28/05/2026
ዘመቻ አንሻ ሰይድ በይፋ ተጀምሯል!
በግራራይ እና አቡነ ዮሴፍ ግንባሮች በተደረገ መጠነ-ሰፊ ፍልሚያ የአገዛዙ ጦር ክፉኛ ተመታ፤ እንጃፋት ከተማ ሙሉ በሙሉ ከጠላት ነፃ ሆነች!
የብልፅግና አገዛዝ ወታደራዊ መዋቅርና የምርጫ ማስፈጸሚያ ስልት በየቀጠናው በፋኖ ብርቱ ክንድ እየፈረሰ ባለበት በዚህ ወቅት፣ በሰሜን ወሎ ዞን በተቀጣጠሉ ሁለት አውደ ውጊያዎች ለአገዛዙ ሰራዊት መርዶ የሆነ ታላቅ ወታደራዊ ስብራት መገናኘቱ ታወቀ።
በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ስር የሚንቀሳቀሰው 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር፣ ዛሬ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም በግራራይ ግንባር እና አቡነ ዮሴፍ ሎጅ ግንባር በመግባት በወሰደው የተቀናጀና መብረቃዊ ጥቃት፣ በአካባቢው ሰፍሮ የነበረውን የአገዛዙን ጦር እንደ በረዶ አቅልጦታል።
ከዕዙ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተገኘው የፊት መስመር መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ውጊያው ከንጋቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ አመሻሹ 11:00 ሰዓት ድረስ ለሙሉ ቀን የቆየ ጽኑ ፍልሚያ ነበር።
የአገዛዙ ሰራዊት በመድፍ፣ በ107 ሮኬት፣ በዙ-23 ፀረ-አውሮፕላን መሣሪያ፣ በሞርተር 120 እና ሞርተር 82 የከበደ ሜካናይዝድ ታግዞ ምሽግ በመያዝ ብርቱ መከላከል ለማድረግ ቢሞክርም፣ የኮሩ አናብስቶች የጠላትን ስድስት ስልታዊ ምሽጎች አንድ በአንድ በመደርመስ የጠላትን ወታደራዊ ቅስም ሰብረዋል። በዚህ አንጸባራቂ ድል በተመዘገበበት አውደ ውጊያ ላይ የኮሩ 14ኛ፣ 16ኛ, 19ኛ፣ 21ኛ እና 30ኛ ክፍለ ጦሮች በግንባር ቀደምትነት ተሳትፈውበታል።
በዚህ መጠነ-ሰፊ ፍልሚያ የአገዛዙ ጦር እንጃፋት፣ ድልገን እና አቡነ ዮሴፍ ከተባሉ ይዞታዎቹ ሙሉ በሙሉ የተጠረገ ሲሆን፣ ስልታዊዋ እንጃፋት ከተማም ከአገዛዙ ሰራዊት ነፃ መውጣቷ ተረጋግጧል።
በዕለቱ የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ያስመዘገባቸው የድምሰሳ፣ የምርኮና የትጥቅ ስኬቶች ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦
♦️የሰው ኃይል ኪሳራ፦ 3 ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች እና 236 የሰራዊቱ አባላት (በድምሩ 239) ሙሉ በሙሉ ተሸኝተዋል፤ 46 የአገዛዙ ወታደሮች ደግሞ በምርኮኛነት ተማርከዋል።
♦️የተማረኩ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሣሪያዎች፦ 02 ድሽቃ፣ 03 ብሬን፣ 01 ስናይፐር እና 118 ዘመናዊ ጥቁር ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች በፋኖ እጅ ገብተዋል።
♦️የተማረኩ ተተኳሾችና የጦር ቁሳቁሶች፦ 3500 የብሬን ጥይት፣ 5400 የክላሽ ጥይት፣ 160 የድሽቃ ተተኳሽ፣ 26 የእጅ ቦምብ፣ 03 መገናኛ ሬዲዮ (ዎኪቶኪ) እና 74 የደረትና የወገብ ወታደራዊ ትጥቆች ተወርሰዋል።
የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ መዳረሻው ሙሉ ነፃነትና ድል የሆነው የአማራ ሕዝብ የህልውና ተጋድሎ በአስተማማኝ ሁኔታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጾ፣ በሌሎች ግንባሮች የተመዘገቡ ታላላቅ ድሎችንም በቀጣይ ቀናት ከቪዲዮና ከፎቶ ማስረጃዎች ጋር አያይዞ ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
ይቀጥላል!