Tarmaber woreda industry and investment group

Tarmaber woreda industry and investment group Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Tarmaber woreda industry and investment group, Advertising/Marketing, Debre Sina.

03/04/2026
የጣርማበር ወረዳ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤትአምራች ኢንዱስትሪዎች ለዘመናዊ ግብርና  የዕውቀት ሽግግር ለማካሄድ ቁልፍ ሚና አላቸው-  የሰ/ሜሸዋ ዞን የጣርማበር ወረዳ ኢንዱስትሪና ኢን...
05/01/2026

የጣርማበር ወረዳ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት
አምራች ኢንዱስትሪዎች ለዘመናዊ ግብርና የዕውቀት ሽግግር ለማካሄድ ቁልፍ ሚና አላቸው
- የሰ/ሜሸዋ ዞን የጣርማበር ወረዳ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት “ኢትዮጵያ ታምርት” በሚል መሪ የንቅናቄ መድረክ አካሄደ፡፡
- ታህሣስ 22/4/2018 ዓ.ም ደ/ሲና
- በመድረኩ የተሳተፉ የወረዳው ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ ባለድርሻ አካላት፣የወረዳው ውስጥ ያሉ ባለሀብቶችና እጩ ባለሃብቶች ተገኝተዋል፡፡
- የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጣ/በር ወረዳ ምክትል አስተዳደሪና የውሃ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሽመልስ ማናዬ “ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ መድረክ አምራች ኢንዱስትሪው ተኪ ምርት በማምረት ለገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን የእውቀት ሽግግር ለማካሄድ ወሳኝ ሚና አላቸው
- የግብርናው ዘርፍ በዘመናዊ መንገድ በማዘመን ምርትና ምርታማትን በመጨመር ለአምራች ኢንዱስትሪዎች በቂ ግብዓት ሲቀርብ ኢንዱስትሪውና ግብርናው ተመጋጋቢ ይሆናል፡፡ በተጨማሪም አምራች ኢንዱስትሪው ለዘመናዊ ግብርና /የገጠር ኢንዱስትሪያላዜሽን/ የእውቀት ሽግግር ለማከናወን ወሳኝ ሚና አላቸው፡፡
- ለውይይቱም የሚሆን ሰነድ ተዘጋጅቶ በጣ/በር ወረዳ ኢንዱ/ኢንቨ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አድሴ ሰይፈ የቀረበ ሲሆን ሰነዱ በተለይም ወረዳው ውስጥ ያሉ የኢንቨስትመንት ፀጋዎችን በስፋት ያስተዋወቀ ሲሆን በግብርና ዘርፍ ብዙ ያልተሰራበት ለውጪ ገበያ የሚቀርብ ለምሳሌ፡- ማሾ ፣ሰሊጥ፣ጤፍ …..፣የአበባና የብዕር ዕህሎችን እንዲሁም ኦፓል፣ የድንጋይ ከሰል በተጨማሪም ሰፊ የቱሪዝም ሀብት…… ወዘተ በዚህ በተዘረዘሩት ፀጋዎች ላይ ባለሀብቶች ትኩረት ሰጥተው ኢንደሰሩ ሰፊ ገለፃ ተደርጓል፡፡
- በማጠቃለያውም አምራች ኢንዱስትሪዎች ከግብርናው ጋር ተመገጋጋቢ በመሆን /የገጠር ኢንዱስትሪያላዜሽን/ በትኩረት አንዲሰራ ለባለሃብቶቹ ጥሪ የቀረበ ሲሆን ወረዳውም የሚጠበቅበትን የድጋፍና ክትትል ምቹ ሁኔታ እንፈጠውራለን ተብሏል ።
-

24/10/2025

የጣርማበር ወረዳ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት
የሰ/ሜሸዋ ዞን የጣርማበር ወረዳ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ወቅታዊ የተቋሙን ተግባራትን ገመገመ፡፡
ጣ/ር/ወ/ኢንዱ/ኢንቨስትመንት ፅ/ቤት ጥቅምት 12/02/2018 ዓ.ም
የወረዳው አጠቃላይ ሰራተኛ እና የሂደት አስተባባሪዎች በተገኙበት የጥቅምት ወር በተቋሙ የተስሩ ተግባራት ሪፖርት ከቀረበ በኋላ ሰፊ ውይይት ተደርጎ በህዳር ወር የሚሰሩ ሥራዎች ላይ የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጧል
ይኸውም 1 ለኢንቨስትመንት የሚሆን ቦታ ከሶስተኛ ወገን ነፃ ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው ቁልፍ ተግባር መሆኑ
 ለአገር ውስጥና ለውጪ ባለሀብቶች ወደ ወረዳችን መጥተው እንዲያለሙ የተለያዩ የኢንቨስትመንት ማራጮችን በተለያዩ የማስታዎቂያ ዘዴዎችን በመጠቀም ማስተዋወቅ፡፡
2 የፕሮጀክቶችን ችግር ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን መፍታት ለምሳሌ፡-
 የመሰረተ ልማት ችግር ያለባቸውን ፕሮጀክቶች በፍጥነት መፍታት
 የፋይናንስ ችግር ያለባቸውን ፕሮጀክቶች መለየትና ግንዛቤ በመስጠት ብድር እንዲያገኙ ከአብዳሪ ተቋማት ጋር ማገናኘት
 የገበያ ችግር ያለባቸውን ፕሮጀከቶች የገበያ ትስስር መፍጠር ወዘተ የመሳሰሉት ናቸው፡፡

