06/04/2026
ብሔራዊ ባንክ በሕገ-ወጥ የገንዘብ አስተላላፊዎች ላይ የሰጠው ማስጠንቀቂያ
++++++++++++++
- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፤ 23 የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች ያለባንኩ እውቅና እና ፈቃድ እየሰሩ መሆኑን ገልጿል።
እነዚህ ተቋማት ከመጀመሪያው ፈቃድ የሌላቸው ወይም ቀደም ሲል የነበራቸው ፈቃድ በሕገ-ወጥ ተግባራት ምክንያት የተሰረዘ መሆኑን ባንኩ አረጋግጧል።
ኅብረተሰቡ የገንዘብ ደህንነቱን ለመጠበቅና በሕገ-ወጥ ተግባራት ውስጥ እንዳይሳተፍ በእነዚህ ድርጅቶች በኩል ገንዘብ ከመላክ እንዲቆጠብ ባንኩ አሳስቧል። በኢትዮጵያ ውስጥ የገንዘብ ዝውውር አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ሕጋዊ የሥራ ፈቃድ የሌላቸው ናቸውም ብሏል።
እነዚህም ድርጅቶች አዱሊስ መኒ ትራንስፈር፤ አማና ኤክስፕረስ፤ አዋሽ ዳይሬክት፤ ባካኣል መኒ ትራንስፈር፤ ሆልደን ግሎባል፤ ኦሊምፒክ ፋይናንሻል ግሩፕ ፤ ታአጅ መኒ ትራንስፈር፤ ዋይዝ ትሬዲንግ መኒ ትራንስፈር፤ ወርልድ ዳይሬክት ሊንክ እና ሌሎችም እንደሚገኙበት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል፡፡
ማንኛውም የውጭ ሀገር የገንዘብ ዝውውር በሕጋዊ የባንኮችና እውቅና ባላቸው የገንዘብ አስተላላፊ ወኪሎች በኩል ብቻ መከናወን እንዳለበት ተገልጿል።
በሀና እጅጋየው
#ጥንቃቄ