GMN ጉራጌ ሚዲያ ኔትዎርክ

GMN  ጉራጌ ሚዲያ ኔትዎርክ የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔር መፍራት ነው

ኢዜማ መንግሥት ለመመሥረት  የሚያበቃ ዕጩ ያስመዘገብኩ ብቸኛው ተቃዋሚ ፓርቲ ብሆንም፣ የምጠብቀውን ውጤት መጥኛለሁ አለ።የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ (ኢዜማ) ዛሬ፣ መጋቢት 19፣...
31/03/2026

ኢዜማ መንግሥት ለመመሥረት የሚያበቃ ዕጩ ያስመዘገብኩ ብቸኛው ተቃዋሚ ፓርቲ ብሆንም፣ የምጠብቀውን ውጤት መጥኛለሁ አለ።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ (ኢዜማ) ዛሬ፣ መጋቢት 19፣ 2018 እያካሔደ ባለው የበይነመረብ ስብሰባ፣ መሪው አቶ ኢዮብ መሣፍንት ኢዜማ 299 ዕጩዎችን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) ዕጩ አድርጎ በማቅረብ መንግሥት ለመመሥረት የሚያስችል ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ ሆኖ ወደ ውድድሩ መግባቱን ገልጸዋል። ሆኖም፣ ባለፈው የ2013 ምርጫ፣ ፓርቲው የተጋነነ ውጤት ጠብቆ እንደነበር አስታውሰው፣ ከዚያ ስህተታችን በመማር በዘንድሮው ምርጫ ግን የተመጠነ ውጤት እንደሚጠብቁ ("managed expectation" እንዳላቸው) ገልጸዋል።

አቶ ኢዮብ አክለውም፣ በዚህ ምርጫ ኢዜማ በፓርላማ መንግሥት መመሥረት የሚያስችል ድምፅ ባያገኝም፣ ያለውን የውክልና ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ በማሳደግ፣ በፓርላማ ትልቁ ተቃዋሚ ፓርቲ ለመሆን አልሞ እንደሚንቀሳቀስ ጠቁመዋል። አቶ ኢዮብ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የመገንባት ሒደትን በአጭር ርቀት ሳይሆን በረዥም ርቀት ሩጫ እንደሚመሰል ተናግረዋል። (ምርጫ 2018 – GMN)
INSIDER'S

ድምፃዊ አቤል ሙሉጌታ ከዘፈኑ ዓለም ራሱን አሰናበተ  | ታዋቂው ወጣት ድምፃዊ አቤል ሙሉጌታ ከዓለማዊ ሙዚቃ (ዘፈን)  ሙሉ በሙሉ መውጣቱንና ወደ ቀድሞ መንፈሳዊ ህይወቱ መመለሱን በይፉ አስ...
31/03/2026

ድምፃዊ አቤል ሙሉጌታ ከዘፈኑ ዓለም ራሱን አሰናበተ

| ታዋቂው ወጣት ድምፃዊ አቤል ሙሉጌታ ከዓለማዊ ሙዚቃ (ዘፈን) ሙሉ በሙሉ መውጣቱንና ወደ ቀድሞ መንፈሳዊ ህይወቱ መመለሱን በይፉ አስታወቀ።

አርቲስቱ ይህንን ውሳኔውን ያስታወቀው በይፋዊው የፌስቡክ ገጹ ሲሆን፣ የዘፈኑን ዓለም "ውስብስብና አጋንንታዊ አሰራር ያለበት" ሲል ገልጾታል።

አቤል ላለፉት ዓመታት በሙዚቃው ዓለም በቆየባቸው ጊዜያት ውስጥ ከፍተኛ ውስጣዊ ትግል ሲያደርግ እንደነበር ገልጿል። በተለይም ከ2005 እስከ 2007 ዓ.ም ድረስ ለሁለት ዓመታት ሙዚቃን አቁሞ እንደነበር አስታውሶ፣ በወቅቱ ወደ ዘፈኑ ዓለም ዳግም መመለሱ ጸጸት እንደፈጠረበት አልሸሸገም።

"ዓለም ውሸት ነው፤ ዝናም ከንቱ ቆሻሻ ነው! የውሸት መልክና የውሸት ፈገግታ ብቻ!" ሲል አቤል አሁን ያለውን አቋም በጽኑ ቃላት ገልጿል።

ድምፃዊው ለውሳኔው መነሻ የሆኑትን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች (2ኛ ጴጥሮስ 2፥22 እና ዕብራውያን 10፥38) በመጥቀስ፣ ወደ ኋላ ማፈግፈግ አብቅቶለታል ብሏል።
ለዚህም ለውጡ የጸለዩለትን ሁሉ አመስግኗል።

