12/06/2026
ዴላን አደረገው፤ ኢትዮጵያዊው ተስፈኛ የእግርኳስ ተጫዋቹ አማን በእንግሊዝ አካዳሚ ዕድል አገኘ
በዛሬው እለት በተሰማው ዜና መሠረት የአንድ ኢትዮጵያዊ ተስፈኛ እግርኳስ ተጫዋች ህልም እውን ሊሆን የዳር ለመድረሱ ማረጋገጫ ተሰምቷል።
ከጥቂት ሳምንታት በፊት ኢትዮጵያ መጥቶ የነበረው ታዋቂው የዜና አንባቢ ዴላን ፔጅ ቃል በገባው መሠረት አማንን ከህልሙ ማገናኘቱን ከደቂቃዎች በፊት ይፋ አድርጓል።
ዛሬ አሜን በዚህ ክረምት ወደ ዩናይትድ ኪንግደም (UK) በማቅናትበቦልተን ዎንደረርስ አካዳሚ (Bolton Wanderers Academy) በሚካሄድ ውድድር ላይ የመሳተፍ ዕድል እንደተሰጠው ተነስተው ተናግሯል።
ዛሬ ህልሙ እውን ሆኗል።ለአሜን ይህንን ዕድል ስለሰጠው ከ SMS Pro Soccer ለሆነው ለማርክ ሄይስ (Mark Hayes) ትልቅ ምስጋና ይግባውም ብሏል ዴላን።
ውሎ አድሮ፣ አንዳንድ ጊዜ ለአንድ ሰው የሚያስፈልገው አንድ አጋጣሚ ብቻ ነው።በአንተ እንተማመናለን አሜን ሲል በኢትዮጵያዊው ወጣት ያለውን ተስፋ በመግለፅ እንደምታኮራንም እናውቃለን፤ በቅርቡ እንገናኛለን ሲልም አረጋግጧል።
ዴላን ዕድሉ ይገኝ እንጂ አስፈላጊ የሆኑ ወጪዎችን እሸፍናለሁ ማለቱን ዶች ኤችዲ መዘገቡ ይታወሳል።
ዶች ኤችዲ