Useful Info

Useful Info To share something important information

የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ኮርፖሬት ኮሙኒኬሽንና ፕሮሞሽን ዳይሬክተር አቶ ሁናቸው ታዬ ሚሊኒየም አዳራሽን አሰመልክቶ ለሚዲያዎች የሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፦በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር ...
28/07/2025

የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ኮርፖሬት ኮሙኒኬሽንና ፕሮሞሽን ዳይሬክተር አቶ ሁናቸው ታዬ ሚሊኒየም አዳራሽን አሰመልክቶ ለሚዲያዎች የሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፦

በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኘው አዲስ ፓርክ እና ማኔጅመንት በተለምዶ ሚሊኒየም አዳራሽ እየተባለ የሚጠራው በኢትዮዽያ ውስጥ ከሚገኙ ግዙፍ አዳራሾች መካከል ግንባር ቀደሙ መሆኑ ይታወቃል።

ሚሊኒየም አዳራሽ የኢትዮዽያ ሚሊኒየምን ታሳቢ አድርጎ በዘመናዊ መልኩ ተገንብቶ የተለያዩ አገልግሎቶችን ሲሰጥ የቆየ ግዙፍ አዳራሽ ነው።

ይህ የሚሊኒየም አዳራሽ ኢትዮዽያ ውስጥ የነበሩ ጥሩም ሆኑ መጥፎ ጊዜያቶች ሁሉንም በአንድ በማሰባሰብ ትልቅ ሚና የተጫወተ ነው። አሁንም በመጫወት ላይ ይገኛል።

እስከ 25 ሺህ ሰዎችን በአንድ ጊዜ የማስተናገድ አቅም ያለው የሚሊኒየም አዳራሽ 20 ሺህ ስኩየር ሜትር ስፋት ላይ ያረፈ ነው።

በዘመናዊ ሳውንድ ሲስተም፣ ዲጅታል ስክሪን፣ የመድረክ መብራቶች እና ዘመናዊ ፈርኒቸርና የኤግዚቢሽን ቁሳቁሶች የተደራጀው ይህ አዳራሽ እስካሁን ድረስ በርካታ ዝግጅቶችን አስተናግዷል።

እንደ ሀገር በኢትዮዽያ ተከስቶ በነበረው የኮቪድ 19 ችግር ወቅት ሙሉ በሙሉ ለህክምና አገልግሎት መስጫነት መዋሉም ይታወሳል።

ትልልቅ ሀገራዊ ፕሮግራሞች፣ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች፣ ኤግዚቢሽኖች፣ ሀይማኖታዊ ፕሮግራሞች፣ ምርቃቶች እንዲሁም ደግሞ ታላላቅ ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍና ሽኝት ሲደረግም ሚሊኒም አዳራሽ ላይ ነበር።

ይህ በኢትዮዽያ ግዙፉ አዳራሽ በሳለፍነው ሰኔ ወር 2017 ምሽት ላይ የተለመደውን አገልግሎት እየሰጠ በነበረበት ወቅት የእሳት አደጋ ያጋጠመው ሲሆን አሁን ሙሉ በሙሉ ተስተካክሎ ወደ ስራ መግባት ችሏል።

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕም ችግሩን በአጭር ጊዜ በመፍታት ወደ ስራ እንዲገባ አድርጎታል።

የችግሩ ምንጭ ለጊዜው በሚመለከተው አካል እየተጣራ በመሆኑ ጊዜው ሲደርስ ይፋ የሚደረግ ይሆናል።

ከዚህ በተጨማሪም ታህሳስ ወር 2018 ጀምሮ ሚሊኒየም አዳራሽ እጅግ ዘመናዊ በሆነ መልኩና አሁን ከሚሰጠው አገልግሎት በላቀ ደረጃ እንዲሰጥ ታስቦ እንደ አዲስ የሚገነባ ይሆናል።

