በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት This is the official page of በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መ/ኮ/ጉ /ፅ/ቤት

ከፍተኛ የማህበረሰብ ጤና ስጋት እየሆነ የመጣውን ህገ ወጥና ጥራቱን ያልጠበቀ የመድሃኒት ዝውውር ችግር ለመቅረፍ ውጤታማና ተመጋጋቢ የቁጥጥር ስርኣት መዘርጋት እንደሚገባ ተጠቆመ ። ሰኔ 18/...
25/06/2026

ከፍተኛ የማህበረሰብ ጤና ስጋት እየሆነ የመጣውን ህገ ወጥና ጥራቱን ያልጠበቀ የመድሃኒት ዝውውር ችግር ለመቅረፍ ውጤታማና ተመጋጋቢ የቁጥጥር ስርኣት መዘርጋት እንደሚገባ ተጠቆመ ።

ሰኔ 18/2018 ለአለም ማህበረሰብ ከፍተኛ የጤና ስጋት እየሆነ የመጣውን ህገ ወጥና ጥራቱን ያልጠበቀ መድሃኒት ዝውውርና የአጠቃቀም ጉድለት ችግር ለመቅረፍ ውጤታማና ተመጋጋቢ የቁጥጥር ስርኣት መዘርጋት እንደሚገባ ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን እና በክልሉ ጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ ተቋማትና ግብኣቶች ቁጥጥር ባለስልጣን በጋራ ባዘጋጁት መድረክ ላይ እንደተጠቆመው ችግሩን ለመቅረፍ የማህበረሰብ ግንዛቤን ከማሳደግ ባለፈ በጠንካራ እርምጃዎች የታጀበ የቁጥጥር ስርኣት መዘርጋት ይገባል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ እንደገለጹት ከጦር መሳሪያ በላይ ከፍተኛ ስጋት እየሆነ የመጣው የህገ ወጥ መድሃኒት ዝውውር ፣ የአጠቃቀም ጉድለትና የመጠቀሚያ ጊዜን አለመጠበቅ ችግር ከፍተኛ ትኩረትን ይሻል።

ከዚህ አኳያ የዘርፉ ተቋማት በችግሩ ዙሪያ ህዝብን ከማስገንዘብ ባለፈ ጠንካራ የቁጥጥርና ክትትል ስርኣት ዘርግተው በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ ይኖርባቸዋል ብለዋል ።

የኢትዮጵያ የምግብና መድሃኒት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ በበኩላቸው የችግሩ አሳሳቢነት እየሰፋ መምጣቱን ገለጸው የሚወሰዱ እርምጃዎች ጠንካራ መሆን እንዳለባቸው ጠቁመዋል ።

ለዚህም የተቆጣጣሪ አካላት ሚና ከፍተኛ እንደሆነ ተናግረዋል ። በተለይ የመድሃኒት አያያዝ፣አጠቃቀምና አወጋገድ ላይ ሰፊ ስራ እንደሚጠብቃቸው አስታውቀዋል ።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ተቋማት በሀገሪቱ የወጡ ዝቅተኛ ስታንዳርዶችን አሟልተው ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝም ገልጸዋል ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጤናና ጤና ነክ ተቋማትና ግብኣቶች ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካ አለሙ ችግሩን ለመቅረፍ የግሉ ዘርፍና የመንግስት የጤና መዋቅሮች ቅንጅት ወሳኝ ነው ብለዋል።

ይህ ብቻ ሳይሆን አገልግሎት አቅራቢው ፣ ተቆጣጣሪ ውና አገልግሎት ተቀባዩ ማህበረሰብ በችግሩ ስፋትና አሳሳቢነት ዙሪያ የጋራ መግባባት ፈጥረው በተደራጀ መንገድ መንቀሳቀስ ይጠበቅባቸዋል ሲሉም አክለዋል።

እንደ መዋቅር የተቀመጠውን ስታንዳርድ በአግባቡ በማሟላትና ውጤታማና ተመጋጋቢ የቁጥጥር ስርኣት በመዘርጋት ብሎም የዲጅታል መረጃ ስርኣትን በማጎልበት በኩል ሰፊ ስራ እንደሚጠይቅ ተናግረዋል ።