10/10/2025

የጣርማበር ወረዳ ኢንዱስትሪናኢንቨስትመንት ጽ/ቤት
የሰ/ሜሸዋ ዞን የጣርማበር ወረዳ ኢንዱስትሪናኢንቨስትመንት ጽ/ቤት
የ2017 በጀት ዓምት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2018 እቅድ ትውውቅ መድረከ አካሄደ
ጣ/ር/ወ/ኢንዱ/ኢንቨስትመንት ፅ/ቤት መስከረም28/01/2018 ዓ.ም ደብረሲና
የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የፅ/ቤቱ ሀላፊ አቶ አዲሴ ሰይፈ ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የወረዳውን እምቅ የኢንቨስትመንት ፀጋ በመለየት እና በማስተዋወቅ በወረዳው ውስጥ ያሉ ለኢንቨስትመንት የሚሆኑ ቦታዎችን ከ3ኛ ወገን ነፃ በማድረግ ባለሀብቱ ወደ ወረዳችን መጥቶ ኢንቨስት እንዲያደርግ ትልቅ ድርሻ መወጣት ይገባል ብለዋል።
አክለውም አዳዲስ ባለሀብቶች ወደ ወረዳችን እንዲመጡ በቂ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሁል ጊዜ ተግባራችን መሆን አለበት ብለዋል፡፡
በመድረኩም የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት ከተደረገ በኋላ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበትና አስተያየት ተሰጥበታል፡፡
በማጠቃለያውም በተለይም ከአሁን በፊት የነበሩ ፕሮጀክቶችን የመሰረተ ልማት እና የፋይናንስ ችግር ያለባቸውን ፐሮጀክቶች መደገፍና ብድር እንደያገኙና ተኪ ምርት ኢንዲያመርቱ ማድረግ ቀጣይም አዳዲስ ባለሀብቶች መልመልና ወደ ወረዳችን መጥተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ ሰፊ ርብርብ ማድረግ የሁሉም አካላት ተግባር ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡

04/06/2025
23/07/2017 የኢንቨስትመንት ስራዎችን ለማሳለጥ ከአጋር አካላት ጋር ዋና አስተዳዳሪ ና ፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ በተገኙበት ሰፋ ያለ ውይይት አካሂደናል።
02/04/2025

23/07/2017 የኢንቨስትመንት ስራዎችን ለማሳለጥ ከአጋር አካላት ጋር ዋና አስተዳዳሪ ና ፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ በተገኙበት ሰፋ ያለ ውይይት አካሂደናል።

04/03/2025
የጣርማበር ወረዳ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት“ወረዳችንን ለማልማትና ኢንቨስትመንቱን  ለማጠናከር  ባለሀብቱ  መሬት አጥሮ  ከማስቀመጥ  ወጥቶ ወረዳውን  ለማልማት  ቁርጠኛ መሆን አለበ...
12/12/2024

የጣርማበር ወረዳ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት
“ወረዳችንን ለማልማትና ኢንቨስትመንቱን ለማጠናከር ባለሀብቱ መሬት አጥሮ ከማስቀመጥ ወጥቶ ወረዳውን ለማልማት ቁርጠኛ መሆን አለበት ተባለ፡፡”
የጣርማበር ወረዳ እና የደ/ሲና ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመነት ጽ/ቤቶች “ኢትዮጵያ ታምርት” በሚል መሪ ቃል የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፉን ችግር ለመፍታት ያለመ የንቅናቄ መድረክ አካሄዱ፡፡
የጣርማበር ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሣሙኤል መርሻ የተሻለ ወረዳና ከተማ አስተዳደር ለመፍጠር ኢንቨስትመንት ያለው ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ባለሀብቱ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ወረዳውንና ከተማችንን በጋራ ልናለማ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የደብረሲና ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ወንድምሲገኝ ማሙዬ የኢንቨስትመንት ዘርፉን ለማጠናከር ከተማችንን ለማልማት ባለሀብቱ መሬት አጥሮ ከማስቀመጥ ወጥቶ ወደ ስራ በቁርጠኝነት ሊገባ እንዲገባ በጥብቅ ያሳሰቡ ሲሆን የፀጥታው ችግር በኢንቨስትመንት ላይ ያሳደረው ተዕፅእኖ ከፍተኛ መሆኑንን አንስተው በችግር ውስጥ ሆነው ወደ ግንባታ የገቡ ባለሀብቶችን አመስግነዋል፡፡
በመድረኩም ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
በማጠቃለያውም የጣርማበር ወረዳ ዋና አስተዳደሪ እንደገለፁት የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ለመቀጠል ወረዳውን ብሎም ህዝቡን የሚጠቅም አምራች ኢንዱስትሪ መፍጠር የሁላችንንም ጥረት ይጠይቃል በማለት ሀሳባቸውን ገልፀዋል፡፡
የሰሜን ሸዋ ዞን ህብረት ስራ ማህበራት ተጠሪ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ዘነበ ሃይሉ በበኩላቸው የኢንቨስትመንት ዘርፉን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በማድረግ የሚመለከታቸው አካላት በጋራ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡
ከእዚህ በተጨማሪ ባለሀብቱ ከመንግስት ጋር በቁርኝት በመስራት ወረዳውንና ከተማዋን ከማሳደግ በላይ የስራ ዕድል ፈጠራው ላይ የድርሻችሁን ልትወጡ ይገባል በማለት አሳስበዋል፡፡

Address

Debre Sina

Telephone

+251116800750

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tarmaber woreda industry and investment group posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share