24/05/2025
ፓስፖርት በመጠባበቅ ላይ ያሉ ግለሰቦች ለመውሰድ ሲመጡ የፋይዳ መረጃቸውን ይዘው መቅረብ ይጠበቅባቸዋል******** ከሰኔ 1፣ 2017 ዓ.ም ጀምሮ የፋይዳ መታወቂያን ለፓስፖርት አገልግሎት ከ...
26/04/2025

ፓስፖርት በመጠባበቅ ላይ ያሉ ግለሰቦች ለመውሰድ ሲመጡ የፋይዳ መረጃቸውን ይዘው መቅረብ ይጠበቅባቸዋል
********

ከሰኔ 1፣ 2017 ዓ.ም ጀምሮ የፋይዳ መታወቂያን ለፓስፖርት አገልግሎት ከሚያስፈልጉ ዋና ሰነዶች ውስጥ በማካተት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ስምምነት ተፈርሟል።

የትብብር ስምምነቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ ከኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት ጋር ተፈራርመዋል።

በዚሁ መሠረት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የፓስፖርት አገልግሎት ጥያቄ አቅርበው በመጠባበቅ ላይ ያሉ ግለሰቦች ፓስፖርት ለመውሰድ ሲመጡ መረጃቸውን ይዘው መቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል።

ተገልጋዮች የፋይዳ ልዩ ቁጥራቸውን በመያዝ፣ QR ኮዱን በወረቀት አትመው፣ ዲጂታል ኮፒውን በ"Fayda ID” application በኩል ይዘው ወይም ትክክለኛውን QR የያዘ ሌላ አማራጭ ተጠቅመው ይዘው በመምጣት ብቻ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ ነው የተባለው።

አገልግሎቶች ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር መተሳሰራቸው አንድ ወጥ ደረጃ ያለው እና የተናበበ መረጃ በብሔራዊ ደረጃ እንዲር በማድረግ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ መረጃ ያመለክታል።

24/07/2022

Kenya 🇰🇪 is one of the countries in Africa with the most modernised train system in Africa.
The Nairobi to Mombasa standard Guage rail is one of the fastest train in Africa with a speed of 120km per hour and also the fastest in East Africa.

05/07/2022

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የነዳጅ ምርቶች የመሸጫ ዋጋ ጭማሪ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የዋጋ ማሻሻያው ከነገ ሰኔ 29 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ይሆናል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ታህሳስ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገው 3ኛ መደበኛ ስብሰባ ባስተላለፈው የነዳጅ ውጤቶች የዋጋ ግንባታና የትርፍ ህዳግ አሰራር እና የመሸጫ ዋጋ ማስተካከያና የታለመ ድጎማ አፈጻጸም ውሳኔ ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ስራ ሲከናወን መቆየቱ ይታወቃል።

ሚኒስቴሩ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ክለሳን አስመልክቶ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ፥ በግንቦት ወር የዓለም አቀፍ የነዳጅ ምርቶች መሸጫ ዋጋ ቤንዚን በሜትሪክ ቶን 1300 ዶላር ፣ ናፍጣ በሜትሪክ ቶን 1162 ዶላር ከነበረበት፥ በሰኔ ወር 2014 ዓ.ም ቤንዚን በሜትሪክ ቶን 1364 ደላር፣ ናፍጣ በሜትሪክ ቶን 1322 ዶላር የደረሰ መሆኑን አውስቷል።

መንግስት የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ አልፎ አልፎ ከ10 በመቶ ያልበለጠ ጭማሪ እያደረገ የቆየ በመሆነ ቤንዚን በሊትር 36.87 ብር ፣ ናፍጣ በሊትር 35.43 ብር መሸጫ ዋጋ ሆኖ እንዲቆይ ማድረጉንም አስረድቷል፡፡

ይሁን እንጂ ይህ ውሳኔ በነዳጅ ማረጋጊያ ፈንድ ላይ በወር በአማካይ ወደ ተጠቃሚው መተላለፍ የነበረበት 10 ቢሊየን ብር ጉድለት ወደ መንግስት እየተመዘገበ መጥቶ በአሁኑ ወቅት ሀገሪቱ 146 ቢሊየን 624 ሚሊየን 248 ሺህ 889 ብር ከፍተኛ ዕዳ ለመሸከም መገደዷን ገልጿል፡፡