በዳውድ አብደላ

ምክር ቤቱ ከ9 ቢሊየን 983 ሚሊየን 783ሺ በላይ ብር የተጨማሪ በጀት ረቂቅ አዋጅ በማጽደቅ ጉባኤውን አጠናቀቀ ሰኔ 18/2018 የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ...
25/06/2026

ምክር ቤቱ ከ9 ቢሊየን 983 ሚሊየን 783ሺ በላይ ብር የተጨማሪ በጀት ረቂቅ አዋጅ በማጽደቅ ጉባኤውን አጠናቀቀ

ሰኔ 18/2018 የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤው በወልቂጤ ከተማ ተካሂዷል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን መሰረተ ልማት እና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበው የተጨማሪ በጀት ረቂቅ አዋጅ ላይ በዝርዝር ተወያይቷል።

ምክር ቤቱ በ 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን በ3ኛ አስቸኳይ ጉባኤው ከ9 ቢሊየን 983 ሚሊየን 783ሺ በላይ ብር የተጨማሪ በጀት ረቂቅ አዋጅ በማጽደቅ ጉባኤውን አጠናቋል።

በተስፋዬ መኮንን

ምክር ቤቱ 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን በወልቂጤ ከተማ እያካሔደ ነው ሰኔ 18/2018 የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት ...
25/06/2026

ምክር ቤቱ 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን በወልቂጤ ከተማ እያካሔደ ነው

ሰኔ 18/2018 የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤው በወልቂጤ ከተማ እየተካሔደ ነው

የክልሉ መንግስት ኮሚኒኬሽን

ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠ...
25/06/2026

ምክክር - ወደ መግባባት መሸጋገሪያው ድልድይ!

በአመለካከት መለያየት ሥሪቱ ተፈጥሯዊ ነው። ሰዎች ልክ በመልክ፣ ቁመት ውፍረት ወይም ቅጥነት ሥብጥር፤ ምድርም በተፈጥሮ አቀማመጥ እና በዓየር ጠባይዋ ወጥ እንዳልሆነችው ሁሉ ማለት ነው።

ለአንድ ሕዝብ እና ሀገር ብልጽግና ሲባል ከተበተነ ይልቅ የተደመረ ሐሳብ በእጅጉ ይጠቅማል። ሀገርኛ ብኂላችን “ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ” ብሎ መሰባሰብን እንደሚሰብከው።

ከሥሪታቸው አንጻር ዕሳቤዎች የግድ ተጨፍልቀው አንድ እንዲሆኑ ባይጠበቅም፤ ሀገርና ሕዝብን ወዳስቀደመው በይበልጥ ገዥ ሐሳብ ወደሆነው መቅረብ ግን ተገቢ ይሆናል። በተለያዩ ዋልታዎች ቆሞ መጓተት ለማን ይጠቅማል?

የለውጡ መንግሥት ለኢትዮጵያ ከቸራቸው ትልልቅ ጉዳዮች መካከልም የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሙ አንዱ ነው።

ሀገራዊ ምክክር በአንድ ሀገር ውስጥ የምንኖር ሕዝቦች ራሳችንን በታማኝነት ፈትሸን በሐሳብ ልየነቶች ላይ ለመነጋገር መፍቀዳችንን የሚጠይቅ ሂደት እንደመሆኑ፤ በቁጥር የማይተመኑ ረቂቅ የሆኑ ዋጋዎች አሉት።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁትው ፤ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔው ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ይካሄዳል።

እዚህ ደረጃ ከመደረሱ በፊት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ኮሚሽኑ በየጊዜው ማሳወቁም ይታወሳል።

👉 ሀገራዊ ምክክር ምን ይጠግናል?
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሥራ በሆነው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 384 ላይ እንደተቀመጠው፤ በሀገረ-መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፤ ያልተግባባባቸውን ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይህን የዘመናት ስብራት ይጠግናል።

የምክክር ጉባኤው ከሚመክርባቸው ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች ውስጥ አጀንዳ ቁጥር ሁለት በምን በምን ጉዳዮች ላይ ይመክራል? አጀንዳ 2 የመንግስት አደረጃጃትና ቅርጽ እንዲሁም የፖለቲካ ስርዓት...
24/06/2026

የምክክር ጉባኤው ከሚመክርባቸው ስምንቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች ውስጥ አጀንዳ ቁጥር ሁለት በምን በምን ጉዳዮች ላይ ይመክራል?

