አጋልጥ - Expose

አጋልጥ - Expose Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from አጋልጥ - Expose, Social Media Agency, Addis Abeba, Addis Ababa.

አጋልጥ - Expose is the first fact-checking page in Ethiopia. አጋልጥ - Expose works it's part to ensure the dissemination of factual information and to limit the influnce of fake news and scammers. አጋልጥ በኢትዮጲያ የመጀመሪያው የእውነታ ማጣሪያ የፌስቡክ ገጽ ነው። ሁሉም ኢትዮጲያዊ እውነተኛ መረጃ የማግኘት መብቱ እንዲረጋገጥ የበኩላቸውን ጥረት በሚያደርጉ በጎ ፈቃደኞች የተመሰረተ ገጽ ነው። ዋና ዓላማው ኢትዮጲያ ላይ አተኩረው የሚሰሩ ዲጂታል ሜዲያወችን በተለይም በማህበራዊ ሜዲያ የሚወጡ ኢትዮጲያን የሚመለ

ከቱ መረጃወችን በመከታተል ሀሰትን ለይቶ የማጋለጥ፣ እውነትን የማጣራትና ለተደራሾቹ የማንቂያ መረጃ መስጠት ነው። በተጨማሪም ስለ ሀሰተኛ መረጃ ስርጭት መንገዶች፣ አሉታዊ ተጽእኖው እና ጉዳቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ አገልግሎትም ይሰጣል።

ብሔራዊ ባንክ በሕገ-ወጥ የገንዘብ አስተላላፊዎች ላይ የሰጠው ማስጠንቀቂያ++++++++++++++   - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፤ 23 የ...
06/04/2026

ብሔራዊ ባንክ በሕገ-ወጥ የገንዘብ አስተላላፊዎች ላይ የሰጠው ማስጠንቀቂያ
++++++++++++++

- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፤ 23 የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች ያለባንኩ እውቅና እና ፈቃድ እየሰሩ መሆኑን ገልጿል።

እነዚህ ተቋማት ከመጀመሪያው ፈቃድ የሌላቸው ወይም ቀደም ሲል የነበራቸው ፈቃድ በሕገ-ወጥ ተግባራት ምክንያት የተሰረዘ መሆኑን ባንኩ አረጋግጧል።

ኅብረተሰቡ የገንዘብ ደህንነቱን ለመጠበቅና በሕገ-ወጥ ተግባራት ውስጥ እንዳይሳተፍ በእነዚህ ድርጅቶች በኩል ገንዘብ ከመላክ እንዲቆጠብ ባንኩ አሳስቧል። በኢትዮጵያ ውስጥ የገንዘብ ዝውውር አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ሕጋዊ የሥራ ፈቃድ የሌላቸው ናቸውም ብሏል።

እነዚህም ድርጅቶች አዱሊስ መኒ ትራንስፈር፤ አማና ኤክስፕረስ፤ አዋሽ ዳይሬክት፤ ባካኣል መኒ ትራንስፈር፤ ሆልደን ግሎባል፤ ኦሊምፒክ ፋይናንሻል ግሩፕ ፤ ታአጅ መኒ ትራንስፈር፤ ዋይዝ ትሬዲንግ መኒ ትራንስፈር፤ ወርልድ ዳይሬክት ሊንክ እና ሌሎችም እንደሚገኙበት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል፡፡

ማንኛውም የውጭ ሀገር የገንዘብ ዝውውር በሕጋዊ የባንኮችና እውቅና ባላቸው የገንዘብ አስተላላፊ ወኪሎች በኩል ብቻ መከናወን እንዳለበት ተገልጿል።

በሀና እጅጋየው

#ጥንቃቄ

የጥራት ጉድለት የታየበት የፌኒቶይን መድኃኒት በአስቸኳይ እንዲመለስ ታዘዘ +++++++++++++++   የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የባህር ዳር ቅርንጫፍ፣ ሜዲካመን ባዮቴክ ሊሚትድ...
31/03/2026

የጥራት ጉድለት የታየበት የፌኒቶይን መድኃኒት በአስቸኳይ እንዲመለስ ታዘዘ
+++++++++++++++

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የባህር ዳር ቅርንጫፍ፣ ሜዲካመን ባዮቴክ ሊሚትድ በተባለ ኩባንያ የተመረተ ለሚጥል በሽታ (Epilepsy) መቆጣጠሪያ የሚያገለግለውን የፌኒቶይን 100 ሚሊ ግራም (Phenytoin 100 mg) ታብሌት መድኃኒት የጥራት ችግር ስላለበት ከጤና ተቋማት በአስቸኳይ እንዲሰበሰብ በደብዳቤ ማዘዙን አስታወቀ።

