Muhibin

Muhibin ���ISLAMisTHEwayOFlife����

15/10/2023

ስለ ስግብግብነት ምን ትላላችሁ

06/09/2022

የነቢ ዘነ!!!!

ጠንቋይ ተጢበኜ ተደበሉወ አገ
ኢጌብሩያነይ ሼጣን በሰብ ክፍከ አዘገ
ኸልቂ ተጫጬጠ
ተወኩል ቀበጠ ኢማንከ ለገገ
ያኙይ ጩቡ ሹፍሮ ኢማን አጦለገ
አዘሪ አጡናናገ።
የጠንቋይ ሉክተኜ
የጢቢ ኩቱበኜ
ኢነብሪያን መሰሊየ ኡለግን በዱኒየ
አናወረ ቲበል ቲኢም ጋረዱኒየ
ቲያክባብሩይ ቲያሽበባብሉይ አንገት ወረዱኒየ
በአራረ በሺሊለ አውሊኸ አረዱኒየ
ኢሄተንኩ ሼካ
በኧልባ አውጣይ ሽካ
አዉሊያይ ኢወርዳን አያኒ ኢቴራን
በማድ በሱጢ ተጥቋኣስ ከተራን
ላለብከ አይኒናስ
ላይነቸኸ ቁስቋስ
ከተራን ተጥቋኣስ
ያሟቲ የሟቺ ኢንከ ኢትከፈታን
በዱኧ ባሚንታን ቢርቅ በጀባታን
አያሚ ሊቤዠኸ ላይነቸኸ ገፍለ
ጀበ ጀበ በለኝ ኢርቅ ቃወ አትፊለ
ከችፍ ቲጨጭኒ ዋሪደ ጎፍለለ
አሁም ክነበለ
አሮት በምኜቲየ ብርዛዝ አንዤውንከ
ምን የባለይ በለኝ ኢቤዣሃን ሬርከ
ከሳይሞር ገሪበት ሳንቸ ቡሸ ቡኧ
ቁሪየት አንኩረ ጤምቡኧ
መሶ ላይረህበኸ ውኸበ ለዱኧ
ለአድባርወ ለኡጥቢ ኒይተይ ሰደኧ
የትወለደይ ግልግል ለአያና አትናገ
ቲሜችት ትጎሪያ ግንቦት አድ ነገ
ሬርከ እልቤዠኸ የትማሃትከይ አትልገ
ያተይ ሀጃ ሊወጭ አላህ ሊያገረይ
ኮርቤሻይ ሞፈኒ ተማሃት ልትጎረይ
የዉን መርሃባ
ያሰብኩይ በሳከኝ ያውጄ አይዶ መኸረ
አዲየ ዮበህማው ሙክት ሞፈን ባረ
ጤፈረ ኤንዘይመ የሸር ኢስቲቃመ
በዋሪደ በከችፍ ባያን በከራመ
መሷ ያጠፍንካው በዱኧ በቂመ
ሀጃ ኢወጫን አመ
በኣመ ......በቃመ።
ሊሄ ዋበኝ ሀጃ
ኢሜልንካው ፉጃ
ቲበለይ ዴለለ
ሺሊለ ሺሊለ
መርሃባ ሺሊለ
ተገዚየ ቲካድሚ ለፎኧረ ጮሌ
ቲያበስቂ አድባር ጨሌ
ቹሉሌ መንጨሌ
ቅወ ቀድር ዋቡየ ለሲን ለጀበነ
ቲያሰክኒ ቲጌብሪ ለአያን ለኧሪነ
ለጂንወ ለሼጣን ቲጎሩኒ ደነ
አበሮስ ጨኘቲ ዉሙርከ ሊል ፈዴ