አጀንዳ 2 የመንግስት አደረጃጃትና ቅርጽ እንዲሁም የፖለቲካ ስርዓት፣ የፖለቲካ ውክልናና የምርጫ ስርዓት ሲሆን በሚከተሉት ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራል:-

👉 የመንግስት አደረጃጃትና ቅርጽ፣

👉 የመንግስት አደረጃጃት አስተዳደር ስርዓት አይነት፣

👉 የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት (39/1)፣

👉 የብሔር ብሔረሰቦች ትርጓሜ፣

👉 የህገ መንግሥቱ አንቀጽ 39/5፣

👉 የፌዴራል መንግሥትና የክልል መንግስታቶች መሪዎች የስልጣን ዘመን፣

👉 የፌዴራል መንግሥትና የክልል መንግስታት ግንኙነት (የስልጣን ክፍፍል፣ የፊስካል ፌዴራሊዝምና የሀብት ክፍፍል)፣

👉 የክልል አስተዳደርና ወሰኖች (የአዳዲስ ክልሎች አመሰራረት፣ የክልል አስተዳደራዊ ወሰኖች)፣

👉 የሕግ አውጪው አካል/ፓርላማ መዋቅርና ሚና፣

👉 ሕገ መንግሥትን የመተርጎም ስልጣን፣

👉 የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ስርዓት (አንቀጽ 104 እና 105)፣

👉 የፖለቲካ ውክልናና የምርጫ ስርዓት ጉዳዮች፣

👉 የሀገሪቱ የምርጫ ስርዓት፣

👉 የመድብለ ፓርቲ ስርዓት፣

👉 የፖለቲካ ፓርቲ አደረጃጀት፣

👉 የመንግሥትና የገዢ ፓርቲ ሚና መለያየት፣

👉 የምርጫ ክልሎች አወቃቀር እና

👉 የፖለቲካ ፓርቲዎች የመንግሥት ሀብት አጠቃቀም ናቸው።

24/06/2026

#በምስራቅ መስቃን ወረዳ በፌድራል ተቋማት ደረጃ በበጎ ፈቃድ የተገነቡ መኖሪያ ቤቶች የተጠቃሚው ቤተሰቦች በ
ማስረከብ መርሐ ግብር ላይ ለመጡ እንግዶች ዱዓ ሲያደርጉ።

ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ጉዞ ወደ አዲስ ምዕራፍ *************የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዋጅ የተሰጠውን ኃላፊነት በመወጣት ባለፉት ዓመታት ስኬታማ የዝግጅት ምዕራፎችን ሲ...
24/06/2026

ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ጉዞ ወደ አዲስ ምዕራፍ
*************

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዋጅ የተሰጠውን ኃላፊነት በመወጣት ባለፉት ዓመታት ስኬታማ የዝግጅት ምዕራፎችን ሲያከናውን ቆይቷል።

በተለይም በስትራቴጂያዊ ዕቅዱ መሠረት የአጀንዳ ማሰባሰብ፣ የመለየትና የመቅረጽ ተግባራትን በስኬት በማጠናቀቅ፣ አሁን ላይ ወደ ታላቁ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ለመሸጋገር የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሷል።

ባለፉት ዓመታት በመላው ኢትዮጵያ የተከናወነው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት፣ ዜጎች እንደ ሀገር ያልተግባቡባቸውን መሠረታዊ ጉዳዮች፣ ሥጋቶችና የነገ ምኞቶቻቸውን በነፃነት ያጋሩበት ሰፊ ሕዝባዊ መድረክ ነበር።

ኮሚሽኑ ለተሳታፊዎች ተደራሽነት ልዩ ትኩረት በመስጠት እጅግ በርካታ ሀገራዊ ሃሳቦችን ማሰባሰብ ችሏል። ይህ ታሪካዊ ሂደት ለሚካሄደው ትልቁ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ እንደ ዋነኛ ቅድመ ሁኔታና የስኬት መሠረት ሆኖ ያገለግላል።

የሚካሄደው የጉባኤ ምዕራፍ ከቀደሙት ሂደቶች የተለየና የላቀ ይዘት ያለው ነው። በምክክሩ አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመፍጠር፣ ሀገራዊ መግባባትን ለማምጣት፣ እንዲሁም ሂደቱ ተዓማኒና ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን ኮሚሽኑ በቅንነት እየሠራ ይገኛል።

