያን የውስጥ ችግር እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር፣ በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎንደር ዞን የሚገኙትን የመተማና የቋራ ወረዳ ለም መሬቶችን በኃይል ተቆጣጥሮ ነበር።

በወቅቱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በቅርብ ርቀት ላይ ሆኖ ሁኔታውን በትዕግስት ሲከታተል የነበረ ሲሆን፣ መንግሥትም ችግሩን በዲፕሎማሲና በውይይት ለመፍታት ያለውን ፍላጎት በተደጋጋሚ መግለጹ ይታወሳል፡፡

በዚህ የሱዳን ወረራ ወቅት ኢትዮጵያውያን ገበሬዎች ከእርሻቸው ከመፈናቀላቸውም በላይ ከፍተኛ የሆነ የሰብልና የንብረት ውድመት እንደደረሰባቸው አይዘነጋም፡፡

የሱዳን ባለሥልጣናት ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ታጣቂዎች በአገሪቱ መከላከያ ሠራዊት በመታገዝ የአማራ ክልል አዋሳኝ ወደኾኑ የሱዳን ለም መሬቶች በመስፋፋት ላይ ናቸው ሲሉ መክሰሳቸው ተዘግቦ ነበር፡፡

በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ከታቀደው በላይ ምርት ይጠበቃል ተባለ>>>>>>>©>>>>>>በአማራ ብሔራዊ ክልል በተያዘው በጀት ዓመት ከታቀደው በላይ ምርት እንደሚገኝ ተተነበየ።በክልሉ ለመኸር...
26/10/2024

በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ከታቀደው በላይ ምርት ይጠበቃል ተባለ
>>>>>>>©>>>>>>
በአማራ ብሔራዊ ክልል በተያዘው በጀት ዓመት ከታቀደው በላይ ምርት እንደሚገኝ ተተነበየ።

በክልሉ ለመኸር ሰብል ልማት ከቅድመ ዝግጅት እስከ ተግባር ምዕራፍ በተሰራው ስራ በሁሉም የሰብል ዓይነት ከታቀደው በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ተገልጿል።

በበጀት ዓመቱ በቂ የግብርና ምርት ማሳደጊያ ግብአት አቅርቦትና ስርጭት፣ ተስማሚ የአየር ንብረትና ወቅቱን የጠበቀ የዝናብ መጠን የነበረበት በመሆኑ ከፍተኛ ምርት ይጠበቃል ተብሏል።

በግብርናው ዘርፍ ኑሮውን የመሰረው አርሶ አደርና በበክልሉ በዘርፉ የተሰማሩ ባለሃብቶች በመኸር ሰብል ልማት የታየውን እምርታዊ የሰብል ልማት ከብክነት በፀዳ መንገድ እንዲሰበስቡ የክልሉ ግብርና ቢሮ ጥሪ አቅርቧል።

CNN Ethiopia

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when CNN Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category