Gurage Fact Page

Gurage Fact Page ትግላችን ከጉራጌ ለጉራጌ በጉራጌ !!!

 !  !በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው እና ልዩ አማካሪያቸው ንጉሴ አስረስ የሚመራው አምባገናዊነት የሕግ የበላይነት እየተሸረሸረ፣ የዜጎች መሠረታዊ መብት በባለሥ...
16/04/2026

!
!

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው እና ልዩ አማካሪያቸው ንጉሴ አስረስ የሚመራው አምባገናዊነት የሕግ የበላይነት እየተሸረሸረ፣ የዜጎች መሠረታዊ መብት በባለሥልጣናት ፍላጎት ሥር እየወደቀ ይገኛል።

:- በቡታጅራ ከተማ ነዋሪ በሆኑት በአቶ ሐሰን ከድር ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍ ነው። አቶ ሐሰን ከድር ያላንዳች በቂ ምክንያትና የሕግ አግባብ ታስረው ለረጅም ጊዜ ሲንገላቱ ቆይተዋል።

አቶ ሐሰን ከድር:- ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው የታሰሩበት መንገድ ከመነሻው ህገ-ወጥ የሆነ፣ ያለ መከሰስ መብታቸው ያልተነሳ መሆኑ፣ የቀረበባቸው ክስ መነሻ የሌለው መሆኑ ተረጋግጦ፣ ፍርድ ቤቱ በነፃ እንዲሰናበቱ ቢወሰንም፣ የሕግ የበላይነትን የማይቀበሉ አካላት ውሳኔውን ጥሰዋል።

አቶ ሃሰን ከድር:- ከፍርድ ቤት ነፃ ተብለው መውጣት ሲገባቸው፣ የትም ተደርጎ የማያቅ በባለ ሥልጣናት ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሃይል እርምጃና እንግልት ዳግም ተይዘው እንዲታሰሩ ተደርጓል።

በሹማምንታት ግፍና ጭቆና እየደረሰባቸው ያለው አቶ ሐሰንን ከድር፣ አቶ ቶፊቅ አወል፣ አቶ ፈይሰል አወል እና አቶ ሸይቾ ኢብራሂም ከመኖሪያቸው ቡታጅራ ተነጥለው ወደ ሆሳና በመጫናቸው ምክንያት ለመጠየቅና ጉዳያቸውን ለመከታተል የሚሄዱ ቤተሰቦችና ወዳጆች ከፍተኛ እንግልት እየደረሰባቸውና ላላስፈላጊ ወጪ እየተዳረጉ ይገኛል።

? አንድ ዜጋ በፍርድ ቤት ነፃ ከተባለ በኋላ በፖለቲካ ሹማምንት ትዕዛዝ ታፍኖ መወሰዱ "ከሕግ በላይ ነን" የሚሉ አካላት መኖራቸውን ያሳያል። ሕገ-መንግሥቱ የሚሰጠው መብት በተግባር ካልተከበረ ፍትሕ የት ትገኝ?

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ በቡታጅራ ከተማ ነዋሪ በሆኑት በአቶ ሐሰን ከድር፣ በአቶ ቶፊቅ አወል፣ በአቶ ፈይሰል አወል እና ሸይቾ ኢብራሂም ላይ እየተፈጸመ ያለውን የሕግ መጣስና እንግልት የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለማሳወቅ እንወዳለን።

#ጥሪያችን፦
1➧ የሚመለከታቸው የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት የፍርድ ቤቱን ውሳኔ አክብረው አቶ ሐሰን ከድርን በአስቸኳይ እንዲፈቱ።

2➧ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ይህንን ሕገ-ወጥ ድርጊት እንዲከታተሉትና ድምፅ እንዲሆኑ።

3➧ ፍትሕ ወዳድ ዜጎች ሁሉ ይህንን ግፍ ለዓለም እንዲያሳውቁ ጥሪ እናቀርባለን።

!
!
!

የጭቁኑ የመስቃን ህዝብ ድምፅ!

 !! !!የፍትህ ስብራት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የህግ የበላይነት ወይስ የባለስልጣናት ጉልበት?በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው እና ልዩ አማካሪያቸው ...
16/04/2026

!!
!!

የፍትህ ስብራት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የህግ የበላይነት ወይስ የባለስልጣናት ጉልበት?

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው እና ልዩ አማካሪያቸው ንጉሴ አስረስ እየታየ ያለው ድራማ መሰል የእስር ሂደት "ህግ አለ ወይ?" የሚያሰኝ ደረጃ ላይ ደርሷል።

ከቡታጅራ ተነጥለው ሆሳና ከተማ እንዲታሰሩ የተደረጉት አቶ ቶፊቅ አወል፣ አቶ ፈይሰል አወል፣ አቶ ሸይቾ ኢብራሂም እና አቶ ሐሰን ከድር በባለስልጣናት ትዕዛዝ በእስር እየማቀቁ ዛሬ 34ኛ ቀናቸውን ይዘዋል።

!
አቶ ሐሰን ከድር ዛሬ ፍርድ ቤት ቀጠሮ እንደነበረውና ፍርድ ቤት ቀርቦ ከቀረበበት ክስ ነፃ ተብሎ ያለ ምንም ዋስ እንዲለቀቅ ተወስኖ ቢለቀቅም፣ የሆነው ግን እጅግ አሳፋሪ ነው። ግለሰቡ ወደ ቤተሰቡ ለመመለስ መናኸሪያ መኪና እየጠበቀ ባለበት ወቅት፣ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ በረገጡ የፖለቲካ አመራሮች ትእዛዝ ዳግም በቁጥጥር ስር ውሏል።

?
ፍርድ ቤት "ነፃ ነው" ብሎ ያሰናበተውን ዜጋ መናኸሪያ ላይ አድብቶ ማሰር የህግ የበላይነትን መናቅ አይደለምን?

#የክልሉ ባለስልጣናት ከህግና ከፍርድ ቤት በላይ የሚሆኑት እስከመቼ ነው?

#ፖለቲከኞች የፍትህ ስርአቱን እንደ የግል መጠቀሚያ ማድረጋቸው ክልሉን ወደ የት እየመራው ነው?