በመዲናችን አዲስ አበባ ከ4 ሺህ በላይ የሕዝብ ተወካዮችና ባለድርሻ አካላት በሚሳተፉበት በዚህ ጉባኤ፣ ቀደም ሲል በሕዝብ የተመረጡ ወኪሎች በኮሚሽኑ ቀርበው በሚመከሩባቸው አጀንዳዎች ላይ በሰፊው ይወያያሉ።

ሂደቱም በሃሳብ ነፃነትና በዲሞክራሲያዊ መብቶች ላይ ተመስርቶ፣ ሀገራዊ አንድነትን የሚያጠናክሩ ውሳኔዎችንና ምክረ-ሃሳቦችን በማመንጨት ይከናወናል።

በመሐመድ ፊጣሞ

በምስራቅ መስቃን ወረዳ ለግብርና ባለሙያዎች እና የልማት ሰራተኞች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ስልጠና በስኬት ተጠናቀቀ!!።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ሰኔ 17፣2018 ዓ፣ም {የምስራቅ መስቃን...
24/06/2026

በምስራቅ መስቃን ወረዳ ለግብርና ባለሙያዎች እና የልማት ሰራተኞች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ስልጠና በስኬት ተጠናቀቀ!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰኔ 17፣2018 ዓ፣ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት}

በምስራቅ መስቃን ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ም/ኃላፊ እና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙስጠፋ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት ግብርና ዘርፉን በዘመናዊ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ለመደገፍ እና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያለመስልጠና ለወረዳው ግብርና ፅህፈት ቤት ባለሙያዎች እና የልማት ሰራተኞች ተሰጥቷል።

ይህ ስልጠና በዋናነት በከፍተኛ ሁኔታ ተሻሽሎ እና ዘምኖ ይፋ የሆነውን Farmer Chat የተሰኘውን የዲጂታል ረዳት መተግበሪያ አጠቃቀም ላይ ያተኮረ ነበር።

መተግበሪያው አርሶ አደሮችና የልማት ሰራተኞች የግብርና መረጃዎችን፣ የምክር አገልግሎቶችን እና አዳዲስ አሰራሮችን በቀላሉ በስልካቸው እንዲያገኙ የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤት ነው።

በስልጠናው ወቅት የልማት ሰራተኞች መተግበሪያውን እንዴት መጠቀምና ማዘመን (Update) እንዳለባቸው፣ አዳዲስ አርሶ አደሮችን እንዴት ወደ ሲስተሙ ማስገባት (Onboard) እንደሚችሉ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የተግባር ልምምድ ተደርጓል።

የወረዳው ግብርና ፅህፈት ቤት የስልጠናው ተሳታፊዎች ያገኙትን እውቀት ተጠቅመው በየቀበሌው የሚገኙ አርሶ አደሮችን የዚህ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲያደርጉ እና የግብርና ስራቸውን እንዲያዘምኑ ጥሪ አቅርቧል።

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው ይህ መተግበሪያ የእለት ተእለት የስራ እንቅስቃሴያቸውን እጅግ እንደሚያቀልላቸው ገልጸው፣ የተማሩትን በተግባር ላይ በማዋል አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

#ሊንኩን በመጫን"ግብርና ነክ ችግሮች ሲያጋጥምዎት መጨነቅ አያስፈልግም። 🌾በ FarmerChat መተግበሪያ፣ እያንዳንዱ አርሶ አደር ፈጣን መፍትሄዎችን ማግኘት ይችላል።
https://farmerchat.go.link/bgKbQ

"ቴክኖሎጂ ለግብርና ስኬታችን እና ለምግብ ዋስትናችን!"

