ምሥራቅ ተረፈ - Misrak Terefe

ምሥራቅ ተረፈ - Misrak Terefe ጦቢያ ግጥም በጃዝ አዘጋጅ
(3)

በአብሳሪ መልአክ ቁልቢ ገብርኤል ፣ ዕንባችን የታበሰ ስዕለታችን የደረሰ ፡ የደጁን በረከት የተቋደስን ውለታውን አንዘነጋም ። ለምስጋና በዘመናት መሀከል ለቁልቢ የሰጠነው ስጦታ ሁሉ ለራሱ ሳ...
23/06/2026

በአብሳሪ መልአክ ቁልቢ ገብርኤል ፣ ዕንባችን የታበሰ ስዕለታችን የደረሰ ፡ የደጁን በረከት የተቋደስን ውለታውን አንዘነጋም ።
ለምስጋና በዘመናት መሀከል ለቁልቢ የሰጠነው ስጦታ ሁሉ ለራሱ ሳያስቀር በቅርባችን ባሉ ክርስቲያናዊ ተቋማት ሁሉ ተመስርተውበት ፣ተገድመው አሻራውን ስናይ ለካ ቁልቢ ገብርኤል አንድ አይደለም ዕልፍ እንጂ!!!

ኑ ወደ ቁልቢ ገብርኤል እንሂድ ቤቱን እናድስ አርሲ ጠለታ ገብርኤልን እንገንባ !!!

23/06/2026
22/06/2026

ሚኒሊክ እና ቴዎድሮስ በቴክኖሎጂ ረቀው እየመጡ ነው ። ሮቦት ፣ ኤ አይ ፣ ኮዲንግ ፣ ዌብሳይት ፣ ሲሙሌሽን እንደቀላል ሲያቀላጥፋት ማየት ከስብራት ይጠግናል በሀገር ላይ ያለንን ተስፋ ይቀጥላል ።

ልጅነታቸውን እየኖሩባት ደግሞም የተሰጣቸውን ልዩ እውቀት እንዲጠቀሙበት የሁላችን ሀላፊነት ነውና በሚያስፈልጋቸው ሁሉ አብረናቸው እንቁም ሀገር እንስራ ።

ከገብርኤል - ለገብርኤል አዎ ቁልቢ ገብርኤል ሀብታም ነው።ለብዙ አህጉረ ስብከት አብያተ ክርስቲያናት ፣ አድባራትና ገዳማት፣የአብነት ት/ቤቶች፣ መንፈሳዊ ኮሌጆች እና በርካታ መሰረተ ልማቶች ...
22/06/2026

ከገብርኤል - ለገብርኤል

አዎ ቁልቢ ገብርኤል ሀብታም ነው።ለብዙ አህጉረ ስብከት አብያተ ክርስቲያናት ፣ አድባራትና ገዳማት፣የአብነት ት/ቤቶች፣ መንፈሳዊ ኮሌጆች እና በርካታ መሰረተ ልማቶች መመስረት ምክንያት ሆኗል።

አሁን ተራው የአርሲ ጠለታ ገብርኤልን ማስገንባት እና በእድሳት ላይ ያለውን ቁልቢ ገብርኤል ማጠናቀቅ ነው ።

የቀጥታ ሥርጭት ቀናት
ከሰኔ 18-22
ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ

CBE ንግድ ባንክ 1000759706165
- ⁠Awash አዋሽ ባንክ 013521749645300
- ⁠Abyssinia አቢሲኒያ ባንክ 2556 02373
- ⁠Dashen ዳሸን ባንክ 517116 3880011
- ⁠Hibret ሕብረት ባንክ 109071323 4152990
- ⁠COOP ኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ 1063900050599
- ⁠Ahadu አሐዱ ባንክ 0093543501901
- ⁠Abay አባይ ባንክ 18411129 58315015
- ⁠Anbesa አንበሳ ባንክ 00313350582
- ⁠Amhara አማራ ባንክ 99000 50109805

21/06/2026

በድል ጉዞ ወደ ቅድስት ሀገር እየሩሳሌም

ድል አስጉብኚና የጕዞ ወኪል

ከገብርኤል ለገብርኤል ታላቁ የቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ዓመቱን ሙሉ ሕዝበ ክርስቲያን የማይለየው በተለይም የታህሣስ እና ሐምሌ ዓመታዊ በዓላት ደግሞ እጅግ በርካታ ምዕመን የሚጎርፍበት ስዕለቱ የ...
20/06/2026

ከገብርኤል ለገብርኤል

ታላቁ የቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ዓመቱን ሙሉ ሕዝበ ክርስቲያን የማይለየው በተለይም የታህሣስ እና ሐምሌ ዓመታዊ በዓላት ደግሞ እጅግ በርካታ ምዕመን የሚጎርፍበት ስዕለቱ የሞላለትና እንዲሁ ለተራዳኢነቱ ፍቅሩን ለመግለጥ በሚመጣ ህዝብ የሚጥለቀለቅበት ገዳም ነው ።

