EthioInfo

EthioInfo EthioInfo Media brings, social, economic, political and cultural issues to its audience.

የክፍለ ዘመኑ ታላቅ ፍልሚያ፡ መኮንን ላዕከ VS ደረጄ ኃይሌየጥበብ ሜዳው ጠቦአቸው ወደ ቦክስ ሪንግ ቢገቡ ማን ያሸንፋል?በቀኝ በኩል በሰላም ፈገግታው የሚታወቀው መኮንን ላዕከ በጥቁር ሾርት...
05/08/2026

የክፍለ ዘመኑ ታላቅ ፍልሚያ፡ መኮንን ላዕከ VS ደረጄ ኃይሌ

የጥበብ ሜዳው ጠቦአቸው ወደ ቦክስ ሪንግ ቢገቡ ማን ያሸንፋል?

በቀኝ በኩል በሰላም ፈገግታው የሚታወቀው መኮንን ላዕከ በጥቁር ሾርት፣

በግራ በኩል ደግሞ በትኩረት የሚመለከተው ደረጄ ኃይሌ በቀይ ሾርት ለፍልሚያ ተዘጋጅተዋል።

መኮንን ላዕከ ጥንካሬው፦

1.በፈገግታ እያታለሉ ድንገተኛ "የጥበብ" ጡጫ ማሳረፍ።

2.ተቃዋሚን በጨዋነት አዳክሞ በመጨረሻው ዙር በቃላት ውርጅብኝ ማንበርከክ።

ደረጄ ኃይሌ ጥንካሬው፦

1.ፈጣን እንቅስቃሴና የማይገመቱ የቀልድ ጥቃቶች።

2.ተቃዋሚን በሳቅ ሆድ አስባርቆ መከላከያውን ሲዘነጋ "የምር" ምት ማሳረፍ።

እናንተስ ማን ያሸንፋል ብላችሁ ታስባላችሁ?

1. መኮንን ላዕከ
2. ደረጄ ኃይሌ

(ጉርሻ page)

የነዳጅ ዋጋ ጨምሯል ?ቲክቫህ ኢትዮጵያ የነዳጅ ዋጋ መጨመሩን ተዘዋውሮ ባደረገው ቅኝት አረጋግጧል።ነጭ ናፍጣ በሊትር 180.46 ብር ገብቷል። ቤንዚንም በሊትር 167.50 ብር ሆኗል።ከዛሬ ሚ...
05/04/2026

የነዳጅ ዋጋ ጨምሯል ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የነዳጅ ዋጋ መጨመሩን ተዘዋውሮ ባደረገው ቅኝት አረጋግጧል።

ነጭ ናፍጣ በሊትር 180.46 ብር ገብቷል። ቤንዚንም በሊትር 167.50 ብር ሆኗል።

ከዛሬ ሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ መደረጉን ማደያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ደብዳቤ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋን መሰረት በማድረግ ከሚያዚያ 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽት 12:00 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሬ መደረጉን ያስረዳል።

በደብዳቤው በተገለጸው መሰረት በሊትር፦
- ነጭ ናፍጣ 180.46 ብር
- ቤንዚን 167.50 ብር
- ኬሮሲን 320.66 ብር
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ 170.62 ብር
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ 167.37 ብር
- የአውሮፕላን ነዳጅ 319.76 ብር ሆኗል።

በተጨማሪም ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ በቅሎ ቤት ፣ ሳሪስ አካባቢ ባሉ ማደያዎች ቅኝት ያደረገ ሲሆን፣ ማደያዎቹ ሽያጭ እያከናወኑ ያሉት በተሻሻለው ዋጋ መሰረት ነው።

የማደያዎቹ ሠራተኞች ቤንዚን 167.50 ብር፣ ነጭ ናፍጣ 180.46 ብር እየሸጡ፣ ሹፌሮችም በዚሁ መሰረት እየቀዱ መሆኑን አረጋግጠዋል።