አቤል ሙሉጌታ ከዚህ በኋላ ወደ ዘፈኑ ዓለም ዳግም እንደማይመለስና ህይወቱን ለእግዚአብሔር አሳልፎ መስጠቱን በማረጋገጥ መልዕክቱን አጠቃሏል።

መረጃ ሐብት ነው

31/03/2026
30/03/2026

የጉራጌ ማህበረሰብ ተባብሮ የማደግ እሴቶች በማስፋት ዜጎች በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች እንዲተገብሯቸው ተጠየቀ።

, የጉራጌ ማህበረሰብ ተባብሮ ለማደግ ከሚጠቀሟቸው እሴቶች አንዱ ደቦ ወይም ጘዝ ሲሆን ዜጎች ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እንዲረጋገጥ ያስችላቸዋል።

መረጃ ሀብት ነው

 !!​የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ጥራትን ለማስጠበቅ ባደረገው ክትትል፣ የሚከተሉት ተቋማት ከዘርፉ እንዲወጡ ተወስኗል።​ተቋማቱ በዳግም ምዝገባ ስርዓት ውስጥ ባለመግባታቸው እ...
30/03/2026

!!

​የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ጥራትን ለማስጠበቅ ባደረገው ክትትል፣ የሚከተሉት ተቋማት ከዘርፉ እንዲወጡ ተወስኗል።

​ተቋማቱ በዳግም ምዝገባ ስርዓት ውስጥ ባለመግባታቸው እና በተደጋጋሚ (በደብዳቤ፣ በስልክና በአካል) የቀረበላቸውን ጥሪ ባለማክበራቸው።

​ ህጋዊነታቸው ተቋርጧል። እነሱም:-

1 አቢሲኒያ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ
2 አፍራን ቀሎ ኮሌጅ
3 አገው ምድር ቢዝነስ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ
4 አዲስ ፋና ኮሌጅ
5 ቢኤ ኮሌጅ
6 ኡቡንቱ ቢዝነስና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ
7 ፈጣም ኮሌጅ
8 ግሪን የምርምርና የልማት ተቋም
9 ሴንቸሪ ኮሌጅ
10 ኮቻ ኪድማስ የቢዝነስና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ
11 ካንድል ላይት የርቀት ትምህርት ኮሌጅ
12 ቀይ ባህር ኮሌጅ
13 ማራኪ ቴክኖሎጂ እና ቢዝነስ ኮሌጅ
14 ኒው ዲፕሎማት ኮሌጅ
15 ፒቢቲ አፍሪካ ኮሌጅ
16 ኳሊቲ ስኮላር ኮሌጅ
17 ራዲካል ኢንተርናሽናል ኮሌጅ
18 ውቅያኖስ ኮሌጅ
19 የኔታ ኢንጅነሪንግ ኮሌ
20 ቪዥነሪስ የድህረ ምረቃ ኮሌጅ
21 ባቱ ግሎባል ኮሌጅ
22 ባህረ ጥበብ ጤናና ቢዝነስ ኮሌጅ
23 ማይክሮ ቢዝነስ ኮሌጅ
24 ማያ ኮሌጅ
25 ትሪፕል ኮሌጅ
26 ቤታሎጎ ኮሌጅ
27 ቤካ ኮሌጅ
28 ቀስተ ደመና ኮሌጅ
29 ብራይት ቪዥን ኮሌጅ
30 ኤ.አር.ቲ ሜዲካል ኮሌጅ
31 ኢሊያስ ኮሌጅ
32 ሳይፕሮ ኮሌጅ
33 ዳይናሚክ ኮሌጅ
34 ግራንድ ማርክ ኮሌጅ
35 ዱርማን ኮሌጅ
36 ህብረት ቴክኖሎጂ ኮሌጅ
37 አይቤክስ ሆቴልና ቱሪዝም ኮሌጅ
38 አይ ኪው ኮሌጅ
39 ገራይ ኮሌጅ
40 ጋላክሲ ቢዝነስና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ
41 ቪዥን ላንድ ኮሌጅ
42 መራ ሄመንገድ ኮሌጅ
43 ዩናይትድ ኦሮሚያ ኮሌጅ
44 ኢንተርናሽናል ሊደርሺፕ ኮሌጅ
45 ሲምለስ የርቀት ትምህርት ኮሌጅ
46 ዛክቦን ኮሌጅ
47 ኤም ኤስ ኤል ጂ ኮሊጅ
48 ስሪሳይ ኮሌጅ
49 ፋም ኮሌጅ
50 ስማርት ቢዝነስና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ
51 ሊድስታር ኮሌጅ ኦፍ ቢዝነስና ሊደርሺፕ
52 ዳሎል የቲክኖሎጂና ቢዝነስ ኮሌጅ

የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን

መረጃ ሀብትሽ ነው

የወልቂጤ የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ጣቢያ ስርጭት ተቋረጠ   በደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ስር የሚገኘው የወልቂጤ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች፣ ከመስከረም 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባ...
30/03/2026

የወልቂጤ የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ጣቢያ ስርጭት ተቋረጠ

በደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ስር የሚገኘው የወልቂጤ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች፣ ከመስከረም 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መሆን የነበረበት የደመወዝ ማሻሻያ አልተደረገልንም በሚል ከመጋቢት 16 ጀምሮ የሥራ ማቆም አድማ አድርገዋል።

ሠራተኞቹ በጻፉት ደብዳቤ፤ "ሌሎች አቻ ቅርንጫፎች ጥቅማጥቅሙ ተከብሮላቸው እኛ ጋር ግን ምላሽ የሚሰጥ አካል ጠፋ" ብለዋል።

በከፍተኛ የኑሮ ውድነት ምክንያት ልጆቻቸውን ከትምህርት ቤት እስከማስወጣት መገደዳቸውንና ማህበራዊ ሕይወታቸው መቃወሱን በምሬት ገልጸዋል።

በአማርኛ፣ በቀቤንሲኛ፣ በየሚኛ፣ በጉራግኛና በማረቂኛ ቋንቋዎች የሚተላለፈው ስርጭት ጥያቄያቸው ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ ተቋርጦ እንደሚቆይ ሠራተኞቹ በፊርማቸው አረጋግጠዋል።



#ኢትዮጵያ #ወልቂጤ #ዜና

በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በክልሉ የፀጥታው ሀይሎች እየደረሰባቸው  ያለውን ጥቃት እንዳስመረራቸው ነዋሪዎቹ ገለፀ።አንዳንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉት የመረጃ ምንጫችን በወልቂጤ ከተማ የክ...
30/03/2026

በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በክልሉ የፀጥታው ሀይሎች እየደረሰባቸው ያለውን ጥቃት እንዳስመረራቸው ነዋሪዎቹ ገለፀ።

አንዳንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉት የመረጃ ምንጫችን በወልቂጤ ከተማ የክልሉ የፀጥታ ሀይሎች በከተማው ላይ እየፈፀሟቸው ያሉት ተግባራት በህብረተሰቡ ዘንድ ትልቅ ቅሬታ እየፈጠረ ይገኛል።

በነፃነት የመንቀሳቀስ መብት ከመንጠቅ ባለፈ ከቀቤና ልዩ ወረዳ የጸጥታ አባላት ጋር በመተባበር በከተማው ነዋሩ አላስፈላጊ ሽብርና ወጣቶች አካባቢው ለቀው እንዱወጡ የማሰርና የማስፈራራት ወንጀል ይፈፀምበታል ብለዋል።

የክልሉ መንግስት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መረጃ እንዲደርሰው ቢደረግም መፍትሔ እያመጣ ባለመሂኑ ህዝቡ ለደህንነቱ ሱል መስዋዕት ለመሆን እንደሚገደድ አስረድተዋል።

በመሆኑም ይህንን ጉዳይ አገርሽቶ ወደ ለየለት አመጽ ከመገባቱ በፊት መንግስት ተገቢው ህግ የማስከበር ስራ መስራት ይኖርበታል ብለዋል።

"መረጃ ሀብት ነው"

🙏"ጉራጊኛ  - አማርኛ መዝገበ ቃላት "🙏❤ስንቶቻችን ነን እነዚህ የጉራጊኛ ቃላት በደንብ የምናውቃቸው?______________________________________❤ዘፈረታ     =  ሥር መ...
24/03/2026