ላረሺ ሊኒናስ ሰኧሊየ አንደዴ
እነ ነር ንብሪ ሆይት በውለል ማዴ።
ቱጉጉፍት ኖኤቲ
ላይናዘርን ሞቲ
ጭሎ በኡሳኣሰይ ፉርጥምግዝ በትኖተ
ዱሚ በፈለጠይ ቀልምግዝ ባትኬተ
ገድ ዕጠኽ ቲሲል ኪታብ አትኬፈተ
አይብ እሎበብ በባቲ
ላምቴ በትናጠብቲ
ነቼታን አረሺ
ደዊሸ !!
በኪታብ አትኪሺ
ልታልቢ ታትጋጂ
ለኧርሸ እርዝ አቲጂ
ለሙኣሙእ አራስ ብረት በለሜሸ
ሼጣን ላይለክፌተ ቲያድጎብሊ አሜሸ
ጎሎዶ ኤንዜተ ትትወጭ ለሹማንሸ
ቀመሌ አስማደ ኡፉር ቀኚ ቆጬ
አያሚ ደረእን ዉንፍ ኤለይን አንጬ
ቡስቅ አያም ገድ አለይ
ተጡፊ ያሰልጣን
ፈየ ገቢየ ያኤጣን
ደረእ አያም ጡፊን ኤንዙይም ያትቄብጣን
እነ ነር ንብሪ በአላህ ያትቄንጣን።
ኢሼዢያን ኢልም ኤውዲያን አሊም ቻይ ታይቀብጥ
ንብር ተሽባበኸ ደለ የዲንከ ሸርጥ
እለፎት ተጮኚየ በዲን በኢማን ቀርጥ
ሊንጣቢትከ ቅንጣፍ ለአንገትከ የደመርጥ
የጅህልነ ዘማን ኢልቢስ ባለ አደረ
ሰቢ ተሽናወጠ በሽርክ ቴንጠረ
በኦሉይ በጄሩይ ቅልፈት ቁነጠረ
ለአድባር ላውጋር ለኡጥብ ቲፍነጭኒ ሳፍረ
ሊንጬ ለመከዞ ለኦቶ ለኡበ ለሸህለ ጌበረ
ኢልም አሊም ገፈሪየ ቲካድሚ ፉእረ
እሴቼ ቲያንጣል ላግዳደ መከዞ
ለችካል ለማጋል ቲያኣኑኒ ጠዞ
ጨሌነይ ቲያበስቂ አቱጣጢየ ሜዞ
እነ ነር ንብሪ ረሲየ የአላህ ኖዞ።
የተውሂዲ ኡንገ የሱናይ ሙረበ
ዛሂር ላይትቤየን አለበሱየ ጨበ
በአክላፍ በኢክላፍ ቲያድናህለይ ጪንበ
ስነበተ ነበር አትቄበጡየ ጠንበ።
ቁርዓንወ ሀዲስ በሸርጥ ተዌጠነ
በሰተተይ ኡንገ በነቢነይ ዘነ
በሱናይ አትፋዛት ጥርመቼ ሜዘነ
አኦዲየ ሊያልፍቢ በኧልብ አትማዘነ
አቤዢየ አእማመጢየ አንሰሲየ አረሲየ
አፍታቲየ አሞጠሊየ ላይረስ አቴከሲየ
ያትሬከቡይ ተውሂድ ቢዳኣ አለበሲየ
ኢነብራን ጨኘቲ ዲንከ ሽርክ ወረሲየ
የገወ ሰብ መርከ የኧበጠ ኤጀነ
የአኼረ ንብር መሰሊየ አውጄነ
በመህሉእ ኢጦእሳን በሰብ ተሜጀነ።
