Ze-Alem ዘ-ዓለም

Ze-Alem ዘ-ዓለም Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ze-Alem ዘ-ዓለም, Media Agency, Bahir Dar.

07/06/2026
በአርሲ ንጹሃን ላይ የተሰነዘረው ጥቃት እና የጀዋር መሀመድ የሽብር ስፖንሰሮች‼️​በምስራቅ አርሲ ሸርካ እና አስኮ ወረዳዎች በምርጫው ዋዜማና ዕለት የተፈጸመው አሰቃቂ ጥቃት፣ ከአገር ውስጥ ...
03/06/2026

በአርሲ ንጹሃን ላይ የተሰነዘረው ጥቃት እና የጀዋር መሀመድ የሽብር ስፖንሰሮች‼️

​በምስራቅ አርሲ ሸርካ እና አስኮ ወረዳዎች በምርጫው ዋዜማና ዕለት የተፈጸመው አሰቃቂ ጥቃት፣ ከአገር ውስጥ አልፎ ከውጭ ኃይሎች ጋር የተገመደ ስልታዊ የሽብር ሴራ ውጤት መሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ።

በጥቃቱ ጀርባ ከአቶ ጀዋር መሀመድ የድሮ የትምህርት ቤትና የቄሮ መዋቅሮች ጋር በቀጥታ የሚገናኝ የሽብር መረብ መኖሩ የተገለጸ ሲሆን፣ ይህ መዋቅር በግብፅ ጽንፈኛ ቡድኖች (ሙስሊም ብራዘርሁድ)፣ በሻቢያ፣ በህወሃት እና በአልሸባብ ጥልፍልፍ አጋርነት በከፍተኛ ሁኔታ ፋይናንስ የሚደረግ ነው።

ዋነኛ ዓላማውም አገራዊ ምርጫውን በማደናቀፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላማዊ የዲሞክራሲ ሥርዓት መገንባት እንደማይቻል ማሳየት ሲሆን፣ ታጣቂዎቹ ንጹሃንን በመግደል፣ የክርስቲያን መኖሪያዎችንና ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናትን በማውደም፣ እንዲሁም ድርጊቱን ፈጽመው የኦነግ ሸኔን ባንዲራ በመስቀል ይፋዊ የሽብር ተግባራቸውን አሳይተዋል።

​ይህንን በአገር ውስጥ ጽንፈኞችና በውጭ ስፖንሰሮች የሚመራውን አደገኛ የጥፋት ዑደት በዘላቂነት ለመስበር የመንግስት ቁርጠኝነትና የማህበረሰቡ ንቃት ወሳኝ መስቀለኛ መንገድ ላይ ይገኛል።

መንግስት የጸጥታ ክፍተቶችን በመሙላት፣ የኃይል ሚዛኑን በማስከበርና የጥፋት መረቡን ዋና አርክቴክቶችና ፈጻሚዎች ለቅሞ ለሕግ የማቅረብ ቀዳሚ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል።

በአዲሱ የሕወሓት ካቢኔ ውስጥ የሙስሊሞች ውክልና አለመኖር በክልሉ የፖለቲካ መድረክ አነጋጋሪ ሆኗል‼️በሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) የተዋቀረው አዲሱ የድርጅቱ ካቢኔ፣ የክልሉን የ...
03/06/2026

በአዲሱ የሕወሓት ካቢኔ ውስጥ የሙስሊሞች ውክልና አለመኖር በክልሉ የፖለቲካ መድረክ አነጋጋሪ ሆኗል‼️

በሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) የተዋቀረው አዲሱ የድርጅቱ ካቢኔ፣ የክልሉን የሃይማኖት ብዝሃነትና ስብጥር ያላገናዘበና ለሙስሊሙ ማኅበረሰብ ተገቢውን የሥልጣን እድል ያልሰጠ ነው በሚል በሰፊው መነጋገሪያ መሆኑን ከክልሉ የሚወጡ መረጃዎች አመላከቱ።