!
ማንኛውም ባለስልጣንም ሆነ ተቋም ከህግ በታች መሆኑ በህገ-መንግስቱ በግልጽ ተቀምጧል። የፍርድ ቤት ውሳኔን ጥሶ ዜጎችን ማሰር የቀጥታ የሰብአዊ መብት ጥሰትና የስልጣን አላግባብ መጠቀም ወንጀል ነው።
1. ፍርድ ቤት ነፃ ያለው አቶ ሐሰን ከድር በአስቸኳይ ይለቀቅ!
2. ቀሪዎቹ ሶስት ታሳሪዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተፈተው ወደ ቤተሰቦቻቸው ይመለሱ!
3. በንጹሃን ዜጎች ህይወትና ሞራል ላይ እየተቆመረ ያለው የፖለቲካ ቁማር ይብቃ!

#ህግ የሁላችንም መጠለያ ሊሆን ይገባል እንጂ የጥቂት ባለስልጣናት የቂም በቀል መወጫ መሆን የለበትም።

ተፈተህም ነፃ አይደለህም!
ታስረህም ወንጀለኛ አይደለህም!

!
!

 "የመዥገር ፖለቲካ" እና "የመንጠቆ ፖለቲካ" 1. የመዥገር ፖለቲካ (Tick Politics)ይህ ማለት ሲገለፅ ጥገኛነትና ተጠቃሚነት (Parasitism) ላይ ነው። መዥገር በሰውነት ላይ ተ...
16/04/2026



"የመዥገር ፖለቲካ" እና "የመንጠቆ ፖለቲካ"

1. የመዥገር ፖለቲካ (Tick Politics)
ይህ ማለት ሲገለፅ ጥገኛነትና ተጠቃሚነት (Parasitism) ላይ ነው። መዥገር በሰውነት ላይ ተጣብቃ ደም እንደምትመጥ ሁሉ፣ የመዥገር ፖለቲካም በሀገር ወይም በድርጅት ሀብት ላይ ተጣብቆ የግል ጥቅም ማጋበስን ይገልጻል።ንጉሴ ለዘመናት በመስቃን ላይ የተጣበቀ ደም መጣጭ መዥገር ለመሆኑ በዘመናት መካከል የመስቃንን ሞት እንግልት ስደት የሚመጥ መዥገር ነው።

የንጉሴ አስረስ ባህሪው ለህዝብ ወይም ለመስቃን ማህበረሰብ የሚጨምረው እሴት ሳይኖር፣ ከስርአቱ የሚገኘውን ጥቅም ብቻ ማሳደድ ላይ የተጠመደ የዘመናት ደም መጣጭ ሴረኛ ነው።

መስቃን እየሞተ እየተሰደደ ሲሞት ሲሰደድ ሲኖር ንጉሴ አስረስ "መዥገሩ" (ጥገኛ ፖለቲከኛው) ግን እየወፈረ እየተደሰተ እየደለበ ስልጣኑን በመስቃን ስም እያካበተ እየሄደ ይገኛል።

የንጉሴ የመጨረሻ ግቡ መስቃን የሚባል ሕዝብና ግዛት እንዲፈርስ እንዲበታተን እርስ በእርሱ እንዲባላ የሚያደርግ መዥገር ነው ።

2. የመንጠቆ ፖለቲካ (Hook Politics)
ይህ ደግሞ ማጥመድንና ቁጥጥርን (Manipulation and Capturing) የሚያመለክት ነው። አሳ አጥማጅ በመንጠቆው ላይ ማጥመጃ (Bait) አድርጎ አሳ እንደሚያጠምድ ሁሉ፣ ንጉሴ እና እንደሻው ደግሞ የመስቃንን ሕዝብ ወይም ለማጥመድ የሚጠቀሙበት ዘዴ ነው።

የንጉሴ የመንጠቆነት ባህሪው ምስራቅ ጉራጌ ዞን ሲመሰረት የሚጣፍጡ ግን የማይጨበጡ ተስፋዎችን በመስጠቱ፣ ስሜት ቀስቃሽ ንግግሮችን ተጠቅሞ መስቃን እንዲዘክርለት በማድረግ እና ግዚያዊ ጥቅሞችን ዞኑን በመመስረት በማሳየት የመስቃንን ሕዝብ ወደ ፖለቲካዊ ወጥመድ ማስገባት የቻለ እና የምስራቁን እና የምዕራቡን ጉራጌ ለሁለት የሰነጠቀ መንጠቆ ፖለቲከኛ ነው።

ንጉሴ በዚህ በመንጠቆ ፖለቲካ አካሄዱ በመስቃን ላይ የስነ ልቦና ጦርነት የአካልም የመንፈስም የፖለቲካ ጦርነት በማድረግ መስቃን በመሬቱ እንዲሰደድ በፖለቲካው እንዲገፋ እንዲሞት እንዲቆስል ንጉሴ እንደ መንጠቆ ቆልፎ የያዘው ሴጣናዊ የፖለቲካ ስርዓት የፈጠረ ጥቁሩ ጂኒ ነው።

ለዘመናት መስቃን ላይ እየተወዳደረ መስቃንን እንደ ክብሪት እየመታ ያለ የመስቃን የዘላለም ነቀርሳ እና ገዳይ ቡድን ንጉሴ አስረስ መሆኑን አለም እንዲያውቅልን እንፈልጋለን።አንባገነኑ እንደሻው ከንጉሴ ምክር የማይወጣ በአንድ ገበታ የሚሸኑ የእፉኝት ልጆች መሆናቸው የመስቃን ስቃይና መከራ ምስክር ነው።

ስንቱን የመስቃንን ፖለቲከኛ ንጉሴ ቆርጦ የበላ የቀን ጅብ መሆኑን መስቃን በክልል ደረጃም ይሁን በዞን ደረጃ ሰው እንዳይወጣለት ያደረገ መስቃን ላይ የተጣበቀ የመስቃን ጥገኛ ጠላት ንጉሴ አስረስ ነው።

ይህ የመዥገርና የመንጠቆ አካሄዳቸው በመሬት ዝርፊያ ላይ የተደቀነ ከባድ ውንብድናም አለ።

ቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ላይ በዲያስፎራ ሰፈር የሚገነባለት አንባገነኑ እንደሻው በባለ ሀብቱ ረድኤት አሰፋ አማካኝነት ህንፃ እየተገነባለት ይገኛል ቡታጅራ ላይ።የዲሞግራፊክ ለውጥ ፕሮጀክታቸው አንዱ ነው።