በነዳጅ ምርቶች ላይ ከአንድ ወር በፊት የዋጋ ጭማሪ ተደርጎ ነበር።

አዲስ አበባ
ሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ/ም

🤯🤯 ቃሉፑቲክ በአንድ ወር INSTAGRAM ላይ 21 ቪድዮዎችን ብቻ ነው የሰራው ታዲያ በዚህ አንድ ወር ያገኘው የተመልካች ቁጥር እና ተከታዮች ለብዙዎች ከአእምሮ በላይ ሆኖባቸዋል! በ1ወር ...
05/03/2026

🤯🤯 ቃሉፑቲክ በአንድ ወር INSTAGRAM ላይ 21 ቪድዮዎችን ብቻ ነው የሰራው ታዲያ በዚህ አንድ ወር ያገኘው የተመልካች ቁጥር እና ተከታዮች ለብዙዎች ከአእምሮ በላይ ሆኖባቸዋል!
በ1ወር
21 ቪድዮ
3.4 ሚሊዮን ተከታዮች
995 ሚሊዮን እይታ
🤯🤯🤯

እኔ ነፃነት ወርቅነህ ነኝ የተወዳጁ ነፃነት ወርቅነህ ሐውልት ተመረቀ።
05/03/2026

እኔ ነፃነት ወርቅነህ ነኝ

የተወዳጁ ነፃነት ወርቅነህ ሐውልት ተመረቀ።

አንዲት እናት 4 አራት ህጻናት ወለደችወ/ሮ ጸጉ ተስፋይ ትባላለች። በትግራይ ግጀት ወረዳ ነዋሪ ስትሆን በአንድ ጊዜ 4 ህጻናትን በሰላም ተገላግላች። በትግራይ መቐለ ሆስፒታል ህጻናቱ በመልካ...
04/28/2026

አንዲት እናት 4 አራት ህጻናት ወለደች

ወ/ሮ ጸጉ ተስፋይ ትባላለች። በትግራይ ግጀት ወረዳ ነዋሪ ስትሆን በአንድ ጊዜ 4 ህጻናትን በሰላም ተገላግላች።

በትግራይ መቐለ ሆስፒታል ህጻናቱ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ።

🚨💚💛❤️ ኢቶሪካ ሪከርድ ሰባበረ 💚💛❤️🚨የቴዲ አፍሮ አዲሱ አልበም ኤቶሪካ ከ5 ቀናት በፊት ተለቋል። አሁን በዩቲዩብ ላይ ከ72 ሚሊዮን በላይ እይታዎች አሉት።በ22 አገሮች ውስጥ በመታየት ...
04/21/2026

🚨💚💛❤️ ኢቶሪካ ሪከርድ ሰባበረ 💚💛❤️🚨

የቴዲ አፍሮ አዲሱ አልበም ኤቶሪካ ከ5 ቀናት በፊት ተለቋል።

አሁን በዩቲዩብ ላይ ከ72 ሚሊዮን በላይ እይታዎች አሉት።
በ22 አገሮች ውስጥ በመታየት ላይ ይገኛል።
በ9ኙ ውስጥ #1፣ በ🇺🇸 #6

ይህ ምናልባት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ አርቲስት በዓለም አቀፍ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ ይህን ያህል እይታ ሲያገኝ የመጀመሪያው ነው።

የእድገት አካሄዱ፡

የመጀመሪያው ሰዓት፡ 15 ሚሊዮን እይታዎች
3 ሰዓታት፡ "ጀምበር" 1 ሚሊዮን ሰበረ (የኢትዮጵያ ሪከርድ)
24 ሰዓታት፡ 30 ሚሊዮን+
5 ቀናት፡ 72 ሚሊዮን
~14 ሚሊዮን እይታዎች በቀን። በአፍሪካ ውስጥ እንደዚህ በፍጥነት የተንቀሳቀሰ የአፍሪካ አልበም የለም።