ስለሆነም መንግሥት የዕዳ ጫናን ደረጃ በደረጃ ለማስቀረት እንዲቻል የሚኒስትሮች ምክር ቤት የነዳጅ ውጤቶች መሸጫ ዋጋ ማስተካከያና የታለመ ድጎማ እንዲተገበር ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት ዝቅተኛ ገቢ ያለውን የህብረተሰብ ክፍል ተጽዕኖ በማያስከትል ሁኔታ የሕዝብ መጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን በመለየት የድጎማ ተጠቃሚ ለማድረግ የነዳጅ ዋጋ ክለሳና የታለመ ድጎማ ትግበራ ከነገ ጀምሮ ወደ ስራ መግባት አስፈልጓል ብሏል፡፡

በመሆነም የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በሰኔ ወር 2014 ዓ.ም በዓለም ገበያ በተገዛበት መሸጫ ዋጋ መነሻ በማድረግ በቀጥታ ቢሰላ የአዲስ አበባ ከተማ የ1 ሊትር ናፍጣ መሸጫ ዋጋ ብር 91 ከ23 ሳንቲም እና የቤንዚን መሸጫ ዋጋ በሊትር 82 ብር ከ07 ሳንቲም መሸጥ የነበረበት ሲሆን፥ አሁንም ሀገራችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ ከዓለም ገበያ መሸጫ ዋጋ የልዩነቱን 75 በመቶ የሚሆነውን ጫና መንግስት በመሸከም፥ ቀሪውን 25 በመቶ ለተጠቃሚው እንዲተላለፍ በመወሰን የነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ መጠነኛ ክለሳ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ነው ያስታወቀው።

ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ መሰረት፦
ቤንዚን --- 47 ነጥብ 83 በሊትር
ነጭ ናፍጣ --- 49 ነጥብ 02 በሊትር
ኬሮሲ --- 49 ነጥብ 02 በሊትር
ቀላል ጥቁር ናፍጣ --- 53 ነጥብ 10 በሊትር
ከባድ ጥቁር ናፍጣ --- 52 ነጥብ 37 በሊትር
የአውሮፕላን ነዳጅ --- 98 ነጥብ 83 በሊትር መሆኑን አስታውቋል፡፡

ከላይ የተገለጸው የቤንዚን፣ የኬሮሲንና የነጭ ናፍጣ ዋጋ ላይ ለህዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ወይም የታለመ ድጎማ ተጠቃሚ ተሸከርካሪዎች 15 በመቶ በመንግስት እንዲደጎምና ቀሪውን 10 በመቶ እንዲከፍሉ በማድረግ የድጎማ መጠኑን በቴሌ ብር ተመላሽ እንዲሆንላቸው ይደረጋል ብሏል ሚኒስቴሩ፡፡

የዋጋ ማስተካከያ የተደረገባቸው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በዝርዝር ከነገው /ሰኔ 29/2014 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም ክልሎች በሚገኙ ማደያዎች ሁሉ ተግባራዊ እንደሚሆን አስታውቋል።

የነዳጅ ምርቶች ወቅታዊ የዓለም አቀፍ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ ሸማቹ ህብረተሰብ ምርቶቹን በቁጠባ የመጠቀም ባህሉን እንዲያዳብር እንዲሁም የታለመ የነዳጀ ድጎማ ተጠቃሚዎች የነዳጅ ምርቱን ለታለመለት የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ብቻ ማዋል የሚኖርባቸው መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

ሁሉም የህብረተብ ክፍል፣ የፀጥታ አካላትና ባለድርሻ አካላት ተገቢውን ትብብር እንዲያደርጉም ጠይቋል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