ድርጅቱ በቅርቡ ይፋ ባደረገው የከፍተኛ አመራሮችና የካቢኔ አባላት ስም ዝርዝር ውስጥ የትግራይ ሙስሊም ማኅበረሰብን የሚወክሉ ግለሰቦች አለመካተታቸው፣ በማኅበራዊ ሚዲያዎችና በፖለቲካ ተንታኞች ዘንድ ጠንከር ያለ ትችትና ቅሬታ እየቀሰቀሰ ይገኛል።

የከሰሩ እና የተሸነፉ ፖለቲከኞች የምርጫ ውጤትን ላለመቀበል ከሚከተሉት ስልቶች መካከል የኢሕአፓ ሰሞነኛ ስልት አንዱ ነው። የማይታረቅ አቋም አራማጆች፣ ከህሊናቸው የተጋጩ የታሪክ አተላዎች ዓ...
03/06/2026

የከሰሩ እና የተሸነፉ ፖለቲከኞች የምርጫ ውጤትን ላለመቀበል ከሚከተሉት ስልቶች መካከል የኢሕአፓ ሰሞነኛ ስልት አንዱ ነው።

የማይታረቅ አቋም አራማጆች፣ ከህሊናቸው የተጋጩ የታሪክ አተላዎች ዓለምአቀፍ ተቋማት እና ሚዲያዎች የመሰከሩለትን ዲሞክራሲያዊ የምርጫ ሥርዓት ጥያቄ ውስጥ ለማስገባት ቀድመው አቅደው እንደነበር መግለጻችን ይታወቃል።

ከጫካው ኃይል በተሰጣቸው ትዕዛዝ መሠረት የዕቅዳቸው አንዱ አካል የሆነው የሚዲያ ፕሮፓጋንዳ ምርጫው "ፍትሐዊ አልነበረም"፣ "ተጭበርብሯል" በማለት የሂደቱን ህጋዊነት (Legitimacy) ለማሳጣት ሲሞክሩ እንደማየት የሚያሳፍር ነገር የለም።

የስልጣን ሽኩቻ እና የውስጥ መፈራረስ! በማርሸት እና በዝናቡ መካከል የፈነዳው ግልጽ የሃይል ግጭት መላው የፋኖ መዋቅር ምን ያህል እየፈራረሰ እንደሆነ ማረጋገጫ ነው። ይህ በማርሸትና በዝናቡ...
29/05/2026

የስልጣን ሽኩቻ እና የውስጥ መፈራረስ!

በማርሸት እና በዝናቡ መካከል የፈነዳው ግልጽ የሃይል ግጭት መላው የፋኖ መዋቅር ምን ያህል እየፈራረሰ እንደሆነ ማረጋገጫ ነው። ይህ በማርሸትና በዝናቡ መካከል የሚታየው የመናከስ አዝማሚያ አሁን ላይ ወደ ሌሎች እዞችም በከፍተኛ ሁኔታ እየተጋባ ይገኛል።

በማርሸትና በዝናቡ መካከል ያለው ግጭት በሌሎች እዞችም ሰርፆ መሪዎች እርስ በርስ ጥርጣሬ ላይ ናቸው።

ለአንድ የጋራ አላማ ከመቆም ይልቅ የየራሳቸውን ጥቅምና ስልጣን ለማስከበር በመሯሯጥ ላይ መጠመዳቸው።

አንዱ እዝ ሌላኛውን የማይሰማበት እና ማዕከላዊ ትዕዛዝ ሙሉ በሙሉ የጠፋበት ደረጃ ላይ መደረሱ።
ይኸው የመሪዎች ብቃት ማጣትና ግጭት በሰላማዊው ማህበረሰብ ላይ የደህንነትና የኢኮኖሚ ቀውስ እያባባሰ መምጣቱ።

ይህ በማርሸትና በዝናቡ ግጭት የጀመረው የውስጥ መበላላት፣ አጠቃላይ የፋኖ ስብስብ የመምራት አቅም እንደሌለውና የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ መድረሱን በግልጽ ያሳያል!