መገን መጀን ቡኸ ለምን ? በአላህ ሊያጄጀነz?
በመህሉእ ኢጦእሳን በሰብ ተሜጀነ።
በነሻጠ ስበብ አንኩም በፈልዳሰ
የአላህ ሉክተኸ ዋጅብ ፈርደ ረሰ
ነብሰኸ ኤዘዝተዪ ነብሰኸ ፌሰሰ
የዲኒ ሸርጠኸ አርካንከ የዳሰ
ኡሃተን ሚያሞ /ዱሚኸ የትቀረሰ።
የሰብ ወልድ አእልከ ባንጠረ
በጅህልነ ቅበት ቴንጠረ
ተገዛት ኢቢሳን በኤረ
ግብስብስከ ብዢን ዉንገ በገፈረ
ሊሊመን ነቢ ኢሳነ ጎይተ አኜያኒ የጠረ
ኢገርማን ያጅባን የሰብ ብል
ነቢዩ ባለኩይ የዲን ቃል
ነቢዩ ባኙይግዝ የዲን ብል
ስንኳን አነሰኸ ልደብል
የቴዘዝከሚ እታኝ በሙል ሙል
አላህ በራህመትከ ኢቲምከ
ኡኸ ኤዤየ ቤንዘንከ በመቅቡል
ጩጥንከ ኤንዜኸ ብል ቁቡል
ደኢፍወ ጩጥንከ መይ ኩንቡል
የዲኒ ሚያሞ ቅልጥሚወ ብርኪ
ቁርዓንወ ሀዲስን በሀቅ መሳኪ
በቃ የደፈንከ ሽርኪ እደገ
በይ ነኸ ሊለፍነ በነቢኘ ኡንገ (ሰዐወ)
የአላህ የነቢ ሉክት የሁን በል ተኢበል
ነቢ በባሉይ ግዝ በስርም አድበል
ታችል በደላሃ ትችለይ ተክነበል።
ዲኒይ ባዳዳልከ አቂዳይ ትችለይ
ማነምግን ጎይተኘ ቢፈርክም ቲቻለይ
ስርም አይቀራን ሱል ኢሲልቢያን ኤት አለይ።
እነ አያም ያሟትን
እነ አያም ሰንበትን
እደግ የደፈንከ እነይ ገውነትን
ጉርተ በወደኧ በጋር ወይ በእበት
በጎይታ ተዊከል አታክብር ሰንበት
ለሰብ አትትማሃት በሰብ አትትማሃት
ያላህ ቀደ ትትቀርብ ብትደፍም ቡንባት
ያኜኸይ ጡፊ ብል ያትቄብጣሃን አሃት
በአላህ ያሻረከ ኤለይ ባሊ ምራት
ሀጂየ ኢወጫን ባሃ በነሻጠ ስጀን
መህሉእ ተኬከምከ አትበል መገን መጀን
ለከሼኸይ ሀጃ አላህነ ተሚጀን
ውንጋይ ብዢን ባሊ በደበ የትቅጣጠፈ
እሶክወ ጉፊቾ ጉርም ተኦርፋፈ
ስርጥ ቀራንቀሮ በዘቢየ ተጨራፈ
ኤለኮ ኤድባን ባሊ ቻሊየ ላላለፈ
አድናናገራኒ ታይጢለኸ አጥላፈ
ተናናወርካኒ ታትቀር እንጅ ጎፈ
የነቢነይ ዘነ አድግፈር ኢንቅፈ።
ያረቢ አደራ አኘኝን ኡንቁፈ
ምንም ብሊየ ቢቦዥ አታውጣኝ አትግፈ!!