መስቃን ስቃይህን መከራህን ለዘመናት የቀበረህን ንጉሴ አስረስን በደንብ እስክታቅ መላ እስክትፈልግ ድረስ ልጆችህ የንጉሴን ተንኮልና መዥገርነት መንጠቆነት በዝርዝር እናሰጣዋለን።

እስኪዘገንናችሁ ድረስ መስቃንን እንዴት እየጮቀናችሁት እንደነበርን አጠናክረን ከመረጃ ጋር እንቀጥላለን።

ፍትህ ለመስቃን

 !!በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰውና የ"ሂላሪ ክሊንተን" ስትራቴጂ በደም እምባ ላይ የሚደረግ የድል ሽሚያ!የፖለቲካ ሰዎች የሕዝብ ድጋፍ ሲርቃቸውና የገቡበት አዙ...
15/04/2026

!!

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰውና የ"ሂላሪ ክሊንተን" ስትራቴጂ በደም እምባ ላይ የሚደረግ የድል ሽሚያ!

የፖለቲካ ሰዎች የሕዝብ ድጋፍ ሲርቃቸውና የገቡበት አዙሪት ሲጠባቸው የማያደርጉት ጥረት የለም። ሂላሪ ክሊንተን በምርጫ ወቅት የደጋፊዎቿ ቁጥር ሲቀንስና ተቃውሞ ሲበረታባት፣ የሕዝቡን ስሜት ለመግዛት ወደ ስታዲየሞች እየሄደች በማጨብጨብ "እኔም ከእናንተ ጋር ነኝ" ለማለት ያደረገችው ሙከራ የብዙዎች መሳለቂያ ሆኖ ነበር። ዛሬ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የምናየው ድራማም ከዚህ የተለየ አይደለም።

ከቤተ እምነት እስከ ስታዲየም፤ የትኛው ነው የልብ ትርታ?
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ባለፉት ወራት የገጠማቸውን ሕዝባዊ ተቃውሞና የቅቡልነት ጥያቄ ለማለዘብ ያልረገጡት ደጅ የለም።
➧ አንዴ ቤተክርስቲያን...
➧ አንዴ መስጂድ...
➧ አንዴ ቸርች...
➧ አሁን ደሞ እስታዲየም...
ይህ ሁሉ ጥረት ግን ከልብ የመነጨ ሳይሆን የፖለቲካ ትኩሳቱን ለማቀዝቀዝ የሚደረግ "የመንፈሳዊ ካባ" ፍለጋ እንደሆነ ግልጽ ነው።

ዛሬ ደግሞ የሀላባ እግር ኳስ ክለብ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማለፉን ተከትሎ፣ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በማጋራት የደጋፊውን ስሜት ለመጋራት እየሞከሩ ነው።

ለመሆኑ ስፖርትና ግድያ አብረው ይሄዳሉ?
በክልሉ ንጹሐን ዜጎች በግፍ እየተገደሉ፣ ወጣቶች ያላግባብ በየእስር ቤቱ እየታጎሩና ሕዝቡ በከፍተኛ የጸጥታ ስጋት ውስጥ እያለ፣ በኳስ ደጋፊ ስም ተሸሽጎ "የሕዝብ ሰው" ለመምሰል መሞከር ተገቢ ነውን?

1. ፍትህ የታለ? ንጹሐን ደማቸው እየፈሰሰ ባለበት ሁኔታ፣ በእግር ኳስ ውጤት የሕዝቡን ቁስል መሸፈን አይቻልም።
2. ፖለቲካዊ ቁማር፡ ስፖርት አንድነትን ይፈጥራል፤ ነገር ግን በፖለቲከኞች እጅ ሲወድቅ የውድቀት መደበቂያ ይሆናል።
3. የሕዝብ ጥያቄ፡ የሀላባ ሕዝብም ሆነ የክልሉ ነዋሪ የሚፈልገው ኳስ ብቻ ሳይሆን ሰላም፣ ፍትህና ነጻነት ጭምር ነው።

በእግር ኳስ ደጋፊ ስም መሸሸግ፣ በሃይማኖት ተቋማት ፎቶ መነሳት የሕዝብን እውነተኛ ጥያቄ አይመልስም። ሕዝቡ የሚፈልገው በፎቶግራፍ የሚታይ መሪ ሳይሆን፣ የንጹሐንን ግድያ የሚያስቆም፣ ፍትህን የሚያሰፍንና ሰላምን የሚያረጋግጥ መሪ ነው።

በሀላባ ድል ደስ ብሎናል እንኳን ደስ አላቹ! የሀላባ ክለብ ድል የሕዝብ ነው! የፖለቲከኞች የውድቀት መሸፈኛ ግን መሆን የለበትም!

እውነተኛ አንድነት በስታዲየም ፎቶግራፍ የሚመጣ ሳይሆን፣ በሕዝቦች መካከል እኩልነትና ፍትሕ ሲሰፍን ብቻ ነው። የሀላባ ወንድሞቻችን የኳስ ድል የናፈቃቸው ያህል፣ የመስቃን ህዝብ ሰላምና ፍትሕም ናፍቆናል!

የጭቁኑ የመስቃን ህዝብ ድምጽ!

