Harot Ethiopia

Harot Ethiopia ሐሮት ኢትዮጵያ ነፃና ገለልተኛ የመረጃ ምንጭ ያወቅነውና የሰማነው የምናሳውቅበት

22/05/2026
https://youtu.be/E2RJTmiDDe4?si=IzomT-hSIFLbDtsd
22/05/2026

https://youtu.be/E2RJTmiDDe4?si=IzomT-hSIFLbDtsd

ሞት የሰው ልጅ እጣ ፈንታ ቢሆንም፣ አሟሟት ግን እንደየሰው ይለያያል። የ30 ዓመቱ ወጣት ኪሩቤል ከበደ አሟሟት ግን የጭካኔን ጥግ የሚያሳይ፣ አዲስ አበባን በእንባ ያጠበ እና ሰሚን ሁሉ በ....

የአውሮጳ እግር ኳስ ማሕበር በእንግሊዘኛ ምህጻሩ (UEFA) በብራዚላዊ የሪያል ማድሪድ ኮከብ ቪኒሺየስ ጁንየር ላይ ደረሰ የተባለውን የዘረኝነት ጥቃት ሊመረምር ነው። ማሕበሩ ዛሬ  ባወጣው መ...
18/02/2026

የአውሮጳ እግር ኳስ ማሕበር በእንግሊዘኛ ምህጻሩ (UEFA) በብራዚላዊ የሪያል ማድሪድ ኮከብ ቪኒሺየስ ጁንየር ላይ ደረሰ የተባለውን የዘረኝነት ጥቃት ሊመረምር ነው።

ማሕበሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፥ የሪያል ማድሪዱ አጥቂ ቪኒሺየስ ጁኒየር የቤንፊካው ጂያንሉካ ፕሪስቲያኒ ትናንት ማክሰኞ ምሽት ሊዝበን በተካሄደው የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ ላይ «የዘረኝነት ስድብ ሰድቦኛል» በማለት ላቀረበው ክስ «አድሎአዊ ባህሪን» በተመለከተ ምርመራ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

ምሽቱን በተደረገው የጥሎ ማለፍ ማጣሪያ የመጀመሪያ ዙር ግጥሚያ ቪኒሺየስ ከቤነፊካዊ ተጫዋች ፕሪስቲያኒ ጋር ግጭት ውስጥ ከገባ በኋላ ለፈረንሳዊው ዳኛ ፍራንሷ ሌቴክሲየር አቤቱታ ማቅረቡን ተከትሎ ጨዋታው ከ10 ደቂቃ በላይ ተቋርጦ ነበር።

በተቻዋቾቹ መሃል ግጭቱ የተፈጠረው ቪኒሺየስ ሪያል ማድሪድን 1 ለ 0 አሸናፊ ያደረገችውን ብቸኛ ግብ ካስቆጠረ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ነው።

ቪኒሺየስ ግቡን ካስቆጠረ በኋላ በቤንፊካ ደጋፊዎች ፊት «ወጣ ባለ ጭፈራ» ደስታዉን በመግለጹ የቢጫ ካርድ ተመልክቷል።

ቪኒሺየስ ከፕሪስቲያኒ የስድብ ድምጽ ከሰማ በኋላ ወደ ዳኛው በመሮጥ በስፓኒሽ ቋንቋ «ሞኖ» (ዝንጀሮ) የሚል ስድብ እንደሰደበው አመልክቷል።

የ20 ዓመቱ አርጀንቲናዊ ኢንተርናሽናል የአማካይ ስፍራ ተጫዋች ፕሪስቲያኒ ለቪኒሺየስ የሆነ ነገር ሲናገር አፉን በልብሱ ሸፍኖ የነበረ ሲሆን የዘረኝነት ስድብ መሳደቡን ግን አስተባብሏል።

የሪያል ማድሪዱ እንግሊዛዊ ተከላካይ ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ ድርጊቱ ምሽቱን እንዳበላሸባቸው ገልጿል።

ድርጊቱን «አስጸያፊ» ሲል የገለጸው ተጫዋቹ «የሆነው ነገር ለእግር ኳስ ትልቅ ውርደት ነው» ብሏል።

የማድሪዱ አጥቂ ኪሊያን ምባፔ በበኩሉ ፕሪስቲያኒ ከጨዋታ እንዲታገድ ጥሪ አቅርቧል።

«በአውሮጳ ምርጥ ውድድር ላይ እየተጫወተ እንዲህ ያለ ባህሪ የሚያሳይ ተጫዋችን አንቀበልም» ብሏል።

ምባፔ አክሎም «ይህ ሰው ዳግመኛ በሻምፒዮንስ ሊግ የመጫወት መብት ሊኖረው አይገባም» ሲል ብርቱ ተቃዉሞውን አሰምቷል።

የቤንፊካው አሰልጣኝ ሆሴ ሞሪንሆ ግን ቪኒሺየስ ግቧን ካስቆጠረ በኋላ ደስታውን የገለጸበት መንገድ ደጋፊዎችን እና ተጫዋቾችን ለቁጣ አነሳስቷል በሚል ተችተውታል።