06/09/2022

ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር በሀሰተኛ ሰነዶች ዙሪያ የተሰጠ የዜና መግለጫ

ሰዎች የማይገባቸውን ጥቅም ለማግኘት በማሰብ ወይም የማይገባቸውን አገልግሎት ከመንግስት ወይም መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ለማግኘት የተለያዩ እውነተኛ ያልሆኑ መረጃዎችን የያዙ ሰነዶችን ሲያቀርቡ ይስተዋላሉ፡፡ በተለይም ሀሰተኛ የማንነት መታወቂያ፣ የጋብቻ ፣ የልደት፣ የሞት፣ የትምህርት እና የስራ ምስክር ወረቀቶች፤ የውክልና ምስክር ወረቀት፣ የህክምና ማስረጃዎች፣ የባንክ ሲፒኦ፣ ቼኮች፣ የአሽከርካሪ ፈቃድ፣ የፍርድ ግልባጭ ወዘተ በስፋት ጥቅም ላይ ከሚውሉ ወይም በሀሰት ከሚዘጋጁ የሰነድ አይነቶች የተወሰኑት ናቸው፡፡

እኚህን እና ሌሎች ሀሰተኛ ሰነዶችን ማዘጋጀትና መገልገል በሀገር ኢኮኖሚ እንዲሁም በዜጎች መብትና ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርስ የወንጀል ድርጊት ነው፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር የወንጀል ህጉን ከማስከበር እና የህግ የበላይነትን ከማረጋገጥ አኳያ እያከናወናቸው ካሉ በርካታ ተግባራት መካከል አንዱ ሀሰተኛ ሰነድን አዘጋጅተው ወይም ተገልግለው በሚገኙ ሰዎች ላይ የህግ ተጠያቂነትን ማስፈን ነው፡፡ በዚህም መሰረት ሀሰተኛ ሰነዶችን ባዘጋጁ እና በተገለገሉ አያሌ ሰዎች ላይ ክስ በመመስረት እንዲቀጡ ማድረግ ችሏል፡፡ ይሁንና ከጊዜ ወደ ጊዜ ሰነዶቹ የሚዘጋጁበት መንገድ እየዘመነ መምጣቱ በመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ውስጥ የሚስተዋለው ቸልተኝነቶች ተጨምሮበት ወንጀሉ ከመቀነስ ይልቅ እየተበራከተ እንዲመጣ አድርጎታል፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙዎች የማይገባቸውን ጥቅም አግኝተዋል፤ በመንግስት እና የህዝብ ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወደዚህ ደግሞ ህግን በሚያውቁ የሕግ ባለሙያዎች ሳይቀር ሀሰተኛ ሰነዶች ጥቅም ላይ እየዋሉ መሆኑን ከወራቶች እና ከቀናት በፊት ክስ መስርተን ወደ ፍርድ ቤት ያቀረብናቸው ጉዳዮች ዋቢ ናቸው፡፡ ይህ መሆኑ ጉዳዩ ምን ያህል አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን ያመላክታል፡፡

በመሆኑም ፍትሕ ሚኒስቴር፡-
•የማይገባቸውን ጥቅም ለማገኘት ሀሰተኛ ሰነዶችን በማቅረብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን የሚያታልሉ ግለሰቦች ከዚህ አይነት ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ፤

• በሀሰት የተዘጋጁ ሰነዶችን በዝግጅት ሂደት ላይም ይሁን ለአገልግሎት መቅረቡን ያየ ወይም ያወቀ ማንኛውም ግለሰብ በአቅራቢያ ለሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ የበላይ ኃላፊ ጥቆማ እንዲሰጥ፤

• ተቋማት ለተገልጋይ የሚሰጡት አገልግሎት በትክክልም ለሚገባው የተሰጠ መሆኑን የሚያረጋግጡበትን አስተማማኝ ዘዴ እንዲያለሙ እና እንዲተገብሩ፤

• የፍትሕ ተቋማት (የዐቃቤ ሕግ ተቋማችንን ጨምሮ) የሚቀርቡላቸውን ጥቆማዎች እና ክሶች በተገቢው በማስተናገድ ሀሰተኛ ሰነድ መርገጫ እንዲያጣ የማድረግ ኃላፊነታችውን እንዲወጡ፤

• ተቋማት ሀሰተኛ ሰነዶችን በመፍጠር፣ ወይም በመስጠት ወይም ሰነዶችን በተገቢው የማጣራት ኃላፊነታቸውን ሳይወጡ ከወንጀለኛ ጋር የሚያብሩ ሰራተኞች ላይ ተገቢውን የክትትል ስርዓት ዘርግቶ እርምጃ በመውሰድ ከፍትሕ ጎን እንዲቆሙ ይጠይቃል፡፡

