Hanaze media ሀናዜ ሚዲያ

Hanaze media ሀናዜ ሚዲያ ይህ የኢትዮጺያ

 የቤት ኪራይ መጨመር አይቻልም !" ለቤት ኪራይ የወጣው ደንብ እስከሚሻሻል ድረስ የኪራይ ዋጋ መጨመር አይቻልም " - ከንቲባ አዳነች አቤቤለቤት ኪራይ የወጣው ደንብ እስከሚሻሻል ድረስ የኪራ...
07/07/2022



የቤት ኪራይ መጨመር አይቻልም !

" ለቤት ኪራይ የወጣው ደንብ እስከሚሻሻል ድረስ የኪራይ ዋጋ መጨመር አይቻልም " - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ለቤት ኪራይ የወጣው ደንብ እስከሚሻሻል ድረስ የኪራይ ዋጋ መጨመር የማይቻል መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ።

ከንቲባዋ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሰጡት መግለጫ ለቤት ኪራይ የወጣው ደንብ እስከሚሻሻል የቤት ኪራይ መጨመር አይቻልም ብለዋል።

ከንቲባዋ በመግለጫቸው የከተማ አስተዳደሩ በየ3 ወሩ የሚታደስ መመሪያ እንደነበረው አስታውሰዋል።

በከተማዋ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት በመኖሩ በዜጎች ላይ ጫና እያስከተለ በመሆኑ የቤት ኪራይ መጨመር መከልከሉን አስረድተዋል።

በመሆኑም የከተማ አስተዳደሩ በልዩ ሁኔታ አይቶ ደንቡ እስካልተሻሻለ ድረስ ምንም አይነተ የቤት ኪራይ ጭማሪ ማድረግ አይቻልም ብለዋል።

#አከራዮችም ሆኑ #ተከራዮች ይህንኑ ማወቅ እንዳለባቸው ጠቁመው ክልከላውን ተላልፈው በሚገኙ ላይ ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል ሲሉ አሳስበዋል።

በዚህ ዙሪያ ዜጎች መብት እና ግዴታቸውን በቅጡ ተገንዝበው እንዲሰሩ አስገንዝበዋል።



t.me//hanazemedia

29/06/2022

Follow our tiktok page

tiktok.com/

18/04/2022

Intro of hanaze media

wellcome to  Subscribe our youtube channel
11/04/2022

wellcome to
Subscribe our youtube channel

Hanaze MediaOffers confirmed current and national news, various suggestions and comments as well as useful and reliable information.

09/03/2022



በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ያሉ ተፈናቃዮች የከፋ ችግር ላይ መውደቃቸው ተገልጿል።

አስተዳደሩ ዛሬ ባሰራጨው መልዕክት " ዋግ ከችግር ቆፈን ላይ ወድቃለች፤ የመከራ ቃፊር እየናጣት ነው የሚደርስላት ትሻለች " ብሏል።

አሁን ላይ ከአበርገሌ፣ ከጻግብጂ፣ ከዝቋላ፣ ከሰቆጣ ዙሪያ፣ ዛታ፣ ወፍላና ኮረም በጦርነት ምክንያት በየቀኑ ከ2000 ሰው በላይ የተፈናቀለ ወለህ ሜዳ ላይ ሰፍሯል እንዲሁም በሰቆጣ ከተማ ከተለያዩ ቦታዎች የሰፈረው ከ52,000 (ከሀምሳ ሁለት ሺህ ) በላይ ህዝብ መሆኑ ተገልጿል

ቤት ንብረቱን ጥሎ በመጠለያ የሚኖረው ማህበረሰብ የማይቻል ችግር ተሸክሟል ተብሏል።

አዛውንቶች፣ እናቶች፣ ህጻናት በአስቸጋሪ ሆኔታ ላይ የሚገኙ ሰሆን ከእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖባቸው እርሀባቸውን እንዳይችሉ በበሽታ ተቆራምደዋል ተብሏል።