 የእንደሻውን ደካማነት በአደም ፋራህ ለማማለልና ለመሸወድ የሚጋጋጠው የክልሉ ሚዲያ የዛሬ አራት ወር በፊት በጥር 05/2018 ላይ አደም ፋራህ የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት ወደ ማዕከላዊ ...
13/04/2026


የእንደሻውን ደካማነት በአደም ፋራህ ለማማለልና ለመሸወድ የሚጋጋጠው የክልሉ ሚዲያ የዛሬ አራት ወር በፊት በጥር 05/2018 ላይ አደም ፋራህ የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት ወደ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጎብኝተው ነበር።በዚህን ጊዜ አደም ፋራህ በተመለከተቱ ጉዳይ ለገፅታ ግንባታ የሚሆን ነገር እንደ ፖለቲከኛ አመራር ፓርቲያቸውም የሰራውን ተግባር አወድሰዋል።

ይህን ንግግር ይኸው ሰርተናል ለማለት የክልሉ ፓርቲ አስር ጊዜ ሚዲያ ላይ እየነገደባት ይገኛል በቪዲዮዋ።

እውነቱ ግን ህዝብን እና መሬት ላይ ያለውን እውነት በ2:00 ደቂቃ ቪዲዮ መቀየር አይቻልም።

እውነታው ክልሉ በእንደሻው የግል አንጋሽነትና አንባገነንነት ክልሉ ውስጥ የእርስ በእረስ ጦርነት መፍታት አቅቶት በልዩ ሃይል የሚተዳደር ብቸኛው ክልል ከሆነ ሰነባብቷል።

ክልሉ ላይ ያለው አንባገነኑ አስተዳደር በአንድ ወገን የስልጣን ካባ የተወጠረው ክልል በፓርቲ ሚዲያ የራሱ ወዳጅ አማካሪው የራሱ በማድረግ ለፕሮፖጋንዳ ማሽንነት የሚጠቀምባቸው ጋኖች ናቸው።

ክልሉ ላይ ፍትህ ከጠፋ ሰነባብቷል።ችግሮች የሚፈቱት በእስር በማሳደድ በግድያ ነው።ኢሰመኮ የሰጠውም ምስክርነት ለዚህ እውነተኛ መረጃ ነው።

መስቃን በክልሉ ውስጥ ግንባር ቀደም የእንደሻው ጥይትና እስር ማብረጃና መለማመጃ ነው የሆነው።

በክልሉ ውስጥ ከ400ሺህ ህዝብ በላይ የያዘውን መስቃንን ያለ አንዳችም ውክልና ባዶ የቀረ የጭቆናው ቀንበር የበዛበት ሕዝብ ሆኗል።እስኪ አንድ መስቃን በወሳኝ ቦታ ላይ አለ ብሎ ይከራከር ማንም የለም።

የመስቃን ሕዝብ በቋንቋዬ ልማር ሲል ከህገ መንግስቱ ውጭ የሚተዳደር ደሴት ተደርጎ በማሰር በማሳደድ በመግደል ተጠምደዋል።

ባህሌን ላልማ ሲል አይ ያንተ ባህል አታለማም በማለት የሀሰት ወሬ በመንዛት ባህሉን ለሌላ አካል ለመስጠት በዚህም በርካታ የመስቃን አመራሮች ወጣቶች ሙህራኖች ለእስር ለሞት ለስደት ተዳርገዋል።ይህ ሁሉ የሚሆነው ለአንባገነኑ ለእንደሻውና ለንጉሴ አስረስ ደስታ ሲባል መስቃን እየተማገደ ይገኛል።

ለእንደሻው ሲባል እንደ ቆሎ መስቃን በልዩ ሃይሉና በማረቆ ፅንፈኛ ገዳይ ቡድን እየረገፈ ይገኛል።ለእንደሻው ሲባል ለንጉሴ ሲባል ቡታጅራ ባለቤት አልባ ከተማ ሆናለች ለእንደሻው ሲባል መስቃን ከቀዬው ከእርስቱ እየተፈናቀለ ይገኛል።

አደም ፋራህ አያውቁትም ነው ወይ ? ሲባል ያውቁታል ለእስትራቴጂ ሲባል ለምጣዱ ሲባል አይጧ እንድታልፍ ተፈልጎ ነው።እንደሻው የተካነው አበባ ምንጣፍና ስጦታን በማበርከት ከፌደራል የመጡ እንግዶችን በስጦታ ገንብቶ ይሸኛል።እውነቱ ግን ይኸው ነው።

የመስቃን ፖለቲካ የእንደሻውን የመኖርና ያለመኖር ሁኔታ የሚወስን ነው።

ፍትህ እንሻለን።

⚖️   ፦  !​በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው እና አማካሪያቸው ንጉሴ አስረስ የሚታየው አምባገነናዊ አካሄድና በፍትህ ስርአቱ ላይ የሚደረገው ጣልቃ ገብነት አሳሳ...
09/04/2026

⚖️ ፦ !

​በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው እና አማካሪያቸው ንጉሴ አስረስ የሚታየው አምባገነናዊ አካሄድና በፍትህ ስርአቱ ላይ የሚደረገው ጣልቃ ገብነት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ያለምንም ወንጀል ከቤተሰቦቻቸውና ከመኖሪያቸው (ቡታጅራ) ተነጥቀው ወደ ሆሳና የተወሰዱት የመስቃን ጉራጌ ተወላጆች፦
1➧ አቶ ፈይሰል አወል
2➧ አቶ ሸይቾ ኢብራሂም
3➧ አቶ ቶፊቅ አወል
​በህግ ጥላ ስር ከዋሉ ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 1/2018 ዓ.ም 26ተኛ ቀናቸውን ይዘዋል። ዛሬ በነበራቸው 4ኛ ዙር ቀጠሮ መሠረት ፍርድ ቤት ቀርበው መርማሪው የዋስትና መብታቸው እንዳይከበር ተጨማሪ ቀጠሮ እንዲሰጠው መከራከሪያ ቢያቀርብም ፍርድ ቤቱ ግራ ቀኙን አይቶ ዋስትና ያሰጣል አያሰጥም የሚለውን ለመወሰን ለ8 ሰዓት ቀጠሮ የሰጠ ቢሆንም 8ሰዓት ፍ/ቤት ቀርበው መዝገቡ እጣ ይውጣበት በሚል ለሚያዝያ7/2018 ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰቶባቸዋል። ይህ የሚያሳየው አሁን መዝገባቸው ከያዘው ዳኛ ነጥቆ እንደፈለገ ለሚታዘዛቸው ዳኛ ለመስጠት መዝገቡ እጣ ይውጣበት በሚል ቀጠሮ መስጠት የፍትህ ስርአቱ እንደፈለጉ ጠምዝዘው እያጨመላለቁት ነው።

መርማሪው አቃቤ ህግ እስካሁን ድረስ የቀረበባቸውን ክስ የሚያረጋግጥ ምንም አይነት ተጨባጭ መረጃ ማቅረብ ባልቻለበት ሁኔታ፣ ፍርድ ቤቱ በባለስልጣናት ቀጥተኛ ትዕዛዝ የዋስትና መብታቸውን ነፍጎ በእስር እንዲንገላቱ እያደረገ ይገኛል።