ነሃሴ 30 ቀን 2014 ዓ.ም
የኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር

05/09/2022
05/09/2022

05/09/2022

ማን ናቸው?
ትምህርትቸውን የትከታተሉት ከ ታላቁ ወለኔ ዘንድ ነበር. ።

ኢማም ሐሰን ኢንጃሞ በ1880ዎቹ መጀመሪያ ግድም በሰባ ቀቤና የተወለደ የሙስሊም ሀዲያ መሪ ነበር። እናቱ የጉራጌ ተወላጅ ስትሆን አባቱ ዋልጋ ሞቼ በእነሞር የሀዲያ መሪ ነበር። ታሪክ እንደሚነግረን የሐሰን ኢንጃሞ ወላጅ አባት ዋልጋ በ1830ዎቹ ዘና በነር ወደተባለ ቦታ በመሰደድ ዑመር ቤኬሳ እና አሊ ደነቦ ከተባሉ ሁለት ጉራጌ (ሲልጤ ናቸውም የሚሉ መረጃዎች አሉ) የእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር በመሆን ከሁለት የቀቤና እስላማዊ መንግሥትን አቋቁመዋል። በዚህ ጊዜ ዋልጋ ዑመር ቤኬሳን የአዲሱ የቀቤና ኢስላማዊ መንግሥት ኢማም አድርጎ እርሱ የኢማሙ ረዳት እና ቃል አቀባይ ሆነ። የቀቤና መንግሥት በዋነኝነት በሀዲይኛ ቋንቋ ተናጋሪ ማህበረሰብ የበላይነት የተያዘ መንግሥት ነበር።
ሐሰን ኢንጃሞ በልጅነቱ በእነሞር በአባቱ በተመሰረተው መስጊድ፣ ከዛም በቀቤና እና አምበልታ ( ) ከታዋቂው ዘንድ ትምህርቱን ተከታትሏል። የአሊ ደነቦን የሚስት ልጅ ያገባው ሐሰን ከአባቱ ሞት በኋላ በአባቱ እግር ተተክቶ የዑመር ቃል-አቀባይ ሆነ። በሐሰን ኢንጃሞ የሰላሳ ዓመታት የሥልጣን ቆይታ የቀቤና መንግሥት እጅጉን እንደተጠናከረ ነው ታሪክ የሚያወሳው። በዚህም መሰረት ከምስራቅ እስከ ምዕራበ ከሰሜን እስከ ደቡብ በሚደረገው የንግድ እንቅስቃሴ ቀቤና አንደኛዋ የንግድ ማዕከል ሆነች። ከዚህም ሌላ አዳዲስ መስጊዶችንና ኢስላማዊ ትምህርት ቤቶችን በመክፈት ብዙ ታዋቂ የሙስሊም መንፈሳዊ ምሁራንን መሳብ የቻለች መንግሥት ሆነች ቀቤና።
ዑመር ቤኬሳ ለሸዋው ክርስቲያን ንጉሥ ምንሊክ ለመገበር በ1867 ዓ.ም. ተስማማ። በዚህም ስምምነት መሰረት ዑመር ከንጉሡ የደጃዝማችነት ማዕረግ ሲያገኝ ሐሰን ኢንጃሞን ግን አስቆጣው። ለሸዋው ክርስቲያን ንጉስ ለመገበር መስማማት ኢስላምን መካድ ነው ሲል ዑመር ለጦርነት ተዘጋጀ። በዚህም መሰረት ለረዥም ጊዜ በንግድና በእስልምና ካፈራቸው ወዳጆቹ ከወሎ፣ገደባኖ፣ ከወለኔ፣ ከጂማ ፣ ከአርሲ ከሱዳንም ሳይቀር እርዳታ አግኝቷል። በተለይም የቀድሞው መምህሩ # ሼህ አብዱለአዚዝ ዘመቻውን በማስተባበር በኩል ትልቅ ስራን መስራታቸው ይነገራል። በ1870 ዓ.ም የአጼ ዮሐንስን የግዴታ ክርስትናን ተቀበሉ ትዕዛዝ እምቢኝ ብለው በሼህ ዚዪን እየተመሩ ቀቤና የደረሱት ሙስሊሞች የሱዳን ማህዲስቶች ማበረታቻ ለሐሰን ኢንጃሞ የልብ ልብ ሰጡት። ከዚህ በኋላ ሐሰን ኢንጃሞ ወደ ወለኔ በማቅናት ከሼህ አብዱልአዚዝና ሼህ ዚዪን ጋር መከረ። በምክራቸውም መሰረት ጂሀድ ለማወጅ ተስማምተው ወደ ጋርባጃ ኮረብታ ዚያራ አደረጉ።