እንደየአቅማችንም የምንለግሰው ስዕለት አስራት በኩራት ምፅዋትና ሌሎች ስጦታዎቻችን በሙሉ ከ50 ዓመታት በፊት ጀምሮ ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት እንዲተላለፍ ተወስኖ በሚገኘው ጠቅላላ ገቢ በሁሉም አህጉረ ስብኩት ለሚገኙ አድባራትና ገዳማት፣ የአብነት ት/ቤቶች፣መንፈሳዊ ኮሌጆች፣ቅድስት ሥላሴ ዩንቨርስቲ፣አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ኮሌጅ፣ሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ኮሌጅ እና ለሌሎችም የትምህርት ተቋማት መመስረትና ለበርካታ ወቅታዊ ሁኔታዎች እና ቋሚ መሰረተ ልማቶች እንዲውል በመደረጉ ለሁለንተናዊ የቤተክርስቲያን ጉዳዮች ችግር ፈቺ፣ የልማት ተሳታፊ፣ ድርና ማግ ፣ ምሰሶና ማገር ለመሆን በቅቷል።

በእነኚህ ረጅም ዓመታት ለቁልቢ በሰጣችሁት ስጦታ በየአቅራቢያሁ ያሉ የቤተክርስቲያን መሰረተ ልማቶች ሁሉ የቁልቢ ገብርኤል አሻራ ታትሞባቸዋል ።

በእድሳት ላይ የሚገኘው ቁልቢ ገብርኤል በቅርቡ በተለመደው ቤተክርስትያንን የማቅናት ተግባሩ የመቃጠል አደጋ የደረሰበት የአርሲ ጠለታ ገብርኤልን ለማስገንባት በዝግጅት ላይ ይገኛል ።

የቁልቢ ውለታ ያለባችሁ ተቋማት፣ ስዕለታችሁ የተሰማ ፣ በተስፋ የምትጠብቁ ምዕመናን ኑ የዕንባ አባሹ ቁልቢ ገብርኤልን እናድስ የአርሲን ጠለታ እንገንባ ክርስቲያናዊ ግዴታችንን እንወጣ ።

ድጋፍ ለማድረግ፡-

- CBE ንግድ ባንክ 1000759706165
- ⁠Awash አዋሽ ባንክ 013521749645300
- ⁠Abyssinia አቢሲኒያ ባንክ 2556 02373
- ⁠Dashen ዳሸን ባንክ 517116 3880011
- ⁠Hibret ሕብረት ባንክ 109071323 4152990
- ⁠COOP ኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ 1063900050599
- ⁠Ahadu አሐዱ ባንክ 0093543501901
- ⁠Abay አባይ ባንክ 18411129 58315015
- ⁠Anbesa አንበሳ ባንክ 00313350582
- ⁠Amhara አማራ ባንክ 99000 50109805

02/06/2026

የነብርን መንጋ ፍየል ገብቶ ላሰው፡
እንዲህ አይደለም ወይ ጊዜ የጣለው ሰው ።

ብላ ገጠመች

እናት አይዋጁ በ1857 ዓ.ም ገደማ ይህንን በመግጠሟ ነገር ሰሪዎች ንጉሳችን ሚኒሊክን አቃለለች በዛብህን አሞጋገሰች የሚል ክስ መሰረቱባት ። ክሱም ንጉስ ሚኒሊክ በተገኙበት ተነበበ ዳኛውም በሻህ አቦዬ (በአደዋ ጊዜ የተሰዉ) ለዕለት እንጀራዋ ብላ የቀባጠረችው የሚያስከስሳት አለመሆኑንና ከሳሹም የማይረባ ክስ መመስረቱን አይቶ በነፃ እንድትለቀቅ ፈረደ ።
ንጉስ ሚኒሊክም ፍርዱን አፀኑ ። ይልቁንም ዳኛው ዳረጎት ሰጣትና እንደፈለገች እንድትናገር ፈቀደላት ብለው ሰርገው ሀብለስላሤ ዳግማዊ አጤ ሚኒሊክ ያዲሱ ስልጣኔ መስራች በተባለ መጽሀፋቸው ላይ ስለከተቡልን ከ100 ዓመታት በፊት በነበረ የሀሳብ ልዕልና ፡ በገጣሚዋ ፡ በዳኛው ፡ በንጉሱ እንድንደነቅ ምክንያት አገኘን።

ገጣሚ እናት አይዋጁ (እናት አዋጁ )

አርቲስት ሰላማዊት ደስታ ህልፈት በመላው የጦቢያ  አዘጋጆች እና ቤተሰብ  የተሰማንን ሀዘን እንገልጣለን ። ሰላማዊት በጦቢያ መድረክ ከሚያስደምሙን ባለሙያዎች መካከል የምትጠቀስ  ታታሪ ባለድ...
30/05/2026

አርቲስት ሰላማዊት ደስታ ህልፈት በመላው የጦቢያ አዘጋጆች እና ቤተሰብ የተሰማንን ሀዘን እንገልጣለን ።
ሰላማዊት በጦቢያ መድረክ ከሚያስደምሙን ባለሙያዎች መካከል የምትጠቀስ ታታሪ ባለድንቅ ተሰጥኦ ባለቤት ነበረች ።
ለቤተሰቦቿ ፣ ለስራአጋሮቿ ፣ ለአድናቂዎቿ መፅናናትን እንመኛለን ።
የሰላምን ነፍስ በሰላም ታርፍ ዘንድ እንመኛለን ።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ምሥራቅ ተረፈ - Misrak Terefe posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category