➡️ የፍትህ ነጻነት ይከበር፦ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና አማካሪዎቻቸው የፍትህ አካላትን በስልጣን ሀይል መጠምዘዝ ያቁሙ! ፍርድ ቤት የፖለቲካ መጫወቻ መሆኑ ይብቃ።

➡️ መረጃ የሌለው ክስ ይቋረጥ፦ አቃቤ ህግ ማስረጃ ማቅረብ ያልቻለባቸው ግለሰቦች በነፃ እንዲሰናበቱና የዋስትና መብታቸው እንዲከበር እንጠይቃለን።

➡️ የቤተሰብ ስቃይ ይብቃ፦ ግለሰቦቹን ከቀያቸው አርቆ በማሰር ቤተሰቦቻቸው ለከፍተኛ እንግልትና ላልተፈለገ ወጪ እየተዳረጉ ነው። ይህ ሰብአዊነት የጎደለው ድርጊት በአስቸኳይ ይቆም!

➡️ ተገቢው ካሳ ይከፈል፦ ያለ አግባብ የታሰሩ ወገኖቻችን በደረሰባቸው ስነ-ልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ተገቢው ካሳ ሊከፈላቸው ይገባል።
​"ህግን የሚጥሱ ባለስልጣናት ራሳቸው ከህግ በላይ ሊሆኑ አይችሉም!"

​የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እና አማካሪያቸው በንፁሃን ዜጎች ላይ እያደረሱ ያለውን አፈና እንዲያቆም እና የህግ የበላይነትን እንዲያረጋግጥ በፅኑ እናሳስባለን። ድምጻችንን ለፍትህ እናሰማ!

የጭቁኑ የመስቃን ህዝብ ድምፅ!!

 #የእንደሰሻው ጣሰው እና የንጉሴ አስረስ ተቃውሞ የማዳከም ሴሴራ ፪1. የመስቃንን ህዝብ መከፉፈል ነው። #ይህ እጅግ የተለመደ ስልት ነው  ሕዝቡ በአንድነት ቆሞ መብቱን እንዳይጠይቅ በዘር ...
07/04/2026

#የእንደሰሻው ጣሰው እና የንጉሴ አስረስ ተቃውሞ የማዳከም ሴሴራ ፪
1. የመስቃንን ህዝብ መከፉፈል ነው።

#ይህ እጅግ የተለመደ ስልት ነው ሕዝቡ በአንድነት ቆሞ መብቱን እንዳይጠይቅ በዘር ፣ በሃይማኖት ወይም በመዋቅር በመከፋፈል እርስ በእርሱ እንዲጠራጠር በማድረግ ተቃውሞውን ለማዳከም መስራት።

# በርግጥ ይህ ስልት እንደ ምስራቅ ጉራጌ ባሉ መዋቅሮች እጅግ አደገኛ ሊባል የሚችል ስልት ነው ምክኒያቱም በህቦች መሀል አለመተማመንን ያነግሳል ቢሆንም ግን እንደ እንደሻው ጣሰው ላሉ ስልጣናቸውን ከህዝብ በላይ ለሚወዱ አምባገነን እና ሀላፊነት ለጎደላቸው መሪዎች በደንብ ያገለግላል።

#ለዚህም ነው ሰሞኑን በምስራቅ ጉራጌ ዞን ያሉ የፓርቲ መሪዎዎች አቶ ንጉሴ አስረስ ተቃውሞ የገጠማቸው ቀጥታ ዶቢ ስለሆኑ ነው እንዳሻው ጣሳው ደግሞ ሶዶ ጉራጌ ስለሆነ ነው በማለት የሚደሰኩሩት ።
# ሌላው ከሀይማኖት ጋር የማያያዝ አፓርታይዳዊ አካሄድ ነው ሲፈልጉ ቸርች ይዘውት ይገባሉ፣ሲፈልጉ ደግሞ ቤተክርስቲያንን ይዘውት ይገባሉ የእነሱ ስልጣን አይነካ እንጂ
ሊደርስ የሚችለው ውድመት ማሰብ እንኳን አይፈልጉም።
#ይህ ሁሉ ግን የሚመነጨው ለመስቃን ህዝብ ካላቸው ጥላቻ አና የህዝቡን ጥያቄ ላለማድመጥ ካላቸው ፍላጉት ነው።

# ህዝቡን በቀጥታ በመንግስት የታጠቀ ሀይል ያስገድሉታል አለፍ ሲልም የታጠቀ ሀይል በሚስጥር አደራጅተው ያስገድሉታል ይሄን ለማስተካከል ማሰብ ግን አይፈልጉም።

#ያለመሪ ሊያስቀሩት መሪዎቹን በሽብልቅ አጀንዳ ያስጨንቁበታል ህዝቡ ተቃውሞ ሲያሰማ የመስቃን ጠንካራ መሪዎች መርጠው ከስልጣን አሸማቀው ያነሱታል አለፍ ሲል ያስሩበታል ያለውክልናም ያስቀሩታል።

#ይህ ሁሉ በደልን ተቃውሞውን ሲያሰማ ለማፈን አንድ ሆኖ እንዳይቆም በመከፋፈል ሰዎች እርስ በእርሳቸው እንዲጠራጠሩ እንዳይተማመኑ በዘር፣በሀይማኖት፣በመዋቅር ገለመሌ እያሉ በመከፋፈል በደል በማለማመድ አንድ ሆኖ አንዳይቆም ያደርጉታል።

#ስለሆነም አፓርታይደዊ የከፍፍለህ ግዛ የሆነው የአቶ እንዳሻው ጣሰው እና ንጉሴ አስረስ አገዛዝ ሳንከፋፈል አንድ ሆነን በመቆም ትግላችን እንቀጥላለን።

# አያቆምም።

#ፍትህ በግፍ ለሚገደሉ፣ፍትህ በማንነት ተመርጠው ለሚታሰሩ፣ፍትህ ያለፍርድ ለሚታሰገሩ፣ለሚገደሉ!!!!!!!!