የቅርንጫፍ መሥሪያ ቤት ለሁሉም የጤና ተቋማት በጻፈው ደብዳቤ ላይ እንደገለጸው፣ በአምራቹ የተመረቱት የዚህ መድኃኒት ባቾች በሙሉ የጥራት ደረጃውን ባለማሟላቱ ተመላሽ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

ይሁን እንጂ እስካሁን መድኃኒቱን የመለሱ ቢሆንም፣ መድኃኒቱን ያልመለሱ ተቋማት ያላቸውን ቀሪ መጠን በደብዳቤ ገልጸው እስከ መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንዲያሳውቁ ጥብቅ ማሳሰቢያ ቢሰጥም፣ እስካሁን ድረስ አንዳንድ የጤና ተቋማት አለመመለሳቸውን አገልግሎቱ ገልጿል።

ይህንን ትዕዛዝ ተላልፈው መድኃኒቱን ተመላሽ የማያደርጉ ተቋማት ለሚከሰት ለጤና መታወክ ሙሉ ኃላፊነቱን እንደሚወስዱ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በመረጃው እንዳመላከተው በተጠቀሰው ባች የተመረተው ምርት ከ19ኙም የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እንዲሰበሰቡ አሳስቧል። ዜጎች ለሚጥል በሽታ መድኃኒት ሲጠቀሙ በጤና ባለሙያ የታዘዘላቸውና ጥራቱ የተረጋገጠ መሆኑን እንዲያረጋግጡ ይመከራል።

በሀና እጅጋየሁ
#ተጠንቀቁ

ዩናይትድ ስቴትስ የኤፍ-15ኢ (F-15E) የጦር አውሮፕላን በኢራን ውስጥ ወደቀ ተብሎ የሚናፈሰው ወሬ መሰረተ ቢስ እና ሀሰት መሆኑን ገለጸች። ያልተረጋገጡ የሶሻል ሚዲያ ዘገባዎች መጋቢት 4...
05/03/2026

ዩናይትድ ስቴትስ የኤፍ-15ኢ (F-15E) የጦር አውሮፕላን በኢራን ውስጥ ወደቀ ተብሎ የሚናፈሰው ወሬ መሰረተ ቢስ እና ሀሰት መሆኑን ገለጸች። ያልተረጋገጡ የሶሻል ሚዲያ ዘገባዎች መጋቢት 4 ቀን (March 4) ጥቃት በሚሰነዘርበት ወቅት አንድ የዩኤስ ኤፍ-15ኢ በደቡብ ምዕራብ ኢራን መውደቁን ገልጸው ነበር። የማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ዛሬ ባወጣው መግለጫ እነዚህ ዘገባዎች "መሰረተ ቢስ እና ሐሰት" ናቸው ብሏል።

የቀድሞው የኢራን ፕሬዝዳንት ማህሙድ አህመዲነጃድ በሕይወት መኖራቸው ተረጋገጠየቀድሞው የኢራን ፕሬዝዳንት ማህሙድ አህመዲነጃድ ደህንነታቸው የተጠበቀና በሕይወት እንደሚገኙ የቅርብ አማካሪያቸው ...
03/03/2026

የቀድሞው የኢራን ፕሬዝዳንት ማህሙድ አህመዲነጃድ በሕይወት መኖራቸው ተረጋገጠ

የቀድሞው የኢራን ፕሬዝዳንት ማህሙድ አህመዲነጃድ ደህንነታቸው የተጠበቀና በሕይወት እንደሚገኙ የቅርብ አማካሪያቸው ለአናዶሉ የዜና ወኪል ገለጹ።

አሜሪካና እስራኤል በጋራ በመሆን የኢራንን ከፍተኛ አመራሮችና ወታደራዊ መሠረተ ልማቶችን ኢላማ ባደረገ ጥቃት መክፈታቸውን ተከትሎ አህመዲነጃድ ተገድለዋል የሚሉ ዘገባዎች ተሰራጭተው ነበር። ሆኖም ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉት አማካሪያቸው “ከእሳቸው ጋር ተገናኝቻለሁ ሁሉም ነገር ሰላም ነው” ሲሉ ወሬውን አስተባብለዋል።