ዘመነ ካሴ አንዲት ቃል መተንፈስ የማይችል የቁም እስረኛ ሆኗል!ዘመነ ካሴ አስመራ ላይ የሻዕቢያ እና የህወሓት የቁም እስረኛ ከሆነ ሰነባብቷል። ትግሉን እየመራ እንዳልሆነ እና ምንም አይነት ...
29/05/2026

ዘመነ ካሴ አንዲት ቃል መተንፈስ የማይችል የቁም እስረኛ ሆኗል!

ዘመነ ካሴ አስመራ ላይ የሻዕቢያ እና የህወሓት የቁም እስረኛ ከሆነ ሰነባብቷል። ትግሉን እየመራ እንዳልሆነ እና ምንም አይነት የአመራር ትዕዛዝ መስጠት የማይችል የቁም እስረኛ ሆኖ መቀመጡን ሾልከው የወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

የውስጥ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ ባለፈው ወር ማገባደጃ አካባቢ በማርሸት እና በዝናቡ መካከል የተፈጠረው አለመግባባት መነሻው ይህ እንደሆነም ተረጋግጧል። ነገሩ እንዲህ ነው... ከኢሳያስ አፈወርቂ እና ከደብረጽዮን ጋር በነበራቸው የ3ዮሽ የፅምዶ ውይይት ዘመነ ካሴ ትግሉን በምንፈልገው ልክ አልመራህውም፣ የግዳጅ አፈጻጸሙ ድክመት በጥልቀት መገምገሙን ተከትሎ የግምገማው ሚስጥር በማርሸት ፀሐይ በኩል ሾልኩ በመውጣቱ እንደሆነም ታውቋል።

በምርጫ የሚፀና ሀገረ መንግስት እንጂ በጠላት የሚዘጋ ጉዞ የለም!​የአንድ ሀገር ህልውና እና ዘላቂነት የሚመሰረተው በህዝቦቿ ነፃ ምርጫ፣ በጋራ መግባባትና በጠንካራ ተቋማዊ ግንባታ ላይ እንጂ...
29/05/2026

በምርጫ የሚፀና ሀገረ መንግስት እንጂ በጠላት የሚዘጋ ጉዞ የለም!

​የአንድ ሀገር ህልውና እና ዘላቂነት የሚመሰረተው በህዝቦቿ ነፃ ምርጫ፣ በጋራ መግባባትና በጠንካራ ተቋማዊ ግንባታ ላይ እንጂ በታሪካዊ ጠላቶች ሴራና ተንኮል አይገታም።

የሀገርን ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም ህዝብ በነጻነት የሚመርጠው፣ የሚያምንበትና የሚደግፈው የመንግስት ስርዓት መገንባት ቀዳሚው ተግባር ነው።

ታሪክ እንደሚያስተምረን ከውጭም ሆነ ከውስጥ የሚነሱ የጥፋት ኃይሎችና የጠላት ወረራዎች ጊዜያዊ ፈተናዎችን ሊፈጥሩ ቢችሉም፣ የህዝብ እውነተኛ ውክልና ያለውና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ የጸና ሀገረ መንግስትን ግን ፈጽሞ ሊያፈርሱት አይችሉም።

ጠላቶች ጉዟችንን ለማስቆም የሚያሴሩት ሴራ ሁሉ በህዝባዊ አንድነትና በህጋዊ ስርዓት ጥንካሬ ፊት መክኖ ይቀራል።

​ኢትዮጵያ ወደ ላቀ ብልጽግና እና ዘመናዊነት የምታደርገው ጉዞ በማናቸውም አይነት ውጫዊ ጫናዎችና የጥፋት ሃይሎች ዛቻ ሊቀለበስ የማይችል ጽኑ መስመር ነው።