ይህ ደረጃ አስደናቂ ነው

አሁን፣ በዩቲዩብ ላይ #1 በመታየት ላይ ያለባቸው ሀገራት (በአጠቃላይ፣ ሙዚቃ ብቻ አይደለም):
🇦🇪 የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ
🇧🇭 ባህሬን
🇮🇱 እስራኤል
🇰🇼 ኩዌት
🇳🇱 ኔዘርላንድስ
🇳🇴 ኖርዌይ
🇶🇦 ኳታር
🇸🇦 ሳውዲ አረቢያ
🇸🇪 ስዊድን
የአማርኛ ዘፈን። በቁጥር 1። ማንም ሰው ማለት ይቻላል አማርኛ የማይናገርባቸው አገሮች ላይ።

ግን ይህንን ታሪካዊ የሚያደርገው ይህ ነው።
የYouTube የሙዚቃ መተግበሪያ ላይ አሁን፡
🇨🇦 ካናዳ — #2 🇬🇧 UK — #4 🇩🇪 ጀርመን — #5 🇺🇸 US — #6 🇧🇪 ቤልጂየም — #6 🇦🇺 አውስትራሊያ — #7
ቴዲ የምዕራባውያንን የፖፕ ሙዚቃዎች በራሳቸው ሜዳ እያሳየ ነው።

የኢትዮጵያ ሙዚቃ ሁልጊዜ ነፍስ ነበረው። ሁልጊዜም ጥልቀት ነበረው። ሁልጊዜም ማንነት ነበረው።
አሁን መላው ዓለም እያጣጣመው ነው።
72 ሚሊዮን እይታዎች። 22 አገሮች። 5 ቀናት።
ይህ የኢትዮጵያ ጊዜ ነው።
ኢቶሪካ 🇪🇹

Via on X

32ሺ ሰው በ10$ አልበሙን ከገዛው ቴዲ ከሰዋሰው ቃል ተገብቶለት የነበረውን 50ሚሊ ብር ከአድናቂዎቹ ማግኘት ይችላል!Teddy Afro  #ኢቶሪካ አልበም ሊለቀቅ ሰአታት ነው የቀሩት ሰአታት...
04/16/2026

32ሺ ሰው በ10$ አልበሙን ከገዛው ቴዲ ከሰዋሰው ቃል ተገብቶለት የነበረውን 50ሚሊ ብር ከአድናቂዎቹ ማግኘት ይችላል!
Teddy Afro #ኢቶሪካ አልበም ሊለቀቅ ሰአታት ነው የቀሩት ሰአታት ብቻ ነው አሁን አንድ የቤት ስራ በተለይ ዳያስፖራ ለሚገኙ የቴዲ አፍቃሪያን ተዘጋጅቷል! ጉዳዪ ቀላል ነው! የቴዲን አልበም በተለይ Apple Music ላይ በሚሸጥበት $ ዋጋ በመግዛት በሰዋሰው ቃል የተገባለትን 50ሚሊ ብር በምስጋና እናቅርብለት!

Apple music መተግበሪያውን ያውርዱ በነፃ ለ1ወር ይመዝገቡ የቴዲን አልበም በ10$ ይግዙና ፍቅርዎን አድናቆቶን ይግለፁ!

የቴዲ አፍሮ ድምፅ እንደገና ታፈነ? መግለጫ እንዳይሰጥ ተደረገገና ሳይወጣ አነጋጋሪ የሆነው የ"ኢትዮሪካ" አልበም መግለጫ በድንገት ታገደ! ​በሚሊዮኖች ዘንድ በከፍተኛ ጉጉት ሲጠበቅ የነበረው...
04/13/2026

የቴዲ አፍሮ ድምፅ እንደገና ታፈነ?

መግለጫ እንዳይሰጥ ተደረገ

ገና ሳይወጣ አነጋጋሪ የሆነው የ"ኢትዮሪካ" አልበም መግለጫ በድንገት ታገደ!