እንደ አማካሪው ገለጻ ትናንት በተሰነዘረው ጥቃት ከአህመዲነጃድ የደህንነት ጥበቃ ጋር ግንኙነት ያለው ሕንፃ ተመትቷል በጥቃቱም
የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ (IRGC) አባል የሆኑ ሦስት የግል ጠባቂዎቻቸው ተገድለዋል የፕሬዝዳንቱ መኖሪያ ቤት ጥቃቱ ከፈጸመበት ሕንፃ 100 ሜትር ያህል ርቀት ላይ የሚገኝ ቢሆንም ቤቱ ኢላማ አልተደረገም እንዲሁም ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰበትም።

ማህሙድ አህመዲነጃድ ከ2005 እስከ 2013 እ.ኤ.አ. ድረስ በፕሬዝዳንትነት ያገለገሉ ሲሆን ይህ ማረጋገጫ የተሰጠው በእስራኤልና አሜሪካ የአየር ድብደባ ተገድለዋል የሚለው መረጃ በስፋት ከተሰማ በኋላ ነው።

ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በአል ናስር ልምምድ ላይ ተገኘ!"ከሳውዲ ወጥቷል" የሚባለው ወሬ ሀሰት መሆኑ ተረጋገጠ።በማህበራዊ ሚዲያ እና በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን "ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ሳውዲ አረቢያን...
03/03/2026

ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በአል ናስር ልምምድ ላይ ተገኘ!

"ከሳውዲ ወጥቷል" የሚባለው ወሬ ሀሰት መሆኑ ተረጋገጠ።

በማህበራዊ ሚዲያ እና በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን "ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ሳውዲ አረቢያን ለቆ ወደ ስፔን አምርቷል" በሚል ሲሰራጭ የነበረው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑ ተረጋግጧል።

የአል ናስር ስፖርት ክለብ ዛሬ ባወጣው ይፋዊ መረጃ፣ ተጫዋቹ ከቡድን አጋሮቹ ጋር መደበኛ ልምምዱን በደመቀ ሁኔታ ማከናወኑን አስታውቋል።

* ሮናልዶ ዛሬ በክለቡ የልምምድ ሜዳ ላይ በመገኘት ለቀጣይ ጨዋታዎች ዝግጁ መሆኑን አሳይቷል።

* CR7 ስራውን የሚያከብር እና ለክለቡ ያለውን ታማኝነት በተግባር የሚያሳይ ፕሮፌሽናል ተጫዋች መሆኑን በድጋሚ አስመስክሯል።

ደጋፊዎች በማይታወቁ ምንጮች በሚሰራጩ የሃሰት ወሬዎች እንዳይደናገሩ እና ሁሌም ቢሆን ትክክለኛ መረጃዎችን ከክለቡ ይፋዊ ገጾች ብቻ እንዲከታተሉ ተመክሯል።

ትክክለኛ መረጃ እና እውነተኛ ዘገባን ከምንጩ ይረዱ!

©️Al Nassr Saudi Club

" መረጃው ፍፁም የተሳሳተ በመሆኑ ሊታረም ይገባል " - ሚኒስቴሩየሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር " ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የፍቺ ቁጥር ለመቀነስ፣ የቅድመ ጋብቻ ስልጠና ሰርተፊ...
14/02/2026

" መረጃው ፍፁም የተሳሳተ በመሆኑ ሊታረም ይገባል " - ሚኒስቴሩ

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር " ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የፍቺ ቁጥር ለመቀነስ፣ የቅድመ ጋብቻ ስልጠና ሰርተፊኬት ሳይዝ ማንም ሰው ወደ ጋብቻ እንዳይገባ የሚያደርግ አሰራር ሊጀምር ነው " በሚል የተሰራጨውን ዘገባ የተሳሳተ ነው አለ።

‎ሚኒስቴሩ " ጥንዶች ስለሚጀምሩት አዲስ የሕይወት ምዕራፍ በቂ ዕውቀት እንዲኖራቸውና ጠንካራ ቤተሠብ መመስረት እንዲችሉ ለማድረግ የቅድመ ጋብቻ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት አስፈላጊ መሆኑን በውል እንገነዘባለን " ብሏል።

" ‎ይህ በተለያዩ ሀገራት እንደ አንድ መፍትሔ ተደርጎ እየተሰራበት እና በሀገራችንም አንዳንድ የሃይማኖት ተቋማት በዚህ ላይ እየሰሩበት እንደሚገኙ ይታወቃል " ሲል ገልጿል።