04/07/2022

ነባሮቹ የእንግሊዝ ፓውንድ ባለ 50 እና ባለ 20 ኖቶች የመጠቀሚያ ጊዜ መስከረም 20 እንደሚያበቃ ባንኩ አስታወቀ
*******************

ነባሮቹ የእንግሊዝ ፓውንድ ባለ 50 እና ባለ 20 ኖቶች የመጠቀሚያ ጊዜ መስከረም 20, 2015 ዓ.ም እንደሚያበቃ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ።

እ.ኤ.አ. በ23/06/2021 ባለ ሀምሳ (50) ፖውንድ ኖት እና ቀደም ብሎ ማሻሻያ የተደረገበት ባለ ሀያ (20) ፓውንድ ኖት ወደ ግብይት መግባታቸውን ያስታወሰው ባንኩ የነባሮቹ ኖቶች የመጠቀሚያ ጊዜ እስከ መስከረም 20, 2015 ዓ.ም ብቻ መሆኑን ነው የገለፀው።

ስለሆነም ነባሮቹ ባለ ሃምሳ እና ባለ ሃያ የእንግሊዝ ፓውንድ ኖቶች በእጃችሁ የሚገኙ ደንበኞቻችን ከቀነ ገደቡ በፊት ወደ ባንኩ ቅርንጫፎች በመምጣት የምንዛሪ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ አሳስቧል።

የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/EBCworld/
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/EBCNEWSNOW
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የቲክቶክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.tiktok.com/

02/07/2022

በክሪፕቶከረንሲ 4 ቢሊዮን ዶላር ያጭበረበችው ግለሰብ የኤፍ.ቢ.አይ ዋነኛ ተፈላጊዎች ዝርዝር ውስጥ ተካተተች
**************************

በክሪፕቶከረንሲ 4 ቢሊዮን ዶላር ያጭበረበችው ግለሰብ በአሜሪካ የፌዴራል ወንጀል ምርመራ ኤጀንሲ /ኤፍ.ቢ.አይ/ 10 ዋና ዋና ተፈላጊዎች ዝርዝር ውስጥ መካተቷን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ገለጹ።

“የክሪፕቶ ንግሥቷ” በሚል ቅፅል ስም የምትታወቀው ሩጃ ኢግናቶቫ የተባለች ግለሰብ፣ ‘OneCoin’ /ዋንኮይን/ በተባለ ሐሰተኛ የዲጂታል ገንዘብ ከተለያዩ ሰዎች ከ4 ቢሊዮን ዶላር በላይ አጭበርብራ መሰወሯ ነው የተገለጸው።

በኤፍ.ቢ.አይ በእጅጉ ተፈላጊ ከሆኑ 10 ዋና ዋና ግለሰቦች ውስጥ ብቸኛዋ ሴት የሆነችው ኢግናቶቫ፣ የፈፀመችው የማጭበርበር ወንጀል እጅግ ትልቁ እንደሆነም ተነግሯል።

ግለሰቧ ወንጀሉን ስትፈፅም መቆየቷን የገለጸው ኤፍ.ቢ.አይ፣ ከ2017 (እ.አ.አ) ወዲህ ደብዛዋ አልተገኘም ብሏል።

እንደ ቢቢሲ ዘገባ፣ ግለሰቧ ማንነቷን ቀይራ ሊሆን ይችላል የሚል ጥርጣሬ በአሜሪካ ባለሥልጣናት ዘንድ ተፈጥሯል።

በ2019 የኤሌክትሮኒክስ ማጭበርበርን ጨምሮ በስምንት የተለያዩ የወንጀል ጉዳዮች ክስ ቀርቦባታል።

ዐቃቤ ሕጎች እንዳሉት ሩጃ ኢግናቶቫ የምትመራው ኩባንያ በዋናነት ‘ዋንኮይን’ን እንደ ፒራሚድ በመጠቀም ሌሎች ሰዎች ዋጋ የሌለውን ክሪፕቶከረንሲ እንዲገዙ እንዲያሳምኑላቸው ለአባላቱ ኮሚሽን ይከፍላል።

