KF2B Gamo

KF2B Gamo Struggle for truth

28/04/2026
27/04/2026
27/04/2026
ጉዞ ወደ ብልጽግና ነዶ በነዶ
27/04/2026

ጉዞ ወደ ብልጽግና
ነዶ በነዶ

23/04/2026

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እንኳን ደስ አለዎት!

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው በመሾምዎ በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም እንኳን ደስ አለን ለማለት እወዳለሁ።

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን የጥረታቸው ፍሬ በአፍሪካ ደረጃ እውቅና አግኝቶ ለዚህ ሹመት መብቃታቸው ለኢትዮጵያን ሁሉ ኩራት ነው ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስቷ ከተማ
23/04/2026

አዲስቷ ከተማ

22/04/2026
21/04/2026

በአዲሱ የወንጀል ሥነ ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ የተካተቱ ዋና ዋና ነጥቦች ...

ሚያዚያ 12/2018 ዓ.ም

በአዲሱ የወንጀል ሥነ ሥርዓት እና የማስረጃ ሕግ ዘመኑን የዋጁ እና የሰብዓዊ መብቶችን አጠባበቅ የሚያጠናክሩ በርካታ የሕግ ማዕቀፎች ተካተውበታል፡፡

ከ6ዐ ዓመታት በላይ ያገለገለውን የወንጀል ሕግ የሚተካ የወንጀል ሥነ ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1410/2018 በመጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁ ይታወሳል።

ከተሻሻሉ ዋና ዋና ሕጎች መካከል የዲጂታል ማስረጃዎች ዕውቅና አንዱ ሲሆን ይህም የቴክኖሎጂ ለውጥን ያገናዘበ የሕግ ማዕቀፍ ነው፡፡

ለአብነትም የቪዲዮ ምስሎች፣ የድምፅ ቅጂዎች፣ የኮምፒውተር መረጃዎች እና የማኅበራዊ ሚዲያ መልዕክቶች እንደ ትክክለኛ ማስረጃ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ሕጋዊ መሠረት ሰጥቷል።

ሌላው የተሻሻለው የምርመራ ዘዴዎች እና የሰብዓዊ መብቶችን የሚመለከት ሲሆን፤ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ሲውሉ ያላቸው መብት፣ የምርመራ ጊዜ ገደብ እና በምርመራ ወቅት ጠበቃ የማግኘት መብታቸው በግልጽ ተቀምጧል።

በዚህም መሰረት አንድ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ሲውል ጠበቃው እስኪመጣ ቃሉን ያለመስጠት መብቱ የሚጠበቅለት ሲሆን የተጠርጣሪው የምርመራ ገደብ ከአራት ወር እንዳይበልጥ በማድረግ ተጠርጣሪ ለረጅም ጊዜ በምርመራ እንዳይቆይ ያስችላል።

የተጎጂዎችን መብት በሚመለከት የወንጀል ድርጊት የተፈጸመባቸው ሰዎች በፍትሕ ሂደቱ ውስጥ ያላቸው ተሳትፎ፣ ጉዳታቸው የሚካካስበት መንገድ እና የሚደረግላቸው ጥበቃ ትኩረት አግኝቷል።

ሌላው የዋስትና መብትን እንደ መሠረታዊ መብት መከልከልን እንደ ልዩ ሁኔታ የሚመለከት ሕግ ሲሆን፤ በዚህም ሕጉ ግልጽ የሆኑ የዋስትና ዓይነቶችን አስቀምጧል።

እነሱም በግል ማረጋገጫ በሰው ዋስትና፣ በንብረት ዋስትና ወይም በገንዘብ ማስያዝ የሚልን አካትቷል።

ሌላኛው የምስክሮች እና የጠቋሚዎች ጥበቃ የሚመለከት ሲሆን በከባድ ወንጀሎች ላይ መረጃ የሚሰጡ ጥቆማ ሰጪዎች እና ምሥክሮች ከበቀል ወይም ከጥቃት እንዲጠበቁ የሚያስችል የሕግ ከለላ መስጠትን ይመለከታል።

በተመሳሳይ የዐቃቤ ሕግ የክስ ድርድርን በተመለከተ አንድ ተጠርጣሪ ወይም ተከሳሽ ጥፋተኛነቱን አምኖ ከዐቃቤ ሕግ ጋር በመደራደር ቅጣቱ እንዲቀልለት ወይም ክሱ እንዲቋረጥ የሚያስችል ሥርዓት በሕጉ እንዲካተት ተደርጓል።

በዚህም በአዋጁ ዐቃቤ ሕግ ክስ ለማንሳት የሚችልባቸው ምክንያቶችና ቅድመ ሁኔታዎች በዝርዝር ተቀምጠዋል።

የክስ ድርድር በሚመለከት ክስ ከመመሥረቱ በፊት ወይም ክስ ከተመሠረተ በኋላ ፍርድ እስከሚሰጥ ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ተጠርጣሪው ወይም ተከሳሹ ጥፋተኛነቱን አምኖ ከዐቃቤ ሕግ ጋር ሊደራደር ይችላል።

የድርድር ዓይነቶችን በሚመለከት ከባድ የሆነውን ክስ ወደ ቀለል ያለ የወንጀል ዓይነት በመቀየር መደራደር እንዲሁም በቅጣት ድርድር በክሱ ላይ ተስማምቶ ቅጣቱ እንዲቀልለት መደራደር የሚል ይገኝበታል።

በዚህም በድርድሩ የተደረገው በፈቃደኝነት መሆኑን፣ ተከሳሹ መብቶቹን መረዳቱን እና ድርድሩ የሕዝብን ጥቅም የማይጎዳ መሆኑን ፍርድ ቤቱ ማረጋገጥ አለበት።

በተጨማሪም ፍርድ ቤቱ ድርድሩን ውድቅ የማድረግ ሥልጣን ያለው ሲሆን በተለይም ዐቃቤ ሕግ የክስ ድርድር ሲያደርግ የወንጀል ተጎጂዎችን ፍላጎትና ስሜት ግምት ውስጥ ማስገባት እንዳለበት ሕጉ ይደነግጋል።

ተጎጂው ካሳ የሚያገኝበት መንገድም በድርድሩ ውስጥ የተከካተተ ሲሆን ይህም ተከሳሹ የቅጣት ቅናሽ እንዲያገኝ ያደርጋል፡፡

በተጨማሪም ድርድሩ መንግሥት ለምስክሮች እና ለረጅም ክርክር የሚያወጣውን ወጪ ይቆጥባል፣ ተጎጂዎች ደግሞ የፍርድ ሂደቱን ሳይጠብቁ ካሳ ወይም ይቅርታ ሊያገኙ ይችላሉ።

በአጠቃላይ እነዚህ ለውጦች ፍትሕን በፍጥነት ለመስጠት እና የተጠርጣሪዎችንም ሆነ የተጎጂዎችን መብት በተሻለ ሁኔታ ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ማሻሻያዎች ናቸው፡፡

ይህም በሀገሪቱ የፍትሕ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ ለውጥ ያመጣል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ አፈጻጸሙም ከሕገ መንግሥቱ እና ከዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌዎች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ ነው።(ኤፍ ኤም ሲ)

Address

Arba Minch'
444

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when KF2B Gamo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share