05/30/2026
የቢዝነስ ዜና ጋዜጠኛ / ቪዲዮ ሪፖርተር (አማርኛ)
መሰላል በኢትዮጵያ ውስጥ ለንግድ ድርጅቶች፣ ለአገልግሎት ሰጪዎች እና ለሸማቾች የተዘጋጀ የማስታወቂያ መድረክ ነው። የኢትዮጵያን የንግድ እና የስራ ፈጠራ እንቅስቃሴዎች ለማጉላት እና ለማስተዋወቅ ይሰራል።
መሰላል ተቀማጭነቷ/ ቱ በአዲስ አበባ የሆነች /የሆነ በአማርኛ ቋንቋ የቢዝነስ እና የንግድ ዜናዎችን ማቅረብ የሚችል ጋዜጠኛ ይፈልጋል።
ተመራጩ እጩ በቪዲዮ ላይ ቀርቦ ሪፖርት ማድረግ፣ ቃለ መጠይቆችን ማካሄድ እና ለዲጂታል ሚዲያ ይዘቶችን ማዘጋጀት ይጠበቅበታል።
ዋና ዋና ኃላፊነቶች
ከንግድ ባለቤቶች፣ ከስራ ፈጣሪዎች እና ከባለሙያዎች ጋር ቃለ መጠይቆችን ማካሄድ።
የቪዲዮ ዜናዎችን፣ ዘገባዎችን እና ቃለ መጠይቆችን ማዘጋጀት።
በካሜራ ፊት ቀርቦ ዜና እና ሪፖርቶችን ማቅረብ።
ለድረ-ገጽ፣ ለዩቲዩብ እና ለማህበራዊ ሚዲያዎች ይዘት ማዘጋጀት።
ተፈላጊ ችሎታዎችና መስፈርቶች
በጋዜጠኝነት፣ በኮሙኒኬሽን፣ በቢዝነስ ወይም በተዛማጅ መስክ የዩኒቨርሲቲ ዲግሪ
በጋዜጠኝነት ወይም በተዛማጅ መስክ የሚታወቀ ልምድ
አማርኛን በጽሑፍና በንግግር በብቃት መጠቀም የሚችል።
ለቢዝነስ፣ ለቴክኖሎጂ እና ለስራ ፈጠራ ጉዳዮች ፍላጎት ያለው
በዩቲዩብ እና በማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ማዘጋጀት ልምድ ያለው።
በአዲስ አበባ የቢዝነስ ማህበረሰብ ውስጥ ግንኙነቶች ያሉት ; ወይንም ግንኙነት ለመፍጠር ተነሳሺነት ያላት ወይንም ያለው
የማመልከቻ ሰነዶች
የህይወት ታሪክ (CV)
የማመልከቻ ደብዳቤ
ሶስት የቀድሞ የጽሑፍ ስራዎች (ካሉ)
የቪዲዮ ስራዎች ወይም የቃለ መጠይቅ ናሙናዎች (ካሉ)
ደመወዝ: በስምምነት
የስራ ቦታ: አዲስ አበባ
የማመልከቻ ጊዜ እስከ ሰኔ 10
የስራ መጀመሪያ ቀን: ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም.
E-mail : [email protected]