​በሚሊዮኖች ዘንድ በከፍተኛ ጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን የቴዲ አፍሮ አዲስ አልበም "ኢትዮሪካ"ን አስመልክቶ ዛሬ ማክሰኞ (ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም) ሊሰጥ የነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ ባልታሰበ ሁኔታ ታግዷል።

​ከታማኝ ምንጮች እንዳገኘነው መረጃ ከሆነ፤ ቴዲ ይህንን ታሪካዊ መግለጫ ከተለያዩ ሚዲያዎች ጋር ሆኖ በቀጥታ ለማስተላለፍ ከአርትስ ቲቪ (Arts TV) ጋር ስምምነት ተፈራርሞ ነበር።

ሆኖም ግን በሚመለከታቸው አካላት በጣቢያው ላይ በተጣለ ድንገተኛ እና ጥብቅ እገዳ ምክንያት የቀጥታ ስርጭቱ ሙሉ በሙሉ ሊሰረዝ ችሏል።

​ገና አንድም ዘፈን ሳይለቀቅ ይህን ያህል ከፍተኛ ውጥረት እና መነጋገሪያ የፈጠረው "ኢትዮሪካ" ምን ሚስጥር ይዞ መጥቶ ይሆን? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል!
​ተጨማሪ አዳዲስ እና የተረጋገጡ መረጃዎችን እንደደረሱን በፍጥነት እናደርሳለን።

​የእርስዎ ሀሳብ ምንድን ነው? ከስር በኮመንት ያጋሩን!

በኮምቦልቻ ከተማ በመጪው እሁድ ሚያዝያ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የጋብቻ ስነ-ስርዓቷን ለመፈጸም በከፍተኛ ዝግጅት እና ደስታ ላይ የነበረች አንዲት ወጣት ሙሽሪት፤ ዛሬ ሰኞ በደረሰ አሰቃቂ የመ...
04/13/2026

በኮምቦልቻ ከተማ በመጪው እሁድ ሚያዝያ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የጋብቻ ስነ-ስርዓቷን ለመፈጸም በከፍተኛ ዝግጅት እና ደስታ ላይ የነበረች አንዲት ወጣት ሙሽሪት፤ ዛሬ ሰኞ በደረሰ አሰቃቂ የመኪና አደጋ ህይወቷ ማለፉ እጅግ አሳዛኝ እና ልብ ሰባሪ ሆኗል። ከዋሱ መሀመድ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ ይህ ዘግናኝ አደጋ የተከሰተው ከሎግያ ወደ ኮምቦልቻ በሚወስደው መንገድ “ወርሰይ” ተብሎ በሚጠራውና ለጉዞ እጅግ አስቸጋሪ በሆነው የመንገድ ክፍል ላይ ነው። ወጣቷ ትጓዝበት የነበረው ተሽከርካሪ ከቁጥጥር ውጪ ሆኖ ገደል ውስጥ በመግባቱ ምክንያት አደጋው የከፋ ሊሆን ችሏል። በአደጋው ወቅት በአካባቢው የነበሩ መንገደኞች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተጎጂዎችን ለማትረፍ ከፍተኛ ርብርብ ቢያደርጉም፤ ምስኪኗ ሙሽሪት ለህክምና ኮምቦልቻ ከተማ ከመድረሷ በፊት በዛው ህይወቷ አልፏል። የህይወቷን አዲስ ምዕራፍ በነጭ የሰርግ ልብስ ለመጀመር ቀናቶችን ስትቆጥር የነበረችው ይህች ወጣት በድንገት በሞት መነጠቋ፤ ቤተሰቦቿን፣ ወዳጅ ዘመዶቿን እና የሰማውን ሁሉ በከባድ ሀዘን ውስጥ የከተተ ክስተት ነው።

​በዚህ አጋጣሚ ለሟች ቤተሰቦች፣ ለትዳር አጋሯ እና ለወዳጅ ዘመዶቿ ሁሉ ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጥ እንመኛለን።