አዛውንቶች፣ ጧሪ የሌላቸው ሽማግሌዎች በሽታው፣ እርጅናው እና ረሀቡ እየተፈራረቀባቸው ሞታቸውን እየናፈቁ ነው።

" ዋግ ላይ መቋጫ የሌለው ችግር ፣ እፎይታ የሌለው መከራ፣ እየተፈራረቀ ነው " ያለው አስተዳደሩ " የሰው ልጅ እንደዘበት ሜዳ ላይ ወድቋል ፤ በዋግ ህዝብ ላይ የመከራ ጅራፍ አልለይ ብሏል፤ የችግር ድምጽ በህጻናት አእምሮ ሰፍሮ የሳቅ አንደበታቸው ተዘግቷል " ሲል አስተድቷል።

በዋግ ያሉ ተፈናቃዮች በየጊዜው የሚመጣው የነፍስ ማቆያ እርዳታ ለጥቂት ጊዜ እንቆይ ይሆናል እንጂ ችግራችን በመሰረታዊነት ሊቀርፍልን አይችልም ያሉ ሲሆን ፤ በዋናነት ችግሩ የሚቀረፈው አከባቢያቸው ነጻ ሆኖ ወደቀያችን ሲመለሱ መሆኑን ገልፀዋል።

መንግስት ለአከባቢው #ትኩረት ሰጥቶ ማህበረሰቡን ሊታደግ ይገባል ሲሉ ጥሪ ማቅረባቸውን ከዋግኽምራ ኮሚኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

Tikivah news

 የአሜሪካ መንግሥት ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (USAID) አስተዳዳሪ ሳማንታ ፓወር ወደ ትግራይ የሚደረጉት የእርዳታ በረራዎች መጨመራቸውን አሳውቀዋል።ከታህሳስ ወር ጀምሮ 210 ሜትሪክ ቶ...
09/03/2022



የአሜሪካ መንግሥት ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (USAID) አስተዳዳሪ ሳማንታ ፓወር ወደ ትግራይ የሚደረጉት የእርዳታ በረራዎች መጨመራቸውን አሳውቀዋል።

ከታህሳስ ወር ጀምሮ 210 ሜትሪክ ቶን የህክምና እንዲሁም ስነምግብ አቅርቦቶች ትግራይ ክልል መድረሳቸውን ፓወር አመልክተዋል።

ነገር ግን ብቸኛው የተቸገሩትን ሁሉ ለመድረስ የሚያስችለው ፤ የጭነት ተሽከርካሪዎች የሚሄዱበት መንገድ እንደተዘጋ ነው ብለዋል።

700 ሺህ ሰዎች የረሃብ አደጋ ተጋርጦባቸዋል ያሉት ሳማንታ ፓወር " የኢትዮጵያ መንግስት ያልተገደበ ሰብአዊ አቅርቦትን ማመቻቸት አለበት " ብለዋል።

Tikivah news

የየካቲት ወር የዋጋ ግሽበት 📈የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየወሩ የሚያወጣው የዋጋ ግሽበት መረጃ የየካቲት ወር 2014 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር...
09/03/2022

የየካቲት ወር የዋጋ ግሽበት 📈

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየወሩ የሚያወጣው የዋጋ ግሽበት መረጃ የየካቲት ወር 2014 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ33.6 ከመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡

የምግብ ዋጋ ግሽበት የየካቲት ወር 2014 ዓ/ም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ41.9 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡

በያዝነው ወር በአብዛኛው በእህሎች ዋጋ ጭማሪ የታየ ሲሆን በአንፃሩ የአትክልት ዋጋ ላይ ቅናሽ ታይቷል፡፡

ምንጭ፦ ካፒታል ጋዜጣ

TTikivah newsnTikivah news

 #ይፈለጋልየኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከላይ በምስሉ ላይ ያለውን ግለሰብ በወንጀል እንደሚፈልገው አሳውቋል።ግለሰቡ የተለያዩ ሀሰተኛ መታወቂያዎችን በማውጣትና በመጠቀም ከተለያዩ ባንኮች ብር አጭ...
09/03/2022