 ብልፅግና ፓርቲ ከለውጡ በፊት የገመገመው አንዱ ችግር የሀገሪቷ መዋቅራዊ ጭቆና እና ሰው ተኮር ጭቆና የሚል ነበር።ኢህአዴግ ወለዶቹ እንደሻውና ንጉሴ አስረስ ሁለቱንም የጭቆና አይነቶች በማዕ...
07/04/2026



ብልፅግና ፓርቲ ከለውጡ በፊት የገመገመው አንዱ ችግር የሀገሪቷ መዋቅራዊ ጭቆና እና ሰው ተኮር ጭቆና የሚል ነበር።

ኢህአዴግ ወለዶቹ እንደሻውና ንጉሴ አስረስ ሁለቱንም የጭቆና አይነቶች በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እየተገበሩ ይገኛሉ።የፓርቲ ሚዲያን ከ2ሚሊየን እና ከዚያ በላይ ያለውን አባላት የፓርቲ አባላት ንብረት የሆነውን የክልሉ ፓርቲ ሚዲያ እና ከ258k በላይ ያለውን ተከታይ ለአንድ ግለሰብ በነጋ በጠባ የእንደሻው ጣሰው ፕሮፋይል መገንባ ሆኖ አርፎታል።

ይህ አንደኛ መዋቅራዊ ጭቆና ይባላል የፓርቲውን ሚዲያ በመጠቀም የግል መፈንጫ ሆኖ በመዋቅር ደረጃ በተለይም በምስራቅ ጉራጌ ዞን ባሉ መዋቅሮች ከፓርቲው በቀጥታ ትዕዛዝ እየተላለፈ አለፍ ሲልም ደግሞ በመዋቅር ደረጃ የግለሰቡን የግል ስብዕና መገንባ የአክቲቭዝም ፖለቲካ ማካሄጃ እንዲሆን እየሰራ ያለ የተዋረደ ሚዲያ ሆኖ አርፎታል።

ሌላው ሰው ተኮር ጭቆናም የሆነበት በግል ደረጃ በእንደሻው ጣሰውና በጓደኛውና በአብሮ አደጉ የክልል ሚዲያ ኃላፊው አቶ ሰብስቤ ተካ አማካኝነት ሰው ተኮር ጭቆናው በመስቃንና መሰል ጭቁን ሕዝቦች ላይ አሳርፈዋል።ከፓርቲው እሳቤ በመውጣት የግል ዝናና ታሪክ መተረኪያ ሆኖ እንዲያርፍ የፓርቲው ሚዲያ የእንደሻው አክቲቪስት እና ስብዕና መገንቢያ ሆኖ እንዲያገለግል አድርገውታል።

አጠቃላይ የክልሉ አመራር በእንደሻው ስብዕና ግንባታ ላይ እንዲጠመድ በእንደሻው ቀጭን ትዕዛዝ ተሰጥቶ አመራሩ ከልማት አጀንዳው ተነጥሎ ተወጥሯል።

የፓርቲው ሚዲያ የእንደሻው የግል አክቲቪስትነት ወጥቶ የፓርቲውን እሳቤ ልማት የሚያጎሉ ነገሮች እንዲሰራ የፌደራሉ ፓርቲ እንዲፈትሽ እንጠይቃለን።

በአንድ ወገን የተጠረነፈው የፓርቲው ሚዲያ አደብ እንዲገዛ እናሳስባለን።የፓርቲው ሚዲያ ልማትና ፍትህ ላይ መስራት ሲገባው በየቀኑ የግለሰብ የእንደሻው ስብዕና ግንባታ ማዕከልነት መጠመዱን የሚያመላክቱ መረጃዎች ያሳያሉ።

አመራር ስራው ምድር ላይ ሊመሰክር ሲገባው ያልሆነ ስብዕና በሚዲያ ስሜ ጠፋ ስነ ልቦናዬ ተጎዳ በሚል በእንደሻው ትዕዛዝ አመራሩ የእንደሻው የግል አክቲቪስት ሆኖ አርፎታል።አመራሩ የልማት አጀንዳዎችን ከመመለስ ይልቅ ሙሉ ሰዓቱን በሶሻል ሚዲያ የእንደሻው ፕሮፋይል ለመገንባት ጊዜውን እያባከነ ይገኛል።ሰሚ ያጣው ክልል ዶር አብይ እንዲመለከቱት እናሳስባለን።

ሶስት ቀን ባለሞላው ውስጥ ብቻ ከአምስት በላይ ፖስት ያውም በአንድ ቀን እና ባላነሰ ቀናቶች ክልሉ አግላይነትና የግለሰብ መፈንጫ መሆኑን የሚያመላክቱ መረጃዎች ያሳያሉ።

ፍትህ ለታሰሩ እስረኞች።

 !!ማህበራዊ ሚዲያ እንደ አራተኛው መንግስት እና የክልል አስተዳደር ተግዳሮቶችበዘመናዊው የአስተዳደር ስርዓት፣ ማህበራዊ ሚዲያ “አራተኛው መንግስት” በመባል ይታወቃል። ከሦስቱ የመንግስት አ...
04/04/2026

!!

ማህበራዊ ሚዲያ እንደ አራተኛው መንግስት እና የክልል አስተዳደር ተግዳሮቶች

በዘመናዊው የአስተዳደር ስርዓት፣ ማህበራዊ ሚዲያ “አራተኛው መንግስት” በመባል ይታወቃል። ከሦስቱ የመንግስት አካላት (ህግ አውጪ፣ አስፈፃሚና ዳኝነት) በተጨማሪ፣ ማህበራዊ ሚዲያ ለዜጎች አስተያየታቸውን እንዲገልጹ፣ በአመራሮች ላይ ክትትል እንዲያደርጉ እና የህዝብ ጥያቄዎችን እንዲያነሱ መድረክ ይፈጥራል።

በዚህ መልኩ፣ ለማንኛውም የህዝብ ተወካይ ወይም የክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው፣ ህዝብ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚሰነዘሩባቸው ትችቶችን መቀበል የዲሞክራሲ ክብር እና የኃላፊነት መገለጫ ወደ ጎን ብለው፣ በመረጃ በተግባር አምባገነንነታቸው ሲጋለጥ፣ የመምራት ብቃት ማነስ፣ ሚዛናዊነት መጓደል፣ ትችት ሲደርስባቸው ከማስተካከል ይልቅ ወደ መከላከያ ዘዴዎች ማፈግፈግ የመሸነፍ መገለጫ ነው።

በርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው እና አማካሪያቸው ንጉሴ አስረስ ላይ የሚነሱ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች የሚከተሉትን ያካትታሉ፦

1. የርዕሰ መስተዳድሩ የእውቀት ብቃት እና የመምራት አቅም ማነስ፦ የህዝብ አገልግሎት ዘርፍ የፍትህ ስርዓት መዛባት፣ ግፍና ጭቆና እያደገ በሚሄድ ውስብስብ ሁኔታ ውስጥ፣ አመራሮች ዘመናዊ የአስተዳደር እውቀትና ችሎታ ማነስ በክልሉ የፈጠራቸው ቀውሶች የሚቀርቡባቸውን ትችቶች ተቀብሎ ማረም አለመቻል። ይህ ጉድለት በክልሉ ህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ፣ ሰላም ደህንነት እንቅፋት ሆነዋል።

2. የርዕሰ መስተዳድሩ ብልሹ አሰራር፦ የህዝብ ሀብት አያያዝ ግልጽነትና ተጠያቂነት መጓደል ያጋልጡኛል የሚሏቸው እያሳደዱ ማሰር፣ እየገደሉ አጀንዳ ለማስቀየር አፍ ለማዘጋት፣ ለማሸማቀቅ መሞከር፣ የከልሉ ብልሹ አሰራርና ሙስና የመከሰት እድል አስፍቶት ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ቀውስ አስከትሏል።

3. ትችትን አለመቀበል፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው እና አማካሪያቸው ንጉሴ አስረስ በመስቃን ህዝብ ላይ ግፍና መከራ እያዘነቡበት፣ እየገደሉት፣ እያፈናቀሉት፣ እያሳደዱ እያሰሩት ያለውን ጥፋታቸውን በማህበራዊ ሚዲያ መጋለጥ ትችት እንደ ጦር ፈርተው ለመሸፈን ሲሉ፣ “በኢንተርኔት መስኮት የኢትዮጵያ ችግር አይፈታም” የሚሉ መግለጫዎችን ለአመራሮቻቸው ትዛዝ ሰተው ቻሌንጅ አስጀምረዋል። በኢንተርኔት መስኮት የኢትዮጵያ ችግር አይፈታም የሚለው እውነት ካመኑበት በክልሉ ስር ለሚገኙ መዋቅሮች አመራሮች ትዛዝ ሰተው ቻሌንጁ እንዲቀላቀሉ የአድኑኝ ትዛዝ ለምን ሰጡ? እርስ በራሱ የሚጣረስ የሚያደርጉትን የማያቁት፣ የመደመር መርህ የጣሱ ብልፅግናን በቁሙ እየናዱ ማሸነፍ አይቻልም። ይህ አካሄድ በቀጥታ ትችትን ከመቀበል ያፈነግጣል እንጂ ችግሩን አይፈታም።

ማህበራዊ ሚዲያ በራሱ ብቻ ችግር አይፈታም የሚለው ሃሳብ እውነት ቢሆንም፣ እውነትን በማጋለጥ ዜጎች በእሱ አማካኝነት የሚያነሷቸው ትክክለኛ ጥያቄዎች ግን መስማት አለባቸው። ትችትን ከማስተካከል ይልቅ በማጥቃት ወይም በማቃለል መልስ መስጠት፣ የህዝብን በደልና ጭቆና የሚያሳይ አሉታዊ ባህል ነው።

ስለዚህ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እና አማካሪያቸው አምባገነናዊ የአስተዳደር አካላት ገንቢ ትችቶችን በክብር መቀበልና ማረም አለመቻል በጎሰኝነት መታወር፣ ድክመቶቻቸውን በግልጽ ማስተካከል አለመቻል የህዝብን እምነት ማጎልበት አለመቻላቸው የፌደራል መንግስት ጣልቃ ገብቶ የክልሉ ሰላም ደህንነት እንዲያረጋግጥ እንጠይቃለን።

የጭቁኑ የመስቃን ህዝብ!!

 !የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥታት (የአፄዎች) ሥርዓት ለዘመናት የዘለቀው በጥልቀት ሥር በሰደዱ የፖለቲካ፣ የሃይማኖት እና የባህል መሠረቶች ላይ ነበር። ይህ ሥርዓት በዋናነት በሚከተሉት ቁልፍ ም...
31/03/2026

!

የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥታት (የአፄዎች) ሥርዓት ለዘመናት የዘለቀው በጥልቀት ሥር በሰደዱ የፖለቲካ፣ የሃይማኖት እና የባህል መሠረቶች ላይ ነበር። ይህ ሥርዓት በዋናነት በሚከተሉት ቁልፍ ምሰሶዎች ላይ የተመሠረተ ነበር፡

​1. የሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት አፈ ታሪክ (Divine Right)
🛷​የንጉሥ ሰለሞን ዘር፡ አፄዎቹ ከንጉሥ ሰለሞን እና ከንግሥት ሳባ (ንግሥተ አዜብ) ዘር እንደሚወለዱ ይነገራል።
​2. የቤተክርስቲያን እና የመንግሥት ትስስር
🌶​የቅባት ዘይት፡ ንጉሠ ነገሥቱ ሲሾሙ በቤተክርስቲያን አባቶች አማካኝነት ቅብዓ መንግሥት ይደረግላቸው ነበር። ይህም ንጉሡ የቤተክርስቲያኒቱ ጠባቂ እና የአምላክ ምድራዊ ወኪል መሆናቸውን ያረጋግጣል።
🌶​የመንግሥት ሕጋዊነት፡ ቤተክርስቲያኒቱ ለንጉሡ ሕጋዊነትን ስትሰጥ፣ ንጉሡ ደግሞ ለቤተክርስቲያኒቱ ጥበቃና ድጋፍ ይሰጡ ነበር።
​3. የፊውዳሊዝም ሥርዓት (የመሬት ይዞታ)
​የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥታት ሥልጣን የተመሠረተው በመሬት አስተዳደር ላይ ነበር።
​ጉልት እና ጋሻ ጃግሬ
​4. የንጉሠ ነገሥቱ ማዕረግ (ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ)
​5. የፍትሐ ነገሥት (የሕግ ሥርዓት)
​6. ወታደራዊ መሪነት