ይሁን እንጂ ሚኒስቴሩ " ከሚቀጥለው አመት ጀምሮ አስገዳጅ ለማድረግ ያለመ የአሰራር ማዕቀፍ እያዘጋጀ ነው " የሚለው ፍፁም የተሳሳተ መረጃ በመሆኑ ሊታረም ይገባል ሲል አሳውቋል።

" ‎ጥንዶች ስልጠና መውሰድ የሚችሉበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የጀመርነውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን " ያለው ሚኒስቴሩ " ከስልጠና በተጨማሪ ትዳር እንዳይናጋና ቤተሠብም እንዳይበተን ቤተሠብ ተኮር የምክር አገልግሎቶችን ለማስፋፋት እና ለማጠናከርም በትኩረት እየሰራን እንገኛለን " ብሏል።

በትላንትናው ዕለት ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የፍቺ ቁጥር ለመቀነስ ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር የቅድመ ጋብቻ ስልጠና ሰርተፊኬት ሳይዝ ማንም ሰው ወደ ጋብቻ እንዳይገባ የሚያደርግ አሰራር ሊጀምር መሆኑን በሚኒስቴር መ/ቤቱ የአረጋውያንና ቤተሰብ ጉዳዮች ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተስፋዬ ሮብሌን ዋቢን ቃል ዋቢ በማድረግ ዘግቦ ነበር።

‘ተጣብቀው የተወለዱ መንትዮች’ በሚል በርካቶችን ያሳሳቱት ሐሰተኛ የኤአይ ቅንብሮች *******በቅርብ ጊዜ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ‘ቫለሪያ’ እና ‘ካሚላ’ በሚል ስም የሚጠሩ መንትዮች...
06/02/2026

‘ተጣብቀው የተወለዱ መንትዮች’ በሚል በርካቶችን ያሳሳቱት ሐሰተኛ የኤአይ ቅንብሮች
*******

በቅርብ ጊዜ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ‘ቫለሪያ’ እና ‘ካሚላ’ በሚል ስም የሚጠሩ መንትዮች ታሪክ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።

መንትዮቹ በአካል ተጣብቀው የተወለዱ (Conjoined twins) መሆናቸውንና በአሜሪካ ማያሚ እንደሚኖሩ በማኅበራዊ የትስስር ገፅ ቢገልጹም፣ የተደረገው ማጣራት ግን ጉዳዩ ከእውነት የራቀ መሆኑን አረጋግጧል።

ተጣብቀው የተወለዱ መንትዮችን በመምሰል በተከፈተው በዚህ ገጽ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከ100 ሺህ በላይ ተከታዮችን ማፍራት የተቻለ ሲሆን፣ ምስሎቹም እጅግ እውነተኛ ይመስሉ እንደነበር በርካታ መገናኛ ብዙኃንም ዘግበዋል።

ሆኖም የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ምስሎቹን መርምረው እንደገለጹት፤ እነዚህ መንትዮች በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) የተፈጠሩ የምስል ቅንብሮች እንጂ እውነተኛ ሰዎች አይደሉም።

በምስሎቹ ላይ የሚታዩ አንዳንድ ጥቃቅን የቴክኒክ ስህተቶች፣ በተለይም የጣቶች ቁጥር መብዛትና የጀርባ ገጽታዎች መዛባት ምስሎቹ በቴክኖሎጂ የተቀነባበሩ መሆናቸውን ያረጋግጣሉ።

መንትዮቹ በማኅበራዊ የትስስር ገፅ ላይ "እውነተኛ ሰዎች ነን" የሚል ክርክር ቢያቀርቡም፣ የዲጂታል ምርመራ ውጤቶች ግን ምስሎቹ ‘ዲፕ ፌክ’ (Deepfake) መሆናቸውን አሳይተዋል።

ጉዳዩን የታዘቡ ብዙዎች የሰዎችን አካል ጉዳት ለንግድ ማስታወቂያነትና ለተከታይ ማፍሪያነት መጠቀም ተገቢ አለመሆኑን በመጥቀስ ድርጊቱን እየተቹት ይገኛሉ።