04/12/2026

በ2018 በ8ተኛው ወር በ8ተኛው ቀን በ8 ሰአት 18ዘፈኖችን ያካተተው ኢቶሪካ አልበም ሊለቀቅ ቀናቶች ብቻ ቀሩት! ሁላችሁም ዝግጁ? የቴዲ አፍሮን ኦፊሻል ዩቱብ ቻናል ሰብስክራይብ እያደረጋችሁ ምርጥ ምርጥ ዘመን አይሽሬ ሙዚቃዎቹን እየኮመኮማችሁ ጠብቁ

የብፁውነታቸው መልዕክትየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ፣ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማት...
04/11/2026

የብፁውነታቸው መልዕክት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ፣ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ የ2018 ዓ.ም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሣኤ በዓል አስመልክተው አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።

ቅዱስነታቸው ሚያዝያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ባስተላለፉት በዚህ መልእክት፤ በሀገር ውስጥ በገጠርና በከተማ ለሚኖሩ፣ ከሀገር ውጭ ለሚገኙ፣ የሀገር ዳር ድንበር ለሚጠብቁ፣ በሕመም ላይ ላሉ እንዲሁም በማረሚያ ቤት ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ ምኞታቸውን ገልጸዋል።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሞት ቅጣትን ሙሉ በሙሉ ሰርዞ ሰውን ነጻ ለማውጣት፣ ራሱ መሥዋዕት፣ ራሱ መሥዋዕት አቅራቢ ሊቀ ካህናት፣ እንዲሁም ራሱ ተወካፌ መሥዋዕት በመሆን በገዛ ፈቃዱ ራሱን አሳልፎ መስጠቱን ፓትርያርኩ በመልእክታቸው አስረድተዋል። የክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ድንገተኛ ሳይሆን ዓለምን ለማዳን በእግዚአብሔር አሠራር የተከናወነ መሆኑንም አብራርተዋል።

በአሁኑ ወቅት ዓለም በጨለማ ተውጣ እየተተረማመሰች የምትገኘው ከብርሃን ይልቅ ጨለማን በመምረጧ መሆኑን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አስገንዝበዋል። ከዚህ አኳያ ሕዝበ ክርስቲያኑ በትንሣኤው በማመን፣ በቅን አስተሳሰብና በርቱዕ አእምሮ በመታገዝ ጨለማውን ዓለም ወደ ብርሃን ለመለወጥ መትጋት እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል። ክርስቲያኖች የትንሣኤ ሰዎች በመሆን በመንፈስና በሞራል ማደግ እንጂ የጨለማው ኃይል መሣሪያዎች መሆን እንደሌለባቸውም ጠቁመዋል። አያይዘውም የጨለማው ዓለም መንፈስ ከማጥፋት ውጭ ስለማይጠቅም፣ የሰው ልጅ ብቸኛው አማራጭ ብርሃን የሆነውን እግዚአብሔርን መከተል መሆኑን አብራርተዋል።

ፓትርያርኩ መልእክታቸውን ሲያጠቃልሉ፣ ሕዝበ ክርስቲያኑ በዓሉን ሲያከብር ሊተገብራቸው የሚገቡ ተግባራትን አብራርተዋል። በተለይም ዓለም በክፋቱ ያጨለመባቸው ወገኖች ጦማቸውን እንዳይውሉ ማድረግ ክርስቲያናዊ ግዴታ መሆኑን በማስታወስ፣ ምእመናን ካላቸው ላይ ከፍለው የተራቡትን እንዲያበሉ፣ የተጠሙትን እንዲያጠጡ እና የታረዙትን እንዲያለብሱ መክረዋል። ሁሉም የዕለቱ ደስታ ተካፋይ እንዲሆን በማድረግ ቀኑ ለሁሉም ፍጹም ብርሃን ሆኖ እንዲውል ጥሪያቸውን በእግዚአብሔር ስም አስተላልፈዋል።

Address

San Diego, CA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EthioInfo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EthioInfo:

Share

Category