#ይፈለጋል

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከላይ በምስሉ ላይ ያለውን ግለሰብ በወንጀል እንደሚፈልገው አሳውቋል።

ግለሰቡ የተለያዩ ሀሰተኛ መታወቂያዎችን በማውጣትና በመጠቀም ከተለያዩ ባንኮች ብር አጭበርብሮ በማውጣት ወንጀል እንደሚፈለግ ነው ፖሊስ የገለፀው።

ፌዴራል ፖሊስ ተጠርጣሪውን የሚመለከት ማንኛውም መረጃ ካልዎት እንዲያሳውቁ ጥሪ ያቀረበ ሰሆን ህብረተሰቡ የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ ጠይቋል።

ስልክ ፡ 0115309139 (ዘውትር በስራ ሰዓት ከ2:30-11:30)
ስልክ : 0111119475 / 0111711012 (በማንኛውም ሰዓት)
ነፃ የስልክ መስመር 861

Tikivah news

09/03/2022



የዩክሬን መንግሥት ስንዴ፣ አጃ እና መሰል የእህል ምርቶች ከሀገር ውጭ ለገበያ እንዳይቀርቡ ማገዱ ዛሬ ይፋ ሆኗል።

የግብር እና ምርቶችን የሚመለከተው አዲሱ ሕግ ዩክሬን ውስጥ የተደነገገው በዚህ ሳምንት መሆኑን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።

በአሁን ሰዓት ከሩስያ ጋር በጦርነት ላይ የምትገኘው ዩክሬን የምድራችን ከፍተኛ የስንዴ አምራች ሀገር ናት።

በተጨማሪ ዓለማችን ግማሹን የሱፍ አበባ እና ከዚህ ሰብል የሚገኙት ዘይትና ሌሎች ምርቶችን የምታገኘው በአሁን ሰዓት ጦርነት ላይ ካሉት 2ቱ ሀገራት ነው።

ዩክሬን በበቆሎ ምርቷም በዓለማችን የምትታወቅ ሀገር ናት።

Tikivah news

09/03/2022

" የምግብ ዋጋ ጣራ እየነካ ነው "

የዓለም አቀፉ ምግብ ፕሮግራም ኃላፊ ዴቪድ ባስሌይ የዩክሬን ጦርነት የምግብ ዋጋን እንደሚያንረውና ያላደጉ አገራትን ምጣኔ ሃብት ሊያደቅ እንደሚችል አስጠነቀቁ።

ዩክሬንና ሩሲያ የምግብ ምርቶችን በገፍ ከሚያመርቱ የዓለማችን አገራት መካከል ናቸው።

ኃላፊው እንደሚሉት ጦርነቱ አንዳንድ አገራትን ወደከፋ ረሃብ ሊገፋቸው ይችላል።

"ምድራችን ላይ ያለው የከፋ ሁኔታ ወደ ባሰ ሁኔታ አይሸጋገርም ብለን ተስፋ ብናደርግም እነሆ ይሄ ተፈጠረ" ብለዋል ኃላፊው።

ሩሲያና ዩክሬን በአንድ ወቅት የአውሮፓ የዳቦ ቅርጫት ይባሉ ነበር። የምድራችንን ሩብ የስንዴ ምርት አምራች አገራት ነበሩ።

በተጨማሪ ዓለማችን ግማሹን የሱፍ አበባና ከዚህ ሰብል የሚገኙት ዘይትና ሌሎች ምርቶችን የምታገኘው ከ2ቱ ሀገራት ነው።

ሩሲያ በነዳጇ ዩክሬን በበቆሎ ምርቷ የዓለማችን ትሩፋቶች ናቸው።

ዴቪድ ባስሌይ በዓለማችን የረሃብ ስጋት ተደቅኖባቸዋል የሚባሉ ሰዎች ቁጥር ከ80 ሚሊዮን ወደ 276 ሚሊዮን ማሻቀቡን ገልፀዋል። ይህ የሆነው የአየር ንብረት ለውጥና የኮሮና ወረርሽኝ ላይ ሩሲያ በዩክሬን ያወጀችው ጦርነት ሲታከልበት ነው ብለዋል።