🙏"ጉራጊኛ - አማርኛ መዝገበ ቃላት "🙏

❤ስንቶቻችን ነን እነዚህ የጉራጊኛ ቃላት በደንብ የምናውቃቸው?
______________________________________

❤ዘፈረታ = ሥር መሠረቱ

❤ ፍርቱስ = ቅጥ ያጣ; ምስቅልቅል

❤ሽሙቸር = ምስጢር; የተደበቀ

❤ስሁረነ = ቀበጥ

❤ወራ ግብር = ድንግል ሴት

❤ሳካ = ቅሬታ; ጉድለት

❤ጭሽወር = ማገገሚያ

❤ጃርየ = ጓደኛ; ሽርክ

❤ወርቃ ትትብር =ስትፈነጥዝ;ስትደሰት

❤ወገት/ወገርድኤማ = አደባባይ

❤ሸት = አፈርን ማስተካከል/መደልደል

❤ኸሞሪም = ተጌጠ; ተሽቆጠቆጠ

❤ኬት = ራሱን ያልቻለ; ጥገኛ

❤ቴመኩኩን = ቅር ሳይለው

❤ተኽጠቦም = ተደፋፈሩ; ፎከሩ

❤ሸመነ = ቤት የሚያርፍበት ቦታ

❤ምራጎዛ = አገልግል

❤አገዶት = ማስታመም;በሽተኛን መንከባከብ

❤ተባዴ = ሚስት የሚለዋውጥ/እያገባ የሚፈታ

እናንተም ጨምሩበት🙏
@ተኬነት አጂነት

14/12/2025

እድግ በሉ

  ታሪክ ውስጥ ትልቅ አሻራ ካኖሩ  #የጉራጌ ባለሃብቶች መካከል ♦=== ? ►►►►►►►►►►► #ቀኝ አዝማች ሞላ ማሩ ከአባታቸው አቶ ማሩ ዶሬና ከእናታቸው ከወ/ሮ ዳዊቴ ሁሉቃ ሶዶ  #ጉራጌ...
14/12/2025

ታሪክ ውስጥ ትልቅ አሻራ ካኖሩ #የጉራጌ ባለሃብቶች መካከል ♦
===
?
►►►►►►►►►►►
#ቀኝ አዝማች ሞላ ማሩ ከአባታቸው አቶ ማሩ ዶሬና ከእናታቸው ከወ/ሮ ዳዊቴ ሁሉቃ ሶዶ #ጉራጌ ባይመል ዋጮ ፉሌ ቀበሌ ውስጥ 1918 ዓ.ም ተወለዱ፡፡

#በተወለዱበት ቀበሌ በቄስ #ትምህርት ቤት የዘመኑን የሀይማኖት ትምህርት የተማሩ ሲሆን ከተወለዱበት የገጠር ቀበሌ ወደ #አዲስ አበባ እንዲመጡ ምክንያት የሆኗቸው አባትየው ነበሩ፡፡

#ነጋዴ የነበሩት አባታቸው ማሩ ዶሬ በጨርቃ ጨርቅ፣ ድርና ማግ ስራ ተሰማርተው ነበር፡፡ ሞላ ማሩ ወደ አዲስ አበባ እንደመጡ በሱቅ በደረቴ ስራ የንግዱን አለም የተቀላቀሉ ሲሆን በየጎዳናው እያዞሩ መሸጥ ጀመሩ፡፡ ከዚያም ብዙም ሳይቆዩ ወደ ተለያዩ ጠቅላይ ግዛቶች ሸቀጣ ሸቀጥ እየወሰዱ መሸጥ ጀመሩ፡፡ ይህንኑ ስራ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች በተለይ ዲላ፣ ይርጋለምና ይርጋ ጨፌ ተመላልሰው ብዙ ሰርተዋል፡፡ ከትውልድ ቀዬያቸው ከወጡ በኋላ ከአዲስ አበባ ቀጥሎ ለስራና ለመኖሪያነት የመረጡት ሁለተኛ ቦታ #ሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት ነበር፡፡

#መርካቶን በመመስረት ሂደት ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ የተወጡት ቀኝ አዝማች ሞላ ማሩ ከመርካቶ ምዕራብ #ሆቴል እስከ ሰባተኛ፣ አብነትና ጭድ ተራ መሀል የሚገኘው አካባቢ በስማቸው የተሰየመላቸው ሲሆን አካባቢው እስከዛሬ በስማቸው ይጠራል፡፡ በዚህ በስማቸው በሚጠራው ሰፈር አንድ አረቄ ፋብሪካ፣ አንድ ሆቴልና በርካታ ሱቆች ከፍተው እንደ ነበር ታሪካቸው ያስረዳል፡፡

#በ1940ዎቹ ከንግዱ ጎን ለጎን ወደ #ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሸጋገሩ ሲሆን ዲላ ከተማ ላይ የማምረት አቅሙ አነስተኛ የሆነ የአረቄ ፋብሪካ በመክፈት የኢንዱስትሪን ዘርፍ ተቀላቀሉ፡፡