መረጃው የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽ ነው

በምስራቅ መስቃን ወረዳ በፌድራል ተቋማት በጎ ፈቃድ የተገነቡ መኖሪያ ቤቶች ለተጠቃሚ ቤተሰቦች የማስረከብ መርሐ ግብር ተካሄደ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ሰኔ 17፣2018 ዓ/ም {የ...
24/06/2026

በምስራቅ መስቃን ወረዳ በፌድራል ተቋማት በጎ ፈቃድ የተገነቡ መኖሪያ ቤቶች ለተጠቃሚ ቤተሰቦች የማስረከብ መርሐ ግብር ተካሄደ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰኔ 17፣2018 ዓ/ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት}

በፌድራል የሠላምና ፍትህ ተቋማት ትብብር በምስራቅ ጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ በክረምት በበጎ ፍቃድ የተገነቡ 9 መኖሪያ ቤቶች ለተጠቃሚ ቤተሰቦች የማስረከብ መርሀ ግብር ተካሄደ።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ ዶ/ር መሀመድ ሰብራላ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት በዛሬው መርሃ ግብር ለተገኙ እንግዶች እንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው፣የፓርቲያችን የሰው ተኮር የሆነው የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በወረዳችን ለዘጠኝ መኖሪያ ቤት ለሌላቸው ለችግር ተጋላጨ ለሆኑ ዜጎች በአዲስ መልክ ገንብቶ ማስረከቡ ለፌድራል ተቋማት ምስጋና አቅርበዋል።

የፌድራል ፍትህ ሚኒስትር ሀና አርዓያ ስላሴን በርክክብ መርሃ ግብር ወቅት እንደገለፁት በጎ ፍቃድ ተቋማት በክርምት ወቅት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየፈፀመ ይገኛል ያሉ ሲሆን አሁን በዚህ አካባቢ በአዲስ መልክ የተገነቡት ቤቶች ለዘመናት ችግራችንን ፈቶላቸዋል ሲሉ ገልፀዋል።

በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ከተከናወኑ የልማት ሥራዎች መካከል የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች አዲስ ግንባታ ሥራ አንዱ ሲሆን በዚህም ብዙዎች ተጠቃሚ ሆነዋል ሲሉ ሚኒስትር ገልፀዋል።

መኖርያ ቤት የሌላቸው በደሳሳ ጎጇቸው ለጸሐይና ዝናብ ተጋልጠው ለሚኖሩ ዜጎች ተቋሙ ደራሽ መሆኑ አስታውሰዋል፡፡

የፌድራል ተቋማቱ በክርምት በጎ ፍቃድ በርካታ ስራዎች መከናወኑ ገልፀው በቀጣይነት ባለው መልኩ እንደሚከናወን ገልፀዋል፡፡

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በመርሃ-ግብር ተገኝተው እንደገለፁት የፌደራል ተቋማት በክርምቱ ለተጠቃሚዎች የተደረገው ጎጇቸው ለዝናብ፣ለጸሐይና ለመጥፎ ሽታ ተጋልጠው በችግር ውስጥ ይኖሩ እንደነበር ገልጸው፣ በአሁኑ ወቅት በበጎ ፍቃደኛ ቤታቸው በአዲስ መልክ ተሰርቶ መረከባቸውን ተናግረዋል።

የበጎ ፍቃድ ተጠቃሚዎች እንደተናገሩት የተደረገልን ድጋፍ ጠያቂና ደጋፊ ወገን እንዳለኝ ያክል ተሰምቶኛል ያሉት ተጠቃሚዎች፣በዚህም ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

"ከሰው እኩል በደስታ መኖር ጀምሬያለሁ" ያሉት ወይዘሮ እጅጋየሁ "የበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ የነበረብንን ችግር ከመፍታት ባለፈ የዘመናት ከሰው እኩል አድርጎናል" ብለዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ የፌድራል ፍትህ ሚኒስትር ሀና አርዓያ ስላሴን ጨምሮ የፌድራል የሰላምና የፍትህ ተቋማት፣የክልል፣የዞን፣የወረዳ አመራሮች፣የሀገር ሸማግሌዎች፣
የሀይማኖት አባቶች፣ወጣቶች፣
የአካባቢው ማህበረሰብ እና ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል።

ዘገባው የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውጤታቸው በምርጫ ቦርድ ይፋ ከተደረጉ 33 የፓርላማ መቀመጫዎች ውስጥ አጠቃላይ የምርጫ ውጤት 👇👇
23/06/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውጤታቸው በምርጫ ቦርድ ይፋ ከተደረጉ 33 የፓርላማ መቀመጫዎች ውስጥ አጠቃላይ የምርጫ ውጤት 👇👇

Address

Ensseno
Butajira

Telephone

+251924705963

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት:

Share