እውነተኛው ሀገራዊ ጥንካሬ የሚመነጨው ከህዝብ ፍላጎትና ከምርጫ ድምፅ በመሆኑ፣ ይህንን በህዝብ ፍቃድ ላይ የተገነባን ጉዞ ማንም ሃይል መዝጋት አይቻለውም።

ጠላቶች በከፋፋይ አጀንዳዎችና በትርምስ መንገዶች ሀገርን ለማዳከም ቢሞክሩም፣ በህዝብ ምርጫና በልማት ቁርጠኝነት የጸናው መንግስታዊ መዋቅር ፈተናዎችን ሁሉ በድል የመሻገር አቅም አለው።

ስለሆነም፣ የሀገራችን ጉዞ ወደፊት መጓዙን ይቀጥላል እንጂ በጠላቶች ምኞትና ሴራ መቼም ቢሆን አይገታም።

የአማራ ህዝብ ፅንፈኛው ያደረሰበትን በደል አምርሮ ፊት ለፊት እየታገለ ነው! የባንዳና የፅንፈኛ ቡድን አካሄድ እንደማያዋጣው ህዝባችን በተግባር አሳይቷል! የአማራ ህዝብ ዛሬ ላይ መንገድ ዝጋ...
28/05/2026

የአማራ ህዝብ ፅንፈኛው ያደረሰበትን በደል አምርሮ ፊት ለፊት እየታገለ ነው! የባንዳና የፅንፈኛ ቡድን አካሄድ እንደማያዋጣው ህዝባችን በተግባር አሳይቷል!

የአማራ ህዝብ ዛሬ ላይ መንገድ ዝጋ፣ የልማትና የሰላም ጉዞን አስተጓጉል ተብሎ በፅንፈኞች የፈጠራ ወሬና ማስፈራሪያ የሚደናገርበት ጊዜ አብቅቷል።

 ‼️ ደቡብ ጎንደር ደራ ወረዳ‼️የምርጫ ኮረጆ ለመዝረፍና ለፕሮፓጋንዳ ለመጠቀም የመጣ ጽንፈኛ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተምስሷል። በደቡብ ጎንደር ዞን ደራ ወረዳ ዋንዛየ ፍል ተሰባስቦ የቆየው የፅን...
25/05/2026

‼️ ደቡብ ጎንደር ደራ ወረዳ‼️

የምርጫ ኮረጆ ለመዝረፍና ለፕሮፓጋንዳ ለመጠቀም የመጣ ጽንፈኛ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተምስሷል። በደቡብ ጎንደር ዞን ደራ ወረዳ ዋንዛየ ፍል ተሰባስቦ የቆየው የፅንፈኛ ቡድን የምርጫ ኮሮጆ በመዝረፍ ፎቶ ለመነሳት ያደረገው ጥረት ህይወት አስከፍሎታል።

ፎክሮ የመጣው የጣና ገላውዲወስ ክፍለ ጦሩ መሪ ሙሉቀን አለኸኝን ጨምሮ ከ9 በላይ የተመሰሰ ሲሆን ከ16 በላይ ቆስሏል። ከ12 በላይ ጉማራ ወንዝ እየዘለለ ገብቶ በውሀ ተወስዷል።

እርምጃው የቀጠለ ሲሆን፦

1) የክፍለ ጦሩ መሪ ሙሉቀን አለኸኝ እስከነ አጃቢዎቹ
2) ጋሻው የተባለ የዘመቻ መሪ
3) ሀብታሙ የተባለ ከዚህ በፊት ወንድሙ ፅንፈኛ ሁኖ ከዜው ቦታ በዝርፊያ በራሱ ጓደኞች የተደመሰሰ ይገኙበታል።

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ze-Alem ዘ-ዓለም posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category