ይህ ክስተት የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ እውነትንና ሐሰትን መለየት እስከሚያቅተን ድረስ እየረቀቀ መምጣቱን የሚያሳይና ማኅበረሰቡ በማኅበራዊ ገጾች የሚመለከታቸውን መረጃዎች በጥንቃቄ መመርመር እንዳለበት ትልቅ ትምህርት የሰጠ ሆኗል።

በሜሮን ንብረት

Meseret Media የተሳሳተ ዘገባ በማሰራጨት ላይ ነውየሙሐመድ ጋዳፊ ልጅ ነው። በኤአይ መረጃ መሠረት ከኾነ ከጋዳፊ ጋር ዝምድና የለውም። እውነታው ግን የጋዳፊ ልጅ ነው። በጋዳፊ የመጨረ...
14/12/2025

Meseret Media የተሳሳተ ዘገባ በማሰራጨት ላይ ነው

የሙሐመድ ጋዳፊ ልጅ ነው። በኤአይ መረጃ መሠረት ከኾነ ከጋዳፊ ጋር ዝምድና የለውም። እውነታው ግን የጋዳፊ ልጅ ነው። በጋዳፊ የመጨረሻ ዘመን እንደተባለውም ቃል አቀባይ ነበር። በጦርነቱ ወቅት ከኹለት ጊዜ በላይ መገደሉም ተነግሮ ነበር። አሁን ነዋሪነቱ ደቡብ አፍሪካ ነው። የአፍሪካ ሌጋሲ ዋና ጸሐፊ ነው።

የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ሶሻል ሚዲያ ላይ የተሰራጨው ሀሰተኛ መረጃን አስመልክተው ያስተላለፉት መልዕክት++++++++++++++++++++++++++++++++...
14/12/2025

የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ሶሻል ሚዲያ ላይ የተሰራጨው ሀሰተኛ መረጃን አስመልክተው ያስተላለፉት መልዕክት
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሰፊ የሪፎርም ማዕቀፍ ነድፎ በመተግበር ላይ ነው። ይህም ሰባት ዋና፣ ዋና አምዶች ያሉት ነው። አምዶቹም፦
1. የኢንዱስትሪ፣ ሙያ ምድብ እና ክፍያና ጥቅማ ጥቅም ማሻሻል
2. የሙያ ብቃት ግንባታ
3. የአገልግሎት ማላቅ
4. ዘመናዊ የሰው ኃይል አመራር
5. የብዝሃነትና አካታችነት ማረጋገጥ
6. ዲጂታላይዜሽ ማስፋፋት እና
7. የአመራር አቅም መገንባት ናቸው።
እነዚህ ሥራዎችን ለማስተግበር ፈጻሚ እና ባለቤት ተቋማት በዌቮች (Wave I, Wave II & Wave III) ተከፋፍለው ወደ ትግበራ የተገባ ሲሆን አፈጻጸሙም ተስፋ ሰጪ ነው።

ከሰባቱ የሪፎርም አምዶች አንዱ የአገልግሎት አቅርቦት ሂደቱን ማላቅ ነው። በተደረገው የአፈጻጸም እንቅስቃሴ ተጨባጭ እና በኢትዮጵያ የመንግስት አገልግሎት ማሻሻል ብቻ ሣይሆን ማላቅም እንደሚቻል በተግባር ታይቷል። የፌዴራሉን ጨምሮ እሰከ እዚህ ወር ባለው ጊዜ 21 የመሶብ (MESOB:-Modern Ethiopia Services for Organized Benefits) ተገንብተው በሥራ ላይ ናቸው።

በየማዕከላቱ የሚሰጡ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ የሆኑ አገልግሎቶች ብቻ ናቸው። የICT እውቀት የሌላቸውን ዜጎች የሚታገዙበት ሥርዓት እንዲኖረው ተደርጎ የተነደፈም ነው። በአሁኑ ሰዓት ይህንኑ ወደ ሁሉም የኢትዮጵያ ከተሞች ለማስፋፋት በመረባረብ ላይ እንገኛለን። ይህንን ሥራ የሚመራ እና በአፍሪካ ተምሣሌታዊ ተግባር እና ቁመና ያለው አደረጃጀት እና ሥርዓት ለመፍጠርም ጥረት እየተደረገ ነው።