ኃላፊው አንዳንድ አገራት አሁን ባጋጠመው ቀውስ ሳቢያ የከፋ አደጋ ፊታቸው ተደቅኗል ብለዋል። ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ እኚህ አገራት ከፍተኛውን ጥራጥሬ የሚያስመጡት ከጥቁር ባሕር አካባቢ በመሆኑ ነው።

ባስሌይ ፤ "ሊባኖስ ለምሳሌ 50 በመቶ ጥራጥሬ የምታስመጣው ከዩክሬን ነው። የመን፣ ሶሪያ፣ ቱኒዚያ እና ሌሎች በርካታ አገራትን መጥራት እችላለሁ፤ ከዩክሬን በሚያስመጡት እህል ላይ ጥገኛ ናቸው" ያሉ ሲሆን "ነገር ግን አሁን የዳቦ ቅርጫት ከመሆን ወደ ዳቦ ጠባቂነት ስትለወጥ በጣም የሚያስገርም የእውነት መመሰቃቀል ነው" ብለዋል።

Tikivah news

09/03/2022

የተመድ ኢሜል ውዝግብ ፈጠረ።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለሰራተስኞቹ በላከው የኢሜል መልዕክት የዩክሬንን ሁኔታ " ጦርነት " ወይም " ወረራ " ብለው እንዳይጠሩ መልዕክት ማስተላለፉን አይሪሽ ታይምስ አስነብቧል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰራተኞቹ በዩክሬን ላለው ሁኔታ " ግጭት " ወይም " ወታደራዊ ጥቃት " የሚሉትን ቃላት እንዲጠቀሙ መመሪያ እንደሰጣቸው ገልጿል።

የተመድ ኮሙኒኬሽን ዲፓርትመንት ለሰራተኞች በላከው የኢሜል መልዕክት ሰራተኞች በዩክሬን ላለው ሁኔታ " ጦርነት " ወይም " ወረራ " እያሉ እንዳይጠቀሙ ከመግለፁ በተጨማሪ የዩክሬንን ባንዲራ በግል ወይም ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ ገፆች ወይም ድረገጾች ላይ እንዳያካትቱ መመሪያ ሰጥቷል።

ይህ ዘገባ ከወጣ ብዙም ሳይቆይ የተመድ ቃልአቀባይ (የትዊተር ገፅ) ዘገባውን በሰራችው የአይሪሽ ታይምስ የአውሮፓ ዘጋቢ ናኦሚ ኦሊሪ የትዊተር ገፅ በመግባት የወጣውን ዘገባ አስተባብሏል ፤ ሀሰተኛ ነው ፤ እንደዛ አልተባለም ሲል ነው ተመድ ዘገባውን ያጣጣለው።

ድርጅቱ ብዙም ሳይቆይ ትዊቱን አጥፍቶታል።

አይሪሽ ታይምስ ተመድ ለሰራተኞቹ የላከውን መልዕክት ሊክደው እንደማይችል እና ማስረጃውም በእጁ ላይ እንዳለ ገልጿል።

በሌላ በኩል የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲሚትሮ ኩሌባ በትዊተር ገፃቸው ላይ ክሬምሊን ሩስያ ላይ " ጦርነት " እና " ወረራ " የሚሉትን ቃላት ጥቅም ላይ እንዳይውሉ እንዳገደችው ሁሉ ተመድም ይህን ያደርጋል ብሎ ማመን እንደከበዳቸው ገለፀው ፤ እንደዚህ ያሉ ዘገባዎች ውሸት ከሆኑ በፍጥነት ውድቅ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

በዚሁ ትዊት ስር የተመድን ኮሚኒኬሽን እመራለሁ ያሉት ሜሊሳ ፍሌሚንግ ፤ አንዳድን ቃላቶችን አትጠቀሙ በሚል ለዓለም አቀፍ ሰራተኞች የተላለፈ ይፋዊ መልዕክት የለም ብለዋል።

Tikivah news

Address

Adama
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hanaze media ሀናዜ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hanaze media ሀናዜ ሚዲያ:

Share