«ኪክ ኢት አውት» የተባለው የእንግሊዝ የእግር ኳስ ጸረ-መድሎ ተቋም የሞሪንሆን ምላሽ በመተቸት አሰልጣኙን «እውነታውን በማድበስበስ» ከስሷቸዋል።

ተቋሙ በመግለጫው «ማንኛውም ሰው በእግር ኳስም ሆነ በየትኛውም ቦታ መድልዎ ሲደርስበት ካመለከተ የመጀመሪያው ቅድሚያ የሚሰጠው ነገር ተጎጂውን ማዳመጥና ድጋፍ መስጠት ነው» ብሏል።

የክስተቱን ትኩረት «ቪኒሺየስ ደስታውን ወደ ገለጸበት ወይም ወደ ክለቡ በማዞር የቀረበውን አቤቱታ ችላ ማለት እውነታውን የማድበስበስ ተግባር ነው» ሲል እየተባባሰ የመጣውን የዘረኝነት ጥቃት አውግዟል።

አድዋ ሙዚየም እንግዳዋን ለመቀበል ተዘጋጅታለችረሲብ ጣኢብ ኤርዶጋን አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን ከደቂቃዎች በኋላ በአድዋ ሙዚየም የአበባ ጉንጉን የሚያኖሩ ይሆናል።በዚህ ሰአት የማርሽ ባንድ የተ...
17/02/2026

አድዋ ሙዚየም እንግዳዋን ለመቀበል ተዘጋጅታለች

ረሲብ ጣኢብ ኤርዶጋን አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን ከደቂቃዎች በኋላ በአድዋ ሙዚየም የአበባ ጉንጉን የሚያኖሩ ይሆናል።

በዚህ ሰአት የማርሽ ባንድ የተለያዩ ሙዚቃዎችን እያስደመጠን ይገኛል።

የቆሰለ ንጉስ አደገኛ ነውጆዜ ሞሪኖ ከ ማድሪድ ጋር ስላላቸው ጨዋታ 🗣" ማድሪዶችን ያደረግናቸውን እናቃለን፣ እነሱ የሻምፕዮንስ ሊግ ንጉስ ናቸው።የቆሰለ ንጉስ ደግሞ አደገኛ ነው "
17/02/2026

የቆሰለ ንጉስ አደገኛ ነው

ጆዜ ሞሪኖ ከ ማድሪድ ጋር ስላላቸው ጨዋታ 🗣

" ማድሪዶችን ያደረግናቸውን እናቃለን፣ እነሱ የሻምፕዮንስ ሊግ ንጉስ ናቸው።

የቆሰለ ንጉስ ደግሞ አደገኛ ነው "

መሐመድ ቢን ዛይድ ተመርዘዋል?የተባበሩት አረብ ኢመሬቶች መሪ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናሃያን በፅኑ ታመው ሆስፒታል መግባታቸው ታውቋል:: ሆርን ፍሪኩዌንሲ ከአቡዳቢ የመረጃ ምንጮች አገኘሁት ...
17/02/2026

መሐመድ ቢን ዛይድ ተመርዘዋል?

የተባበሩት አረብ ኢመሬቶች መሪ መሐመድ ቢን ዛይድ አል ናሃያን በፅኑ ታመው ሆስፒታል መግባታቸው ታውቋል::

ሆርን ፍሪኩዌንሲ ከአቡዳቢ የመረጃ ምንጮች አገኘሁት ባለው መረጃ ቢን ዛይድ ሳይመረዙ እንዳልቀሩ ለማወቅ ተችሏል ብሏል።

የቱርኩ መሪ ረሲብ ጣይብ ኤርዶጋን በአቡ ዳቢ ሊያደርጉት የነበረው ጉብኝት በቢን ዛይድ መታመም ምክንያት መሰረዙን የአገሪቱ ሚዲያዎች እየዘገቡት ሲሆን በርካታ ሚዲያዎች ደግሞ ሞተዋል ሲሉ እየዘገቡ ይገኛሉ::

በጉዳዩ ዙሪያ ከአቡዳቢ የተሰጠ መግለጫ የለም::

የአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ የመታሰቢያ መርሐ-ግብር የጊዜ ለውጥ ማሳሰቢያ​የካቲት 10 ቀን 2018 ዓ.ም. ተወዳጁ የጨዋታ ሰው አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ በሕይወት ቢኖር ኖሮ የ44ኛ ዓመት ...
17/02/2026

የአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ የመታሰቢያ መርሐ-ግብር የጊዜ ለውጥ ማሳሰቢያ

