PR Department Getachew

PR Department Getachew Ethiopian communications authority is a legal entity that registers and regulates all types of commu

23/05/2022
፟ በስነ ምግባር የታነፀ አመራር ከሙስና ለፀዳች ኢትዮጵያ ፟የባለስልጣኑ አመራርና ሠራተኞች ዓለማቀፉን  የፀረ- ሙስና ቀን ህዳር 30/ 2014 ዓ/ም በተቋሙ የመሰብሰቢያ አዳራሽ አከበሩ።  ...
10/12/2021

፟ በስነ ምግባር የታነፀ አመራር ከሙስና ለፀዳች ኢትዮጵያ ፟
የባለስልጣኑ አመራርና ሠራተኞች ዓለማቀፉን የፀረ- ሙስና ቀን ህዳር 30/ 2014 ዓ/ም በተቋሙ የመሰብሰቢያ አዳራሽ አከበሩ።
የባለስልጣን መ/ቤቱ የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ባዘጋጀው በዚሁ በዓል ላይ ዋና ዳይሬክተሩ ኢንጂነር ባልቻ ሬባ እና ም/ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ሚሊዮን ሃይለሚካኤል እንዲሁም አጠቃላይ ሰራተኞች የተገኙ ሲሆን ዋና ዳይሬክተሩ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ሙስና ሀገራት ሊያገኙ የሚገባቸውን ጥቅም የሚያሳጣና ዕድገትን የሚፈታተን በመሆኑ አጥብቀን ልንጠላውና ልንርቀው እንደሚገባ ገልፀው ሁላችንም እንደመንግስት ሰራተኛ የአገልጋይነት መንፈስን በመላበስ ህብረተሰቡን በንፁህና ቅን ልቦና ማገልገል አለብን ብለዋል።
የባለስልጣን መ/ቤቱ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሠለሞን ኪዳኔ ከሙስና ጋር የተያያዘ ሰፊ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ሙስና ሀገራቀፍ ብቻ ሳይሆን በዓለማቀፍ ደረጃም የልማትና የዕድገት ፈተና ሆኖ እንደቀጠለ ያለ መሆኑን ገልፀዋል።
ዳይሬክተሩ አያይዘውም ሀገራት የህግ ማዕቀፎቻቸውን ተግባራዊ በማድረግና ሙስናን የሚፀየፍ ትውልድ በማፍራት ሊከላከሉትና በእጅጉም ሊቀንሱት እንደሚችሉ አብራርተዋል።
ከቀረበው ሰነድ በማስከተልም ግልፅ ባልሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው በዋና ዳይሬክተሮቹና የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል።
በመጨረሻም አጠቃላይ ሠራተኞቹና አመራሮቹ ምዕራባውያን በኢትዮጵያና በአፍሪካም ላይ መልሰው ሊጭኑት የሚፈልጉትን እጅ የመጠምዘዝና እኛ የምንለውን ብቻ ስሙ ጩኸት ለማስቀልበስ በዓለማቀፍ ደረጃ ሲካሄድ በቆየው # በቃ ( # No more) ንቅናቄ መቀላቀላቸውን በይፋ አሳውቀዋል።

ሁለተኛው የቴሌኮም አገልግሎት ፈቃድ የጨረታ አሸናፊ በቅርቡ እንደሚገለጽ ታወቀ፡፡    መንግስት የቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፉን ለውድድር ክፍት ለማድረግ በወሰነው መሠረት ዘርፉን የሚቀላቀሉ ሁለት ኩ...
01/11/2021

ሁለተኛው የቴሌኮም አገልግሎት ፈቃድ የጨረታ አሸናፊ በቅርቡ እንደሚገለጽ ታወቀ፡፡
መንግስት የቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፉን ለውድድር ክፍት ለማድረግ በወሰነው መሠረት ዘርፉን የሚቀላቀሉ ሁለት ኩባንያዎች ለ15 ዓመታት አገልግሎቱን ማቅረብ የሚችሉበት ፈቃድ ለመስጠት በ2013 ዓ/ም በወጣው ጨረታ ግሎባል ፓርትነርሺፕ እና ኤም ቲ ኤን የተባሉት ኩባንያዎች ተወዳድረው ግሎባል ፓርትነርሺፕ ፎር ኢትዮጵያ የተባለው የኩባንያዎች ጥምረት አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ባልቻ ሬባ እንደገለጹት ሁለተኛውን የቴሌኮም አገልግሎት ፈቃድ ለመስጠት መስከረም 18 ቀን 2014 ዓ/ም የወጣው ጨረታ አሸናፊ የሚሆነው ኩባንያ በመጪው ጥር ወር ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡
እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለጻ የቴሌኮም አገልግሎት ፈቃድ ለመስጠት በወጣው ጨረታ ለ126 ዓመታት ተይዞ የነበረውን የኢትዮጵያ የቴሌኮም ኢንዱስትሪ የተቀላቀለው ግሎባል ፓርትነርሺፕ ፎር ኢትዮጵያ ‘ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ‘ በሚል ስያሜ አራት ታዋቂ የግል የቴሌኮም ኩባንያዎችን ይዞ ያሸነፈበትን 850 ሚሊዮን ዶላር ለመንግስት በማስገባት ወደ ስራ እንደገባ አብራርተዋል፡፡
ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ በመጪዎቹ 3 እና አራት ወራት ውስጥ ወደ ስራ እንደሚገባ የገለጹት ኢንጂነር ባልቻ ሬባ ኩባንያው ዓለም የደረሰበትንና ዘመናዊ የተባለውን የኢንተርኔት አገልግሎት በማቅረብ ተወዳዳሪ ለመሆን መዘጋጀቱን እንደገለጸ ተናግረዋል፡፡

31/10/2021

Welcome to Ethiopian Communications Authority official face book page

Address

Addis Ababa
1000

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when PR Department Getachew posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to PR Department Getachew:

Share