በአሜሪካ ማንሃታን ግዛት ከፍተኛ የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ የሆኑት ዳሚያን ዊሊያምስ እንደገለጹት፣ ግለሰቧ የማጭበርበር ዕቅዷን የተጠቀመችው ስለክሪፕቶከረንሲ ብዙ ሲወራለት በነበረበት ወቅት ነው።

‘ዋንኮይን’ የተባለው የዲጂታል ገንዘብ በታሪክ ውስጥ ትልቁ የማጭበርበሪያ ዘዴ እንደሆነም ዐቃቤ ሕጉ መናገራቸውን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል።

የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/EBCworld/
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/EBCNEWSNOW
የተመረጡ አጫጭር የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የቲክቶክ አካውንታችንን ይከተሉ
https://www.tiktok.com/

27/06/2022
25/06/2022

This YouTube channel is one of the digital products of the Ethiopian Reporter. To address breaking and pressing issues in today’s eventful Ethiopia, the chan...

25/06/2022

ሩስያ ስዊፍትን ለመተካት ያዘጋጀችው የገንዘብ መላኪያ ስርዓት ለብሪክስ ሀገራት ዝግጁ ነው አለች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሩስያ በስዊፍት ምትክ ያዘጋጀችው አዲሱ የገንዘብ መላኪያ ስርዓቷ ለብሪክስ ሀገራት ዝግጁ መሆኑን ገለጹ፡፡

ፕሬዚዳንት ፑቲን እንዳሉት፥ የብሪክስ አባል ሀገራት ማለትም ደቡብ አፍሪካ ፣ ብራዚል፣ ሕንድ እና ቻይና የፋይናንስ ተቋማት ከሀገራቸው የገንዘብ ማስተላለፊያ ስርዓት ጋር አስመልክተው መገናኘት እንደሚችሉ ገልጸዋል።

ፑቲን በብሪክስ የቢዝነስ ፎረም ላይ ባደረጉት ንግግር፥ ሞስኮ ዓለም አቀፍ የገንዘብ መላላኪያ ስርዓቶቿን አጋር ላለቻቸው እነዚህ ሀገራት አስተማማኝ አማራጮችን እያዘጋጀች ነው ብለዋል።

አክለውም ፥ የብሪክስ መገበያያ በሆነ ገንዘብ ዓለም አቀፍ ግምጃ ቤት ለማቋቋም ሂደት ላይ መሆናቸውንም ነው የገለጹት፡፡

አዲሱ የገንዘብ ማስተላለፊያ ስርዓት ከስዊፍት ጋር ተመሳሳይ ተግባር እና በገንዘብ ተቋማት መካከል መልዕክቶችን በተመሳሳይ ማስተላለፍ የሚያስችል ነው ተብሏል።

አዲሱ የገንዘብ ማስተላለፊያ ስርዓት ሞስኮ ከዩክሬን ጋር እያካሄደችው ባለው ጦርነት ምክንያት በምዕራቡ ዓለም የተጣለባትን ማዕቀብ ለመቋቋም የተፈጠረ እንደሆነም ነው የተገለጸው፡፡

በሚያዝያ ወር ላይ የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ገዥ ኤልቪራ ናቢሊና አብዛኞቹ የሩሲያ አበዳሪዎች እና ከ12 ሀገራት የመጡ 52 የውጭ ድርጅቶች አዲሱ የገንዘብ ማስተላለፊያ አገልግሎት ማግኘታቸውም ተነስቷል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘም የክፍያ ስርዓቱ የአባላቱን ማንነት በሚስጥር ይጠብቃል ሲል የዘገበው አር ቲ ነው ።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Dirección

Madrid

Página web

Notificaciones

Sé el primero en enterarse y déjanos enviarle un correo electrónico cuando Useful Info publique noticias y promociones. Su dirección de correo electrónico no se utilizará para ningún otro fin, y puede darse de baja en cualquier momento.

Contacto La Empresa

Enviar un mensaje a Useful Info:

Compartir