SBC Sidaamu Afoo

SBC Sidaamu Afoo SBC Hedote Luphiimira

ቦርዱ ሐሰተኛና አደናጋሪ ምርጫ ነክ መረጃዎችን ለመከላከል የሚያስችለውን ብሔራዊ ትብብር ይፋ አደረገየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በያዝነው ሣምንት በምርጫ እና በድኅረ ምርጫ ወቅት ሊፈጠሩ ...
20/02/2026

ቦርዱ ሐሰተኛና አደናጋሪ ምርጫ ነክ መረጃዎችን ለመከላከል የሚያስችለውን ብሔራዊ ትብብር ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በያዝነው ሣምንት በምርጫ እና በድኅረ ምርጫ ወቅት ሊፈጠሩ የሚችሉ ምርጫ ነክ ሐሰተኛና አደናጋሪ መረጃዎችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የሚያስችለውን የብሔራዊ ትብብር ስምምነት ይፋ አደረገ። የይፋ ማድረጊያው መድረኩን የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በንግግር የከፈቱት ሲሆን፤ በንግግራቸውም የትብብር ማዕቀፉ ቦርዱ መጪው ምርጫ ነፃ እና ተዓማኒ እንዲሆን ምርጫ ነክ መረጃዎች ተዛብተው እና አሳሳች ሆነው ለኀብረተሰቡ እንዳይቀርቡና 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተዓማኒነት ተጠብቆ እንዲከናወን ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራበት ነው ብለዋል።

ቦርዱ ምርጫን በገለልተኝነት፣ በነፃነትና በታማኝነት ለማካሄድ የተቋቋመ ሕገ-መንግሥታዊ ተቋም መሆኑን ያስታወሱት ሜላትወርቅ፤ የትብብር ስምምነቱ ቦርዱ ሐሰተኛ እና አደናጋሪ መረጃዎችን በመከላከል በምርጫው ሂደት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንዳያደርሱ የሚያደርገውን ጥረት በእጅጉ እንደሚያግዝ ተናግረዋል። የብሔራዊ ትብብር ስምምነቱ ዐላማ በምርጫ ሂደት ሊሠራጩ የሚችሉ ሐሰተኛ መረጃዎችን ለማጣራት፣ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት፣ መራጮች እና በምርጫው በቀጥታ እና በተዘዋዋሪ ድርሻ ያላቸውን ተቋማትና ግለሰቦች በተዛባ መረጃ ላይ ከተመሠረተ ውሣኔ አሰጣጥ እንዲጠበቁ ለማድረግና ምርጫው ነፃ እና ተዓማኒ መሆኑን ለማረጋገጥ ያለመ ነው።

ከተባበሩት መንግሥታት የልማት ድርጅት (UNDP) ጋር በመተባበር በተዘጋጀው በዚኽ መድረክ ላይ የልማት ድርጅቱ የአፍሪካ ተወካይ የሆኑት ሳሙኤል ዶ (ዶ/ር) የጥላቻ ንግግር እና ሐሰተኛ መረጃ የምርጫን ተዓማኒነት አደጋ ላይ ከመጣልም በተጨማሪ ግጭት የሚያስነሱ እንደሆኑ በመግለጽ፤ ኢትዮጵያ ለ7ኛ ጊዜ የምታካሂደው ጠቅላላ ምርጫ ተዓማኒነቱ የሚረጋገጠው በምርጫ ጣቢያ ከሚተገበረው የምርጫ ሂደት በተጨማሪ ለዜጎችና በምርጫው ተሣታፊ ለሆኑ ግለሰቦችና ተቋማት በሚደርሰው እውነተኛ የምርጫ መረጃ ነው ብለዋል።

በመድረኩ ላይ አጠቃላይ የብሔራዊ ትብብር ሥራው ዕቅድና ተጠባቂ ውጤትን የተመለከተ ገለጻ ተሰጥቶበታል። የሌሎች ሀገሮች ተሞክሮዎችም ቀርበው እንዲሁ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