በ1870 ዓ.ም ሐሰን ኢንጃሞ ዑመር ላይ ጦርነት ከፈተበት። የሐሰንን ጦር መቋቋም ያልቻለው ዑመር ሲሸሽ፣ ንብረቱ የሚዘረፈው ተዘርፎ የተቀረው ወደመ። ምንም እንኳን ዑመር ከወለኔ፣ ሙኸር፣ ጉመር እና ቸሀ በመታገዝ ሐሰን ላይ የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ ቢከፍትም ሳይሳካለት ቀረ። በዚህ ድል ምክንያት ሐሰን ኢንጃሞ የቀቤና መንግሥት ቁንጮነቱን ማረጋገጥ ችሎም ነበር። ከዚህ በኋላ የሐሰን ኢንጃሞ እንቅስቃሴ የነበረው በዑመር ቤኬሳ ዘመን ተበርዟል ያለውን እስልምና ማጽዳትና ለሸዋው ንጉስ በገበሩት ጎረቤት መንግሥታት ላይ ዘመቻ መክፈት ነበር። ሐሰንን ለማግባባት የዲፕሎማሲ ሙከራዎችን አድርጎ ያልተሳካለት የሸዋ መንግሥትም የሐሰን ኢንጃሞን ጦር ለማንበርከክ በቀኛዝማች ውቤ አርጃኖ፣ ደጃዝማች ወልዴ አሻጋሪ እና በባሻ ሀብተሥላሴ የተመራ ጦር አዘመተ። ነገር ግን ሐሰን ኢንጃሞ በቀላሉ የሚሰበር ሰው አልነበረም። የሸዋውን ጦር ድል በመንሳት ሰባት ቤት ጉራጌን እና አክሊልን ተቆጣጥሮ ዑመር ቤኬሳን በቁጥጥሩ ስር አዋለ። ከዚህ በኋላ ለሐሰን የገባው ዑመር ቤኬሳም የሐሰንን ዘመቻ በመቀላቀል በሰባት ቤት ጉራጌ እስልምና እንዲስፋፋ ሲደረግ ባህላዊ አምልኮዎችና የአምልኮ ስፍራዎች እንዲወድሙ ተደረገ። በዚህ ጊዜ እስልምናን ተቀብዬ የአባቶቼን ባህላዊ የአምልኮ (ዋቅ) ስረዓት አልተውም ብሎ ያመጸው ሳራሞ ጋቼኖ በያበዜ በህዝብ ፊት እንዲገደል ሲደረግ፣ ክርስቲያኖቹ መኸሮች በእቸኔ እና በያሚናን ደም አፋሳሽ ውጊያ አድርገዋል። በመጨረሻው ግን ድሉ የሐሰን ኢንጃሞ ሆነ።
ታላቁ የሀዲያ-ጉራጌ የጂሃድ ዘመቻ ከአርሲ ኦርሞ ኃይል ጋር በመተባበር ለሸዋ መንግሥት ከፍተኛ የራስ ምታት ሆኑበት። ምንም እንኳን በ1878 እና 80 በደጃዝማች ወልዴ አሻጋሪ የተመራ ጦር እንደገና ቢዘምትም ድል ሊቀናው ግን አልቻለም። ወሊቆ ላይ በተደረገ ውጊያ ድል በድጋሚ የነሐሰን ኢንጃሞ ሆነ።
በመጨረሻም ንጉሥ ምንሊክ ታላቁን ጦራቸውን በራስ ጎበና ዳጨ መሪነት አዘመቱ። በወሊሶ አቅራቢያ ጀቢዱ ሜዳ ላይ በሐሰን ኢንጃሞ የሚመራውን የተባበረው ሙስላም ጦርን የገጠመው ራስ ጎበናም ድል ሲቀናው ሐሰን ኢንጃሞም ወደ ጂማ ሽሽት ጀመረ። በዚሁ ጉዞ ላይ እያለም ጊቤን ሲሻገር በወባ በሽታ ተጠቅቶ ሰባ ሲደርስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። የሐሰን ኢንጃሞ አስክሬን ያረፈውም በቤተሰቦቹ የቀብር ስፍራ ላይ ነበር

ኮኪር ሚዲያ
ዶር ሰለሀዲን

ምንጭ https://www.sewasew.com/p/

ብራቮ ቭላድሚር ቡቲን የድሀ አገሮች አለኝታ
04/09/2022

ብራቮ ቭላድሚር ቡቲን የድሀ አገሮች አለኝታ

እንደ ሩሲያ አውሮፓዊያንን እየተጫወተባቸው ያለ ሀገር የለም !