#የህይወት ዘመናቸው አብዛኛውን ያሳለፉት በንግድ ስራና ኢንዱስትሪዎችን በማቋቋም ሲሆን ለተወሰነ ጊዜ በዲላና አካባቢው የሸቀጣ ሸቀጥ ንግዱና የአረቄ #ፋብሪካ ገንብተው አረቄ የማምረት ስራ ከሰሩ በኋላ ሲዳሞ ክፍለ ሀገር ውስጥ የነበራቸውን ቢዝነስ ሙሉ በሙሉ በመተው ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ፡፡

#ወደ አዲስ አበባ ከተመለሱ በኋላ ከአንድ ጓደኛቸው ጋር በጋራ ‘‘የሀረር ሶዳ’’ በሚል ስያሜ የለስላሳ መጠጥ ፋብሪካ አቋቋሙ፡፡ በዚሁ ስራ እስከ 1951 ዓ.ም ከቆዩ በኋላ ከጓደኛቸው ጋር ካቋቋሙት የሽርክና ስራ ወጥተው በግላቸው የምግብ ዘይት ፋብሪካ ከፈቱ፡፡ #ንግዱንና ኢንደስትሪውን እያጣጣሙ በማስኬድ ስኬታማ የሆኑት ቀኝ አዝማች ሞላ ማሩ ከሁለት ዓመት በኋላ በ1953 ዓ.ም አሁን አብነት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በስማቸው የሚጠራ አረቄ ፋብሪካ ከፈቱ፡፡

#የንግድና የኢንዱስትሪ ስራቸውን በማስፋት በ1960 ዓ.ም አሁን አብነት በሚባለው ሰፈር ላይ አብነት ሆቴል ከፈቱ፡፡ ከሚባለው ሰፈር በተጨማሪ ዛሬ አብነት ተብሎ የሚጠራው አካባቢም የሳቸውን አብነት ሆቴል ተከትሎ የተሰጠ ስያሜ መሆኑን ታሪክ ያስረዳል፡፡

#ከልጅነት እድሜያቸው አንስቶ የኢንዱስትሪ ማቋቋም ዝንባሌ የነበራቸው ቀኝ አዝማች ሞላ ማሩ በመቀጠል በ1966 ዓ.ም የረጲ #ብሎኬት ፋብሪካን አቋቋሙ፡፡

#በማስከተል #የኮንስትራክሽን ድርጅት ለመመስረት መኪኖችና ማሽነሪዎች አስገብተው የነበረ ቢሆንም በተለያዩ እንቅፋቶች ምክንያት ስራውን መጀመር ሳይችሉ ቀርተዋል፡፡ ሌላው ጀምረውት ያልተሳካላቸው ነገር ከባለቤታቸው አባትና ወንድሞች ጋር በጋራ በአባያ #ሀይቅ ዙሪያ ጀምረውት የነበረው #ዘመናዊ እርሻ በ1966ቱ የመንግስት ለውጥ ምክንያት ፍሬያማ ሳይሆን ቀርቷል፡፡

#የ1966ቱ አብዮት ተከትሎ ስልጣን የያዘው #ደርግ እንደ ሌሎች ባለሀብቶች ሁሉ ሞላ ማሩንም አብነት ሆቴልን ጨምሮ አብዛኞቹ ንብረቶቻቸው ወርሷቸዋል፡፡

#ሞላ ማሩ በተሰማሩባቸው የስራ መስኮች ለሀገራቸውና ለወገናቸው ላበረከቱት በጎ አስተዋጽኦ በ1964 ዓ.ም የኢትዮጵያ መንግስት የሀገሪቷ ትልቁ #ሽልማት የሆነውን ኒሻንና የቀኝ አዝማችነት ማዕረግ አበርክቶላቸዋል፡፡ በዚህ ሁሉ ስኬት ውስጥ ያለፉት ቀኝ አዝማች ሞላ ማሩ በ1972 ዓ.ም በህዳር ወር በተወለዱ በ54 ዓመታቸው ያረፉ ሲሆን ቀብራቸው #በቅዱስ ዮሴፍ ቤተ-ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡

▼ምንጭ- የብርሃኑ ሰሙ ‘‘ከእንጦጦ ሀሙስ ገበያ እስከ መርካቶ’’ መጽሐፍ፣ ገበያው ጋዜጣ ቅጽ 1 ቁ 2 - 1988፣ የጥበቡ በለጠ ኢትዮያዊ ስንክሳር ዶክመንተሪ!

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when GMN ጉራጌ ሚዲያ ኔትዎርክ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to GMN ጉራጌ ሚዲያ ኔትዎርክ:

Share

Category