For English readers use the link: https://nebe.org.et/en/node/1251

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዲስ ዓርማን መረቁ******************የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በሐዋሳ ከተማ በተለያዩ ወታደራዊ ዝግጅቶች መከ...
20/02/2026

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዲስ ዓርማን መረቁ
******************

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በሐዋሳ ከተማ በተለያዩ ወታደራዊ ዝግጅቶች መከበሩን ቀጥሏል።

በዝግጅቱ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላን ጨምሮ ከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮች ፣ የሲዳማ ክልልና የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች የሀይማኖት አባቶችና የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

በዕለቱ የክብር እንግዳ ሆነው የተገኙት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የዕዙን አዲስ ዓርማ መርቀዋል።

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ በዚሁ ወቅት፤ አዲሱ ዓርማ የዕዙን የጋራ ዓላማና የመንፈስ ጥንካሬ የሚያሳይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ዓርማው የዕዙን የልብ ትርታና ዝግጁነት የሚያንጸባርቅ መሆኑን ገልጸው፤ የታሪክ ማህደር ከመሆን ባለፈ ለዕዙ የግዳጅ መነሳሻ ሆኖ ያገልግላል ብለዋል፡፡

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የኦፕሬሽን ምክትል አዛዥ ሜጄር ጄኔራል አበባው ሰይድ፤ ዕዙ በተለያዩ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ በማለፍና በደምና በአጥንቱ ሀገርን በማፅናት ታሪክ የጻፈ የሠራዊቱ የጀርባ አጥንት መሆኑን ገልጸዋል።

በዓሉን ስናከብር ያሉትን ጥንካሬዎች ይበልጥ ለማጉላትና ድክመቶችን በማረም፣ ተቋሙ ለሚሰጡት ማንኛውም ግዳጅ በላቀ ዝግጁነት ላይ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

በዝግጅቱ ላይ የዕዙን ታሪካዊ ጉዞና ወቅታዊ ቁመና የሚያሳዩ የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ ዶክመንተሪ ፊልም እና የተለያዩ ወታደራዊ ትጥቆች ለጎብኝዎች ቀርበዋል።

የምሥረታ በዓሉ የጀግኖችን ታሪክ ለትውልድ ለማሸጋገርና ሰማዕታትን በመዘከር እየተከበረ እንደሚገኝ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

የሲዳማ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ማርቺንግ ባንድ ‎የመከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ኛ አመት የምስረታ በዓልን አስመልክቶ የጎዳና ላይ ትርኢት አቀረበ‎‎የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያ‎ሀ...
20/02/2026

የሲዳማ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ማርቺንግ ባንድ ‎የመከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ኛ አመት የምስረታ በዓልን አስመልክቶ የጎዳና ላይ ትርኢት አቀረበ

‎የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያ
‎ሀዋሳ፣
‎የካቲት 13/2018 ዓ.ም

‎ማርቺንግ ባንዱ በከተማዋ መነሻውን ሱሙዳ አደባባይ አድርጎ በተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር ነው ትርዒቱን ያቀረበው።

20/02/2026
22/01/2026
11/01/2026

ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1133/2011 እና በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ስነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሰረት የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመመዝገብ ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡

በዚሁ መሰረት እነ ዓለሙ ጨእቾ የሲዳማ ራሽናል ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ሲራዴፓ) ወይም Sidama Rational party በሚል ስያሜ ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ያቀረቡ በመሆኑ በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 68 ንዑስ አንቀጽ 2 እና 3 መሰረት በፓርቲው ስም፣ አርማ ወይም ሌሎች ጉዳዮች ተቃውሞ ያለው ሰው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከዛሬ ጥር 03/2018 ዓ/ም ጀምሮ በ14 ቀናት ውስጥ ተቃውሞውን ለቦርዱ ጽሕፈት ቤት እንዲያቀርብ ያሳስባል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

11/01/2026
10/12/2025
06/12/2025

Address

Hawassa, Sidama
Hawassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when SBC Sidaamu Afoo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share