ከእነዚህ ተግባራት አንዱ የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ግንባታ ማካሄድ ነው። የግንባታ የጨረታ ሰነድ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሳይሆን በኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (EEC) ተዘጋጅቶ እና በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ጸድቆ በ egp.mofed.gov.et አለም አቀፍ ጨረታው ወጥቷል። ለእዚህም ዲዛይን እና ግንባታ ግልጽ ጨረታ ውድድር የዓለም አቀፍ እና የኢትዮጵያ ተቋራጮች እየተሳተፉ ነው። በጨረታው ሂደት ማን እንደሚያሸንፍ የሚታወቅ ነገር የለም። ተወዳዳሪዎቹ ለመገምገም ከኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (EEC)፣ ከከተማ ልማትና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እና ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የተውጣጡ ባለሙያዎች ተደራጅቶ በሥራ ላይ ናቸው። አሸናፊው ከሂደቱ ይለያል ተብሎ ይጠበቃል።

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ሂደቱን የሚያደናቅፍ እና መሠረት የሌለው እና የተዛባ መረጃ በአንድ የማህበራዊ ሚዲያ ተሰራጭቷል። ትክክለኛ መረጃው ከላይ የገለጸው ስለሆነ ለእራሱ ታዕማኒነት ሲል ማህበራዊ ሚዲያው የተዛባውን መረጃ እንዲስተካከል እመክራለሁ።
ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር

ራሳችሁን በሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ውስጥ ብታገኙትስ?የኬንያ የወንጀል ምርመራ ዳይሬክቶሬት፣ ዜጎችን በሞስኮ ሥራ እናስቀጥራችኋለን በሚል ማማለያ፣  በሩሲያ የጦር ግንባር ውስጥ የሚዶል  ህገወ...
26/09/2025

ራሳችሁን በሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ውስጥ ብታገኙትስ?

የኬንያ የወንጀል ምርመራ ዳይሬክቶሬት፣ ዜጎችን በሞስኮ ሥራ እናስቀጥራችኋለን በሚል ማማለያ፣ በሩሲያ የጦር ግንባር ውስጥ የሚዶል ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ ሰንሰለትን ማፈራረሱን አስታወቀ፡፡

ቡድኑ፤ በከፍተኛ ደሞዝ ሥራ እናስቀጥራችኋለን በሚል ሃሰተኛ ተስፋ በማጭበርበር፣ ለቪዛ፣ ለጉዞና ለማረፊያ ከ12ሺ እስከ 17ሺ ዶላር የሚደርስ ክፍያ እንደሚያስከፍል ታውቋል፡፡

መርማሪ ፖሊሶች ባደረጉት የክትትል ዘመቻ 21 ኬንያውያንን መታደጋቸው የተዘገበ ሲሆን፤ የድርጊቱ አስተባባሪ ነው የተባለ አንድ ተጠርጣሪም በቁጥጥር ስር መዋሉ ተጠቁሟል፡፡

መርማሪዎቹ የጉዞ ሰነዶችን፣ የሥራ ቅጥር ደብዳቤዎችንና ከሩሲያ ሁለት የቅጥር ኩባንያዎች ጋር የተገናኙ ውሎችን ማግኘት መቻላቸው ተዘግቧል፡፡

የወንጀል ምርመራ ዳይሬክቶሬት ባለሥልጣናቱ፣ በኬንያ ያሉ ገንዘብና ሥልጣን ያላቸው ግለሰቦች፣ ለቡድኑ ከለላ ሰጥተውት ቆይተው ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን ገልጸዋል፡፡

የእንደዚህ ዓይነቱ የወንጀል ድርጊት ሰለባ ከነበሩት መካከል ኢቫንስ የተባለው ኬንያዊ ተጠቃሽ ሲሆን፤ በዩክሬን የጦር ምርኮኛ መሆኑን የሚገልጽ ቪዲዮ ላይ ከታየ በኋላ ታሪኩ በሰፊው ተሰራጭቷል። ለአትሌቲክስ ውድድር ነው ተብሎ ወደ ሩሲያ መጓዙን የሚገልጸው ኬንያዊው፤ በዩክሬን ሰራዊት ከመያዙ በፊት ለሩሲያ ጦር እንዲዋጋ መገደዱን ተናግሯል።

***

ወገኖቼ፤ ከዚህ ዘገባ የምንማረው ትልቅ ቁምነገር አለ፡፡ ይሄ ነገር በጎረቤት ኬንያ ከተከሰተ በኛም አገር የማይከሰትበት ወይም የማይሞከርበት ምክንያት የለምና ጥንቃቄ ማድረግ መልካም ነው፡፡ እስካሁን ላለመደረጉም በእርግጠኝነት መናገር አይቻልም፡፡ ህጋዊና ህጋዊነትን ብቻ እንምረጥ ለማለት ነው፡፡

