ዜና-ቪው

ዜና-ቪው "ትኩስ መረጃን እና ምርጥ የገበያ አማራጮችን በአንድ እይታ የሚያገኙበት የታመነ የዲጂታል መስኮት።"

21/06/2026
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት ይፋ መሆንን ምክንያት በማድረግ ከብልፅግና ፓርቲ የቀረበ የምስጋና መልዕክት፤እጅግ የተከበራችሁ ውድ ኢትዮጵያዊያን፣ የተከበራችሁ የፖለቲካ ማኅበረሰብ አባ...
21/06/2026

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት ይፋ መሆንን ምክንያት በማድረግ ከብልፅግና ፓርቲ የቀረበ የምስጋና መልዕክት፤

እጅግ የተከበራችሁ ውድ ኢትዮጵያዊያን፣ የተከበራችሁ የፖለቲካ ማኅበረሰብ አባላትና የምርጫው ባለድርሻ አካላት፤

ዛሬ ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲን በተግባር ያሳዩበት፣ ታሪካቸውን በደማቁ የጻፉበት እና አፍሪካ ስለ ራሷ በራሷ መወሰን እንደምትችል ለአለም ያበሰሩበት ታላቅ ምዕራፍ መመዝገቡ ይፋ ተደርጓል! በታሪካዊው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ ሕዝባችን ትናንትን በማከም እና ነገን በፅኑ መሠረት ላይ በመተለም፣ የኢትዮጵያን ከፍታ እውን ለማድረግ ፋና ወጊ ለሆነው ለብልፅግና ፓርቲ ዳግም ታላቅ ኃላፊነትና አደራ ሰጥቷል። ብልፅግና ፓርቲ ይህንን ታላቅ ሕዝባዊ አደራ የተቀበለው በስኬቱ ሳይኩራራ፣ ጉድለቶቹን እያረመ ሕዝብን በቅንነት ለማገልገልና ቃልን በተግባር ለማረጋገጥ ባለው ፅኑ እምነት ነው። ለዚህ ታላቅ ክብር መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሰጠንን የዴሞክራሲ ውል በታላቅ ትሕትና እና በከፍተኛ አክብሮት እንቀበላለን።

ይህ የምስጋና መልዕክት እኛን ለመረጡን ዜጎች ብቻ የቀረበ አይደለም፤ ይልቁንም ያሻቸውን አማራጭ በመምረጥ መብታቸውን የተጠቀሙ፣ በካርዳቸው ድምፅ በመንፈግም ቢሆን ሂደቱ ሕጋዊና ሰላማዊ እንዲሆን የበኩላቸውን የተወጡ ዜጎችን ሁሉ ያጠቃልላል። ምክንያቱም የእያንዳንዱ ዜጋ ተሳትፎ የሀገራችን ዴሞክራሲ እውነተኛ አሸናፊ እንዲሆን አድርጓል።

በዚህ ምርጫ ሂደት ውስጥ በግልጽ መለየት ያለበት መሠረታዊ እውነት አለ፡- የብልፅግና ፓርቲ አብላጫ ድምፅ አግኝቶ መንግሥት የመመሥረት መብት ማግኘቱ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና የማረጋገጥ ራዕይ ሰንቆ ውጤታማ ጉዞ እያደረገ እንዳለ ፓርቲ እንደ ትልቅ እድል የሚወሰድ ሲሆን፤ የምርጫው ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ፍትሓዊና ተዓማኒ ሆኖ መጠናቀቅ ግን የውድ ሀገራችን ኢትዮጵያ እና የመላው ሕዝቧ ስትራቴጂያዊ አሸናፊነት ማረጋገጫ ነው!

ይህ ምርጫ እንደ ከዚህ ቀደሙ የተለመደ የፖለቲካ ውድድር ወይም ወቅታዊ ኩነት አልነበረም። ይህ ምርጫ የውስጥና የውጭ የሴራ መረቦችን የበጣጠሰ፣ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በተግባር ያደመቀ፣ የዴሞክራሲ ተቋሞቻችንን ብስለት ያጎለበተ ታላቅ የታሪክ እመርታ ነው። ኢትዮጵያ በማንኛውም ውጫዊ ጫና ሳትበገር፣ ሙሉ በሙሉ በራሷ ሁለንተናዊ አቅም ያከናወነችው ይህ ታሪካዊ ክንውን ሀገር በቀል ዴሞክራሲን እና አህጉራዊ ሉዓላዊነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ለመላው አፍሪካ ኩራትና ተምሳሌት ሆኗል።

ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መሳተፋቸው የሕዝባችንን የፖለቲካ ንቃት የሚያሳይ ሲሆን፣ የሕዝብን ድምፅና ሉዓላዊ ፈቃድ ማክበር የመንግሥትና የማንኛውም የፖለቲካ ተዋናይ ቀዳሚ ተግባር መሆኑ በተግባር ተረጋግጧል። በምርጫው የኢትዮጵያ ጠላቶች ሀገርን ለማወክ የሸረቡት ተንኮልና መፍጨርጨር በሕዝባችን ብስለት ሙሉ በሙሉ እንዲመክን ተደርጓል።

የዚህ ታሪካዊ ስኬትና የኢትዮጵያ አሸናፊነት መረጋገጥ ያለ ባለድርሻ አካላት ተጋድሎ ሊታሰብ አይችልም። በመሆኑም ፓርቲያችን ብልፅግና ለምርጫው ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ የላቀ ምስጋናውንና አክብሮቱን ያቀርባል፡፡

በተለይም የኢትዮጵያ ሕዝብ የአገር ህልውናንና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በፅኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ያለውን የማይናወጥ ወገንተኝነት በተግባር ባሳየበት በዚህ ታሪካዊ የምርጫ ሂደት፣ በተለይም በምርጫው ዕለት ከሌሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ እግር ጥሎት ሳይሆን ራዕይ መርቶት፣ ብርድና ድካምን በሀገራዊ ፍቅር እያሸነፈ፣ እስከ ሚቀጥለው ቀን ሌሊት 10 ሰዓት ድረስ ለሙሉ 24 ሰዓታት ያለመሰልቸት በታላቅ ትዕግሥትና ዲሲፕሊን ተሰልፎ ሕ

ምርጫ ቦርድ በ11 የምርጫ ክልሎች የድጋሚ ምርጫ እንዲደረግ ወሰነ *********************የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ11 የምርጫ ክልሎች የድጋሚ ምርጫ እንዲደረግ መወሰኑን ዛ...
21/06/2026

ምርጫ ቦርድ በ11 የምርጫ ክልሎች የድጋሚ ምርጫ እንዲደረግ ወሰነ
*********************

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ11 የምርጫ ክልሎች የድጋሚ ምርጫ እንዲደረግ መወሰኑን ዛሬ ባካሄደው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ማሳወቂያ መርሐ ግብር ላይ አስታውቋል።

ውሳኔው የተላለፈው ጉልህ የሆነ የድምፅ አቆጣጠር እና ውጤት አሞላል ችግር በማጋጠሙ እንደሆነ አመልክቷል።

በዚህም የድጋሚ ምርጫው የሚደረግባቸው ሶሮ 1፣ ጠንባሮ፣ ሀርገሌ፣ ዳሮር፣ ሀድጋላ፣ አዋሬ፣ ዳራቶሌ፣ ባቱ (ዝዋይ)፣ ቤጊ፣ አሮሬሳ እና ጨንቻ ምርጫ ክልሎች መሆናቸውን ነው ምርጫ ቦርድ የገለጸው።

በድጋሚ ምርጫው እንዲደረግ ከተወሰነባቸው አምስቱ የምርጫ ክልሎች በሶማሌ ክልል የሚገኙ ሲሆን፣ እነዚህም ሀርገሌ፣ ዳሮር፣ ሀድጋላ፣ አዋሬ እና ዳራቶሌ የተባሉ የምርጫ ክልሎች መሆናቸው ተመላክቷል።

እንዲሁም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሶሬ1 እና ጠምባሮ ምርጫ ክልሎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የድጋሚ ምርጫ ይደረግላቸዋልም ነው የተባለው።

ባቱ (ዝዋይ) እና ቤጊ ምርጫ ክልሎች በኦሮሚያ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤት የድጋሚ ምርጫ የሚደረግበት ይሆናል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ጨንቻ ምርጫ ክልል ለክልል ምክር ቤት የድጋሚ ምርጫ እንደሚካሄድም ተገልጿል።

በአድማሱ አራጋው

 #ምርጫ2018  : ብልፅግና ፓርቲ ዛሬ ይፋ በተደረገው ውጤት 438 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) መቀመጫዎችን አግኝቷል።ይህም ፓርቲው መንግሥት መመስረት የሚያስችለው ነው።በሌላ በ...
21/06/2026