​የካቲት 10 ቀን 2018 ዓ.ም. ተወዳጁ የጨዋታ ሰው አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ በሕይወት ቢኖር ኖሮ የ44ኛ ዓመት የልደት ቀኑን ያከብር ነበር።

​ቤተሰቦቹ እና ወዳጅ ዘመዶቹ ይህንን ዕለት በልዩ መታሰቢያ ዝግጅት ለማክበር ዝግጅታቸውን አጠናቀው የነበረ ቢሆንም፣ የአርቲስት ነፃነት የቅርብ የሥራ ባልደረባና ወዳጅ የነበሩት የኢቢኤስ (EBS) ቲቪ መስራች የአቶ አማን ፍስሃጽዮን ድንገተኛ ሕልፈት በመስማታቸው ዝግጅቱ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ተወስኗል።

​📍 ምክንያት፦
የአቶ አማን ፍስሃጽዮን ድንገተኛ ሕልፈትና ቤተሰቡ ካለበት ጥልቅ ሐዘን የተነሳ።

​📍 ቀጣይ ዝግጅት፦
መርሐ-ግብሩ የሚካሄድበት ቀን ወደፊት በይፋ የሚገለጽ ሲሆን፣ በዕለቱም በነፃነት ወርቅነህ ስም የሚገነባ የመታሰቢያ ተቋም ይፋ ይደረጋል።

​በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ቤተሰብ ስም ለአቶ አማን ፍስሃጽዮን ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶችና ለሥራ ባልደረቦቻቸው በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።

ሻብያ የኢትዮጵያን ባንዲራ ረገጠ!በጸረ ኢትዮጵያ አቋሙ የሚታወቀው ሻብያ፤ ኢትዮጵያ ጠልነቱን ዳግም ያሳየበትን ድርጊት ፈጽሟል።ከሰሞኑ የፈንቅል ኦፕሬሽን መታሰቢያ በምጽዋ እየተከበረ እንዳለ ...
17/02/2026

ሻብያ የኢትዮጵያን ባንዲራ ረገጠ!

በጸረ ኢትዮጵያ አቋሙ የሚታወቀው ሻብያ፤ ኢትዮጵያ ጠልነቱን ዳግም ያሳየበትን ድርጊት ፈጽሟል።

ከሰሞኑ የፈንቅል ኦፕሬሽን መታሰቢያ በምጽዋ እየተከበረ እንዳለ ይታወቃል።

በአሉን አስመልክቶ ከተዘጋጁ ዝግጅቶች አንዱ በሆነው የስእል አውደርእይ ላይ የታየው ክስተት አነጋጋሪ ሆኗል።

በአውደ ርእዩ ላይ ከቀረቡ ስእሎች አንዱ የኢትዮጵያን ክብር እና እሴት የሚነካ ነው።

በስእሉ ላይ እንደሚታየው አንድ ከስክስ ጫማ ያደረገ ወጣት የኢትዮጵያን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ ረግጦ ይታያል።

በተጨማሪም በስእሉ ላይ የሚታየው ወጣት፣ የአጼ ኃይለስላሴ፣ መንግስቱ ኃይለማርያም እና የአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድን ምስል ሲረግጥ ይታያል።

ይህ በሻብያ ድሕረገጽ ላይ የተለቀቀው የስእሉ ፎቶግራፍ እያነጋገረ ሲሆን፤ የሻብያን ኢትዮጵያ ጠልነት ከሚያሳዩ ድርጊቶች እንደ አንዱ ሆኖ ተመዝግቧል።

ለዚህ የሻብያ አገዛዝ ድርጊት ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ምላሽ አልተሰጠም።

በተለያዪ የቲያትር መድረኮች እና በበርካታ ፊልሞች ላይ ባሳየው የትወና ጥበቡ እንዲሁም በቴሌቪዥን የመዝናኛ ፕሮግራሙ በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትንና አድናቆትን ባተረፈው በተወዳጁ የኪነጥ...
16/01/2026

በተለያዪ የቲያትር መድረኮች እና በበርካታ ፊልሞች ላይ ባሳየው የትወና ጥበቡ እንዲሁም በቴሌቪዥን የመዝናኛ ፕሮግራሙ በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትንና አድናቆትን ባተረፈው በተወዳጁ የኪነጥበብ ሰው አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ህልፋተ ህይወት የተሰማኝን ጥልቅ ሐዘን ለመግለፅ እወዳለሁ። በዛሬው ዕለትም በተሰማው ህልፈተ ህይወቱ በደረሰው ሀዘን ለቤተሰቦቹ ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለመላዉ አድናቂዎቹ መጽናናትን እየተመኘዉ ፋጣሪ ነፍሱን በአጸደ ገነት እንዲያኖርልን ከልብ እመኛለው።

ነፍስ ይማር!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ፍቅር ያሸንፋል!
ቴዎድሮስ ካሳሁን
(ቴዲ አፍሮ)

Address

Piassa
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harot Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share