ሳይታገት ታግቻለሁ በማለት የትዳር አጋሩን ሦስት ሚሊዮን ብር የጠየቀን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገለፀ።***ወንጀሉ የተፈፀመው ...
19/09/2025

ሳይታገት ታግቻለሁ በማለት የትዳር አጋሩን ሦስት ሚሊዮን ብር የጠየቀን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገለፀ።
***
ወንጀሉ የተፈፀመው ነሐሴ 27 ቀን 2017 ዓ/ም በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው ኮተቤ እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ ነው።

ዶክተር አበባው በላይነህ የተባለው ይህ ግለሰብ ከሚሰራበት ኮተቤ ጤና ጣቢያ አካባቢ ባልታወቁ ሰዎች ታግቶ የተወሠደ በማስመሰልና በገዛ ስልኩ አጋቾች እንደጻፉ በማስመሠል ለትዳር አጋሩ "ሦስት ሚሊዮን ብር እንዲያመጡ ይህን ካላደረጉ በህይወት እንደማይገኝ የሚገልጽ የጽሁፍ መልዕክት ይልካል፤ ቤተሠብም በወቅቱ በመደናገጥ ጉዳዩን ለፖሊስ አመልክተዋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የተደራጁና የልዩ ልዩ ወንጀሎች ምርመራ መምሪያ የደረሰውን አቤቱታ መነሻ በማድረግ ጥቆማው ከደረሰው ሠአት ጀምሮ የምርመራ ክፍሉና የክትትልና ኦፕሬሽን ቡድኑ በመቀናጀት ተገቢውን የክትትል ስራ በመስራት ታግቻለው ያለው ግለሰብ ደብረ ብርሀን ከተማ ከአንድ ሆቴል ውስጥ እንዳለ ይደርሱበታል።

በሆቴሉ ደርሰው ሲያጣሩም ግለሰቡ ለሦስት ቀናት ቆይቶ መሄዱን መረጃ ያገኛሉ። ፖሊስ ለምርመራው እንዲረዳም የባንክ እንቅስቃሴውን እየተከታተለ መሆኑን የተረዳው ተጠርጣሪ ጳግሜ 1 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 10 ሠአት ገደማ አጋቾቹ ብሩ ሊላክላቸው ባለመቻሉ ለቀውኛል በሚል ከሦስት ቀናት ቆይታ በኋላ ወደ መኖሪያ ቤቱም ተመልሷል። ፖሊስም ግለሰቡ ወደ ቤተሠቡ መመለሱን በደረሠው መረጃ በቁጥጥር ስር ሊያውለው መቻሉን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።

ፖሊስም ግለሰቡ ላይ ባደረገው ምርመራ የማስፋትና ስራ ታገትኩ ያለው ግለሰብ ምንም ዓይነት የእገታ ወንጀል ያልተፈፀመበት መሆኑን እና ገንዘቡን የጠየቀውም እራሱ መሆኑን፣ ለሦስት ቀናት ሆቴል አልጋ ይዞ እንደቆየም ጭምር በተደረገው ምርመራ ሊደረስበትም ችሏል።

አንዳንድ ግለሰቦች ያልተገባን ጥቅም ለማግኘት በማሰብ ያልተፈጸመባቸውን ወንጀል ተፈጽሞብኛል በማለት በሌሎች ሰዎች ላይ ፍርሀትን ከመንዛትም ባለፈ የሚፈፅሙት ድርጊት ከህግ ተጠያቂነት እንደማያድናቸው ሊገነዘቡ ይገባል ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን ያስተላልፋል፡፡
*
ዘገባ፡- ኢንስፔክተር እመቤት ሀብታሙ

 አቶ ጌታቸው ረዳ የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ሆነው አልተሾሙም። ተሹመዋል እየተባለ በማህበራዊ ሚድያ የሚታየው ዜና ምንጩ ያልታወቀ ውሸት ነው።
03/09/2025


አቶ ጌታቸው ረዳ የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ሆነው አልተሾሙም። ተሹመዋል እየተባለ በማህበራዊ ሚድያ የሚታየው ዜና ምንጩ ያልታወቀ ውሸት ነው።

Address

Addis Abeba
Addis Ababa
NOTYET

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አጋልጥ - Expose posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to አጋልጥ - Expose:

Share