#ምርጫ2018 : ብልፅግና ፓርቲ ዛሬ ይፋ በተደረገው ውጤት 438 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) መቀመጫዎችን አግኝቷል።

ይህም ፓርቲው መንግሥት መመስረት የሚያስችለው ነው።

በሌላ በኩል ፦
- የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) 👉 13 መቀመጫዎች
- የግል ዕጩዎች 👉 8 መቀመጫዎች
- አማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) 👉 6 መቀመጫዎች
- የአፋር ህዝብ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ 👉 3 መቀመጫዎች
- አርጎባ አንድነት ጀርበቲ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ 👉 2 መቀመጫዎች
- ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ 👉 3 መቀመጫዎች
- ጉሙዝ ብሔራዊ ንቅናቄ 👉 1 መቀመጫ
- አዲስ ትውልድ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 👉 1 መቀመጫ
- የጌዴኦ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- የወላይታ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ 👉 1 መቀመጫ
- የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) 👉 3 መቀመጫዎች
- የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር 👉 1 መቀመጫ
- ህብረት ለዴሞክራሲና ለነጻነት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ
- ሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ 👉 1 መቀመጫ

ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ/ም

የኢትዮጵያ አየር ኃይል የሀገር ሉዓላዊነትን የማያስደፍር የሰማይ ላይ ጋሻ ነው - ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አየር ኃይል የሀገር...
20/06/2026

የኢትዮጵያ አየር ኃይል የሀገር ሉዓላዊነትን የማያስደፍር የሰማይ ላይ ጋሻ ነው - ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አየር ኃይል የሀገር ሉዓላዊነትን የማያስደፍር የሰማይ ላይ ጋሻ ነው አሉ የአየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ።

ሀገርን ከባዕድ ወረራና ከባንዳዎች ሴራ የሚከላከል ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታጠቀና የማይበገር አየር ኃይል መገንባቱን የገለጹት ዋና አዛዡ÷ የሀገር ሉዓላዊነትን የማያስደፍር የሰማይ ላይ ጋሻ ሆኗልም ነው ያሉት።

በቴክኖሎጂ የላቀ፣ በሥነ-ልቦና የጠነከረ፣ ለሀገር ክብር መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ የሆነ እና ጠላትን አምርሮ የሚጠላ ጀግና ሠራዊት መገንባቱንም ተናግረዋል።

የአየር ኃይሉ የውጊያ ዝግጁነት ቀዳሚ ዓላማ ውጊያን ከሩቅ ማስቀረት ነው፤ ሆኖም ጠላት የሰላም አማራጭን ችላ ብሎ ወደ ውጊያ ከገባ፣ አየር ኃይላችን የጠላትን ህልውና እስከወዲያኛው የሚያከስም አስተማማኝ መቺ ኃይል መሆኑን በተግባር ያረጋግጣል ብለዋል።

የጦር መሪ ቀዳሚ ኃላፊነት በሰላም ጊዜ ሠራዊቱን ለውጊያ ዝግጁ ማድረግ፣ ጦርነት ካጋጠመም ድል መቀዳጀት እንደሆነ አንስተው÷ ሀገር የምትፀናው በዘመናዊነት በተደራጀ፣ በሰለጠነ፣ በታጠቀና ብቁ በሆነ ጀግና ሠራዊት እንደሆነ አስረድተዋል።

የአየር ኃይሉ ዘላቂ የተቋም ግንባታ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በዲጂታል የሥልጠና አሠራሮች እንዲሁም በዘመናዊ የአቪዬሽን ቴክኖሎጂዎችና የጦር ትጥቆች የታጀበ መሆኑ ተቋሙን በቀጣናው የማይበገርና አስተማማኝ ኃይል እንዳደረገውም ገልጸዋል።

ጀግኖች አብራሪዎቻችን እና ቴክኒሺያኖቻችን የኢትዮጵያን ሰማይ በንቃት በመጠበቅ ላይ ይገኛሉ ያሉት ሌተናል ጄኔራል ይልማ÷ ተቋሙ አሁን ላይ በዘመናዊ አውሮፕላኖችና ሄሊኮፕተሮች የታገዘ ፈጣን የኃይል ስምሪት እና የላቀ ሎጂስቲክስ አቅም መገንባቱን አብራርተዋል።

ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሚያልሙ ኃይሎች ሰማያችንን ሌት ተቀን በንስር ዓይን የሚጠብቀውና በፅኑ ክንድ የሚቆጣጠረው ጀግናው አየር ኃይል የታሪካዊ ውድቀታቸው ምክንያት እንደሚሆን ሊያውቁት ይገባል ማለታቸውን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለፋና ዲጂታል ገልጿል።
ዜና-ቪው

በሙዝ ንግድ የምትተዳደር አንዲት እናት መንገድ ላይ ያገኘችውን ገንዘብ ወደ ፖሊስ ጣቢያ በመውሰድ አስረከበች። የታማኝነት እና የቅንነት ተምሳሌት — ከዶዮገና ከተማ!ድህነት ማለት የገንዘብ ማ...
20/06/2026

በሙዝ ንግድ የምትተዳደር አንዲት እናት መንገድ ላይ ያገኘችውን ገንዘብ ወደ ፖሊስ ጣቢያ በመውሰድ አስረከበች።

የታማኝነት እና የቅንነት ተምሳሌት — ከዶዮገና ከተማ!

ድህነት ማለት የገንዘብ ማጣት እንጂ የማንነት እና የሞራል መውደቅ አይደለም!"

ዛሬ ሁላችንም ልንማርባት የሚገባን፣ በቅንነቷ እና በጽናትዋ ሁላችንንም ያስተማረች ድንቅ እናትን ልናስተዋውቃችሁ ወደድን።

ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በከምባታ ዞን ዶዮገና ከተማ ውስጥ የምትኖር፣ በሙዝ ንግድ የምትተዳደር አንዲት ታጋይ እናት መንገድ ላይ ወድቆ የነበረ ገንዘብ (ብር) ታገኛለች።

ኑሮዋን ሙዝ በመሸጥ ሌት ተቀን የምትለፋ እናት ብትሆንም፣ "የሰውን አልፈልግም፤ ባለቤቱ እየተጨነቀ ይሆናል" በማለት ያገኘችውን ገንዘብ ሳታንገራግር በቀጥታ ወደ ዶዮገና ከተማ ፖሊስ ጽህፈት ቤት በመውሰድ በታማኝነት አስመዝግባለች።

ይህች እናት በዚህ በፈተና በበዛበት ዘመን፣ እውነተኛ ሀብት የሰው ልጅ ማንነት እና ህሊና መሆኑን በተግባር አሳይታለች። የላቧን እንጂ የሰውን የማትመኝ፣ ለልጆቿም ሆነ ለሀገር ትልቅ ተምሳሌት የሆነች ድንቅ የኢትዮጵያ እናት!

ገንዘቡ የጠፋባችሁ ወይም ባለቤቱን የምታውቁ ሰው፣ ትክክለኛ እና ህጋዊ መረጃ ይዛችሁ በዶዮገና ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በመቅረብ ገንዘባችሁን መረከብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

እባካችሁ ይህ መልዕክት ለባለቤቱ እንዲደርስ በማድረግ ተባበሩን!

ፈጣሪ ይህችን እናት በጤና፣ በበረከት እና በኪሷ ሞልቶ ይባርካት! ታማኝነት መቼም ቢሆን አይረክስም።

#ዶዮገና #ከምባታ #ታማኝነት #ኢትዮጵያዊነት

Via ዶዮገና ከተማ ፖሊስ ጣቢያ

ጉርሻ Page

🌴🌴🌴

ልዩ መረጃ‼️በሱዳን የሚገኘው የህወሓት ታጣቂዎች የትጥቅ መጋዘን ዛሬ በድሮን ተመቷል‼️የሻዕብያ ተላለኪ ቡድን የሆነው የነ ደብረፅዮን ቡድን፥ በሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት በቀጥታ  እየተሳ...
19/06/2026

ልዩ መረጃ‼️

በሱዳን የሚገኘው የህወሓት ታጣቂዎች የትጥቅ መጋዘን ዛሬ በድሮን ተመቷል‼️

የሻዕብያ ተላለኪ ቡድን የሆነው የነ ደብረፅዮን ቡድን፥
በሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት በቀጥታ እየተሳተፈ ይገኛል።

(ዘ-ሐበሻ ዜና) በሰሜን ኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ ክልል አዲስ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ውጥረት እያንዣበበ ይገኛል። የዘ-ሐበሻ ምንጮች ሾልኮ የወጣ መረጃን ዋቢ አድርገው እንዳጋለጡት፣ የኢ...
19/06/2026