​🎩የኢትዮጵያ የአፄዎች ሥርዓት ሃይማኖታዊ እምነትን፣ የደም ትስስርን (ዘርን)፣ መሬትን እና የጦር ኃይልን በማቀናጀት የተገነባ ጥብቅ ተዋረድ ያለው ሥርዓት ነበር።

እንደሻውና አማካሪው ሙሴሊም ጠልነታቸው በመሰረታዊነት ከሚከተሉት እሳቤ ነው።እሳቤያቸውም ሙሴሊም በክልሉ ደረጃ ፖለቲካ ላይ ተፅዕኖ ለማሳረፍ ያለመና መስቃን ሙስሊም በመሆኑና አብዛኛው ሙስሊም ነው በሚል የሙስሊም ሴምና ቆብ ያደረገ ሁሉ ለእነሱ ጠላታቸው ነው።

መለኮታዊው የእንደሻው አገዛዝ ከብልፅግና እሳቤ ያፈነገጠ እና ዘመኑን ያማይመጥን ፅዮናዊ አገዛዝ በመሆኑ መንግስት ልብ ሊለው ይገባል።

በብልፅግና ዘመን ይህ እንደማይህን የብልፅግናን መንገድ ያልተረዱ የዘመኑ አፄዎች ቆብ የደፉ ሱፍ ለባሾቼና የመስቀሉ ስር ቁማርተኞች ናቸው።የሚከላከሉላቸውም ከጌታ ልጅነት የመነጩ የአመራር ስም ካልሆነ በስተቀር እንደሻውም ቀዳሽ ከበሮ መች ፀናፅሉን ያዥ ነው።ንጉሴ መስቀል አሳላሚ ምዕመኑ አመራሩ ክክር ያሰረ ነው።

በመሆኑም መስቃንን ከስር መሰረቱ ለመንቀለረና የትርክት መዛባት ለመፍጠር የተሰሩ ስራዎች ናቸው።

ዛሬም የክርስቲያን ደሴት ነን በሚል የተሳሳተ ትርክት እንደሻው አጥማቂ ንጉሴ ቀዳሽ አሳላሚ እይታዎች ሁሉ ከሙስሊም ጠልነት የመነጨ የቤተ መንግስት ቀበሮነትና ተኩላነት ነው።

የመስቃን እስርም ጭቆናም እንግልቴና መሰደድም ከዚሁ እሳቤያቸው የመነጨ ነው።መስቃን ሙስሊም ብቻ አይደለም መስቃን ክርስቲያንም አለ ።የእንደሻው ትርክት ግን የተሳሳተ ቁርባን እንደ ቀመሱ ያስታውቅባቸዋል።

ወታደሩም ከዚህ የመነጨው የእንደሻው ወታደራዊ አቀዳድም ከዚሁ የመነጨ ነው።

ፍትህ መስቃን ይሻል።

የፖለቲካ ድንኩ እንደሻው ጣሰው፤የሀሳብ የመግለፅ መብት መገደብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስፋት እየተንሰራፋ ይገኛል።ለዚህም ጠንሳሽ አንባገነኑ እንደሻው ጣሰውና ንጉሴ አስረስ ናቸው።የመስቃ...
28/03/2026

የፖለቲካ ድንኩ እንደሻው ጣሰው፤

የሀሳብ የመግለፅ መብት መገደብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስፋት እየተንሰራፋ ይገኛል።ለዚህም ጠንሳሽ አንባገነኑ እንደሻው ጣሰውና ንጉሴ አስረስ ናቸው።

የመስቃን ችግሮች ምንጭ ንጉሴ አስረስ እና እንደሻው ጣሰው ነው።

የመስቃን ችግሮች ምንጫቸው አንድ ነው።እሱም የፖለቲካ የበላይነት በክስታኒኩ ኃይል ተጠርንፎ ስለተያዘ ነው።ችግሮቹ ምንጫቸው በመሪ ደረጃ እንደሻው ጣሰው እና ንጉሴ አስረስ ናቸው።

ይህንን የምንለው በመሪ ደረጃ ከ30 ዓመት በላይ በመስቃን ስም ወንበር ይዞ ወዲህና ወዲያ የሚገዋለለው ንጉሴ አስረስ አንድም ቀን መስቃን ሲሞት ድምፅ ያላሰማ አንድም ቀን መስቃን ያለ አግባብ ሲታሰር ድምፅ ያላሰማ አንድም ቀን ቤት ንብረት ሲወድም አንድም ቀን ድምፅ ያልሆነ፣

በክልል ደረጃ የመስቃን አመራር በካቢኔ ደረጃ ያለመኖሩ ምንጭ ንጉሴ አስረስ መሆኑ በመስቃን አራቱም ቀጠናዎች የሚደረጉ የአመራር ሹም ሽር የንጉሴ አስረስ እና የእንደሻው ጣሰው በጎ ፈቃድ ስውር እጅ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ያለበት ነው።

ወጣቶች ሀሳባቸውን በመግለፅ መብት ተደፍጥጦ መያዛቸው የንጉሴ አስረስና የእንደሻው ጣሰው የእጅ አዙር ጥምዘዛንና የህገ መንግስት ጥሰት መሆኑን የቀውስ ጊዜ አመራር እጦት መሆኑን እና የፖለቲካ ድንክነት ነው።

አመራር በምርጫ ሰዓት የመጀመሪያው ማድረግ ያለበት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ ሰላሙን ማስጠበቅ መሆኑ ይታወቃል።ይህን በተቃራኒው እየሰራ ያለው እንደሻው ጣሰውና ንጉሴ አስረስ ሀሳባችሁን ለምን ገለፃችሁ በማለት ብቻ ወደ ግዞት ወጣቶችን እየወረወሩ ይገኛሉ ይህ የሚያሳየው የፖለቲካ ድንክነታቸው ነው።

ፍትህ የፌደራል መንግስት በአስቸኳይ በመረመር ሊያስቆምልን ይገባል።አመት ንደሻው የግድ በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመወለዱ ብቻ የራሱን ሕዝብ ሊያፍን መብትም አይደለም።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gurage Fact Page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share