29/09/2025
የግሎባል ሱሙድ ፍሎቲላ ቅሌት
በዋናነት በአለም አቀፍ የአከባቢ መብት ተቆርቋሪነት፤ እንዲሁም በኋላ ላይም በሰብአዊ መብት ተቆርቀሪነት በምትታወቀዉ ሲዉዲናዊቷ “ግሬታ ዙንበርግ” የፊት አዉራሪነት እየተመራ በጋዛ ላይ የተጣለዉን የባህር ላይ ከበባን ለመስበር በማሰብ በስሩ ከ55 በላይ ጀልባዎችን እና ከ44 የዓለማችን አገራት የተዉጣጡ በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር፡ “ግሎባል ሱሙድ ፍሎቲላ”/Global Sumud Flotilla/ በሚል ስያሜ እ.ኤ አ. ነሐሴ 31, 2025 ከስፔና የባርሴሎና ወደብ የተነሳዉ ቡድን በዉስጡ የደቡብ አፍሪካዉ ተወዳጅ መሪ የነበሩት የኔልሰን ማንዴላ የልጅ ልጅ “ማንድላ ማንዴላ” እና የፈረንሳይዋን ታዋቂ ተዋናይት “አዴሌ ሀኤኔል” እና ሌሎች ብዙ ተጽዕኖ ፈጣሪዎችን በዉስጡ ያቀፈ ነዉ፡፡
ዛሬ ሰኞ መስከረም 29, 2025 ጉዞ ከጀመሩ 29ነኛ ቀናቸዉን የያዙ ሲሆን ምናልባትም ነገ ወደ ጋዛ ሰርጥ የዉሃ ክልል ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ መላዉ አለምም እስራኤል ምን አይነት ምላሽ ልትሰጥ ትችላለች በሚል ስጋት ጉዳዩን በአይነቁራኛ እየተከታተለ ይገኛል፡፡
ታዲያ ይህ ብዙ የተባለለት የተጓዦች ቡድን መንገድ ላይ ከእስራኤል በኩል እየገጠመን ነዉ ካሉት የድሮን ቅኝት፣ ቦንብ እና የኬሚካል ጥቃት ተግዳሮቶች ባለፈ ትልቅ ቅሌት ገጥሞታል፡፡
ይህ በዋናነት “በሰብዓዊነት ተልዕኮ ስም” የተሰባሰበዉ ቡድን በዋናነት በአራት ክፍሎች የተቧደነ ነዉ፡፡ የመጀመሪያዎቹ ልክ እንደስማቸዉ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪዎች ሲሆኑ፤ ሁለተኛዉ ቡድን ደግሞ አፍቃሪ ሀማስ ናቸዉ፡፡ በሶስተኛዉ ቡድን ዉስጥ የሚካተቱት ደግሞ አክራሪ እስልምናን የሚያቀነቅኑ ሲሆኑ በአራተኛዉ ጎራ ዉስጥ እራሳቸዉን የሚከቱ ደግሞ ለግብረሰዶማዉያን መብት እንታገላለን የሚሉ ናቸዉ፡፡
ግብረሰዶማዊነትን አጥብቀዉ በሚቃወሙ አክራሪ እስላማዊ ቡድኖች እና ዘግየት ብሎ ከቱኒዚያ ወደብ ቡድኑን በተቀላቀለዉ እራሱን “የኮሚኒስት ፍናፍንቶች ተዋጊ”/Communist q***r fighter/ በማለት በሚጠራዉ በቱኒዚያዊዉ ሰይፍ አያዲ መካከል በተፈጠረዉ አተካራ የተነሳ በተጓዦቹ መካከል መቃቃርን ፈጥሯል፡፡
በዚህም ሳያበቃ ግንባር ቀደም የጉዞ አስተባባሪዎች ከሆኑት መካከል አንዱ የሆነዉ፤ ካሊድ ቦኡቼማ ሲናገር “የልዑካኑ ዋና መርሕ የነበረዉ ለፍልስጤማዉያን ድምጽ ለመሆን ታስቦ የተጀመረዉ ዘመቻ የተለየ ፍላጎት ባላቸዉ አካላት ተጠልፋል” በማለት ጉዞዉን አቋርጦ ወጥቷል፡፡
ካሊድ ቦኡቼማን ተከትለዉ ብዙኋኑ “በተራማጅ የባህል አጀንዳ አራማጆች”/Culturally Progressive Agenda/ አላማችን ተጠልፏል በማለት በተለያየ ጎራ ተቧድነዋል፡፡
ይህንን ቅሌት ተከትሎ ሲዉዲናዊቷ አክቲቪስት ግሬታ ዙንበርግ ከዋና አስተባባሪ የማኔጅመንት ቡድን ዉስጥ ተወግዳ፤ በጉዞ ዉስጥ እንደ ተራ በጎ ፈቃደኛ ግለሰብ ብቻ እየተሳተፈች እንደምትገኝ ተገልጿል፡፡
በነገራችን ላይ የፍልስጤማዉያንን መብት እና የሁለት አገርነት መፍትሄን በመደገፍ በምዕራቡ አለም በሚደረጉ የተቃዉሞና የድጋፍ ሰልፎች ላይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ፤ የሰብዓዊ መብት አቀንቃኞች፣ የግራ ዘመም ፖለቲካ ደጋፊዎች እና የግብረሰዶማዊያን መብት ተማጋቾችን በጥምረት መመልከት የተለምደ ትዕይንት ሆኗል፡፡
እንዴት በእነዚህ 3ት ኃይሎች መካከል ጥምረት ሊፈጠር ቻለ? በመካከላቸዉ የሚያዛምዳቸዉ አንዳች የጋራ አጀንዳ ይኖር ይሆን? የሚለዉ እንቆቅልሽ፤ እስካሁን ድረስ በመላዉ አለም በሚገኙ ህዝቦች ያልተፈታ ሚስጥር ሆኗል፡፡
እናንተስ ይህንን ጉዳይ ልብ ብላችኋል? በጉዳዩ ላይ ያላችሁስ መረዳትና ምልከታ ምንድነዉ?
ሰላም ሰንብቱ!
ይህ በዋናነት “በሰብዓዊነት ተልዕኮ ስም” የተሰባሰበዉ ቡድን በዋናነት በአራት ክፍሎች የተቧደነ ነዉ፡፡ የመጀመሪያዎቹ ልክ እንደስማቸዉ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪዎች ሲሆኑ፤ ሁለተ.....