(ዘ-ሐበሻ ዜና) በሰሜን ኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ ክልል አዲስ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ውጥረት እያንዣበበ ይገኛል። የዘ-ሐበሻ ምንጮች ሾልኮ የወጣ መረጃን ዋቢ አድርገው እንዳጋለጡት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ሕወሓትን ዳግም በሽብርተኝነት ለመፈረጅ በዝግጅት ላይ ነው። ቡድኑ ከዚህ ቀደም በሽብርተኝነት ተፈርጆ የነበረ ቢሆንም፣ የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተከትሎ ከሽብር መዝገብ መሰረዙ ይታወሳል።

ይህ አዲስ ክስተት የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተከትሎ የተገነባው የሰላም ትርክት በይዘቱ ምን ያህል ደካማ እና ተሰባሪ እንደነበረ የሚያረጋግጥ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ፣የኢትዮጵያ መንግሥት ቡድኖችን ከሽብር መዝገብ የመሰረዝ እና ዳግም የመመለስ ሂደት በተቋማዊ አስተማማኝነት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን በፖለቲካዊ ሚዛን ብቻ የሚወሰን መሆኑን ያሳያል። መንግሥት በጸጥታና በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ እየወሰደ ያለው እርምጃም ከስትራቴጂያዊ ዕቅድ ይልቅ "ለጊዜያዊ መደናገጥ የተገዛ" መሆኑን አጋልጧል።

የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ትናንት ያወጡት መግለጫ እና ወቅታዊ ሁኔታዎች፣ በትግራይ ፖለቲካዊ መዋቅር ውስጥ የተንሰራፋውን የከረረ የመረጃ መበጣጠስ፣ ጥልቅ የአመራር መከፋፈል እና የሰላም ሂደቱን ተጋላጭነት ፍንትው አድርገው አሳይተዋል።

በአሁኑ ወቅት በሕወሓት የደብረጽዮን ክንፍ በኩል ታጣቂዎችን በድብቅ የመመልመል፣ ሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር የማካሄድ፣ የሰነድ ማጭበርበር እና አልፎም የመዋቅር "መፈንቅለ-መንግሥት" ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑ ተጋልጧል። እጅግ አስደንጋጩ መረጃ ደግሞ፣ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ወጣቶችን በማፈስ እና ድንበር አቋርጦ ወደ ኤርትራ በማስገባት፣ በአቆርዳት እና በሳዋ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምፖች ውስጥ ስልጠና እየተሰጣቸው መሆኑን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አረጋግጠዋል።

ይህንን የፖለቲካ እና የፀጥታ መበላሸት ተከትሎ፣ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትናንት ባወጣው መግለጫ የሰላም ሂደቱን በማደናቀፍ ላይ ባሉ አካላት ላይ የማያዳግም እርምጃ መውሰድ መጀመሩን አስታውቋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቶማስ ፒጎት እንዳረጋገጡት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ጽንፈኛ በሆኑ የህወሓት አባላት እና በቅርብ የቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ ያነጣጠረ የቪዛ ማዕቀብ መጣል ጀምረዋል።

አሜሪካ ይህንን እርምጃ የወሰደችው፣ የትግራይ የፀጥታ ኃይሎች እና የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በቅርቡ በቀጥታ ግጭት ሊገቡ መሆኑን ተከትሎ 600,000 ሰዎችን ከቀጠፈው ጦርነት በኋላ ዳግም ቀጠናው ወደ እልቂት እንዳያመራ በማሰብ መሆኑን አስታውቃለች። ዩናይትድ ስቴትስ በሰላም መኖር ከሚፈልገው የትግራይ እና የመላው ኢትዮጵያ ህዝብ ጎን እንደምትቆም ገልጻ፣ ቀውሱን በሚያባብሱ ባለስልጣናት ላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን ሁሉንም አማራጮች እንደምትጠቀም አሳስባለች።

Adresse

Democratic Republic Of The

Site Web

Notifications

Soyez le premier à savoir et laissez-nous vous envoyer un courriel lorsque ዜና-ቪው publie des nouvelles et des promotions. Votre adresse e-mail ne sera pas utilisée à d'autres fins, et vous pouvez vous désabonner à tout moment.

Partager