በጣም በሚገርም ሁኔታ የአውሮፓ የኢኮኖሚ ህልውና በሩሲያ መዳፍ ውስጥ ገብቶ ሩሲያ እንደፈለገች እያወዛወዘቺው ነው ቢባል ማን ያምናል ?

ጀርመንን የመሰለች የአውሮፓ የኢኮኖሚ ቁንጮ በአለምም አራተኛዋ ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ የመፀዳጃ ሶፍት ለማምረት ጭምር ጭንቅ ውስጥ እንደሆነችስ ማን ያምናል ?
እንግዲያውስ ነገሩ በእውኑ ተከስቷል ።

ቁማርተኛው መሪ ቭላዲሚር ፑቲን አውሮፖችን ቀላል ቆመረባቸው እንዴ !!??

ሩሲያ ዩክሬይንን ስትወር አውሮፖች እንደ አደገኛ ነገር አጫወታቸውና በሩሲያ ላይ የማእቀብ ናዳ ማውረድ ጀመሩ ። በቅሎ ማሰሪያዋን በጠሰች ቢሉ አሳጠረች እንዲሉ ለካስ አውሮፖች በሩሲያ ላይ ማእቀቡን ሲጥሉ በሩሲያ ላይ ሳይሆን በሪሳቸው ላይ ነበሩ እየጣሉ የነበሩት ። ራሳቸው ላይ ተኮሱ !

አሁን ሩሲያ በቀል ላይ ነች በቀል - አልኢንቲቃም አለ ሰአደዲን ኮቢክ 😁
እናም ሩሲያ አሁን ወደ አውሮፓ የምትልከውን ጋዝ ሙሉ በሙሉ ጥርቅም አድርጋ ዘግታዋለች - ሙሉ ለሙሉ ! የአውሮፓ ኢኮኖሚያ ማእበል እንደሚያናውጣት ጀልባ ከዚያ እዚህ እየተንገጫገጨ ነው ። የጋዝ ዋጋ በ በፊት ከነበረው በ 10 እጥፍ ጨምሮ አንዱ በርሜል 500 ዶላር ደርሶ ነበር አሁን ጨርሶ ሲዘጋ የት እንደሚደርስ መገመት አያዳግትም ።

ጀርመን አሁን ያላት ጋዝ ለማለቅ የሚፈጅበት ከ 3 ወር ያነሰ ብቻ ነው ። አውሮፓን ቀጣዩ እጅግ ብርዳማው የበጋ ወቅት አይኑን አፍጥጦ እየመጣላቸው ነው ። ካለ ጋዝ ያንን ወቅት ማለፍ አይቻልም ። ጀርመን ወይ ኢንዱስትሪዎቿን መዝጋት አለበት አሊያ ህዝቦቿን መስዋእት ማድረግ አለባት ።

ልብ በሉ !
የአውሮፓ መገበያያ ገንዘብ ዩሮ የቁልቁለት ጉዞውን ተያይዞታል ! የአውሮፓ የዋጋ ግሽበት የማይቀመስ ሆኗል ። ኢንዱስትሪዎቻቼው ለመዘጋት እየተዘጋጁ ነው ። አለምን የሚጠመዝዙባቸው የኢኮኖሚ ተቋሞቻቼው ሺባ ለመሆን እየተወላሸሹ ነው ። በማን የተባለ እንደሆነ በሩሲያ !

ማእቀብ ጣዮቹ በማእቀብ ሲቀጡ ማየት እንደት ደስ ይላል !
ብራቮ ሩሲያ ! ብራቮ ፑቲን !



ቴሌግራም
👉 t.me/Seidsocial

Address

ደቡብ ክልል ጉ/ዞን ወልቂጤ ከተማ
Wolkite

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Muhibin posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Muhibin:

Share