ኬር አውድ ፕሬስ Kere-Awed Press

ኬር አውድ ፕሬስ Kere-Awed Press የጉራጌን ባህል የማስተዋወቂያ እና በተለያዩ ጠቃሚ ጉዳዮች ዙሪያ መረጃ የመለዋወጫ እና የመማማሪያ መድረክ ነው

10/03/2026

ሶዶ ወረዳ😭

የጥንቃቄ መልዕክት ለዋትስአፕ ተጠቃሚዎች!***የኢፎርሜሽ መረብ ደህንነት አስተዳደር የተቀናጁ የዋትስአፕና የቴሌግራም ጠለፋዎች መበራከታቸውን አስተዋቋል።አስተዳደሩ የጠለፋው ዒላማ እየሆኑ ብሎ...
27/02/2026

የጥንቃቄ መልዕክት ለዋትስአፕ ተጠቃሚዎች!
***
የኢፎርሜሽ መረብ ደህንነት አስተዳደር የተቀናጁ የዋትስአፕና የቴሌግራም ጠለፋዎች መበራከታቸውን አስተዋቋል።
አስተዳደሩ የጠለፋው ዒላማ እየሆኑ ብሎ ከዘረዘራቸው ውስጥ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ተማሪዎች፣ በርቀት ሆነዉ በዲጂታል አማራጮች የሚማሩ ግለሰቦች እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ይገኙበታል።
አስተዳደሩ የዋትስአፕና የቴሌግራም ተጠቃሚዎች የጠለፋው ሰለባ እንዳይሆኑ የጥንቃቄ ስልቶችና የመከላከያ መንገዶች ያላቸውን የጥንቃቄ መልዕክቶች በማህበራዊ ገፁ አሰራጭቷል።
የመረጃ መንታፊዎች የሚጠቀሙባቸዉ ዋና ዋና የጠለፋ ስልቶች
1. የምርጫ ሂደትን እና የፖለቲካ ኩነቶችን ለሴራ መጠቀም፦አጥፊዎቹ የሀገራዊ የምርጫ ወቅት መሆኑን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የዜጎችን የፖለቲካ ፍላጎትና ስሜት ለጥቃት ምቹ አጋጣሚ አድርገዉ እየተጠቀሙ ይገኛል፦
የምርጫ ደጋፊ በመምሰል፦ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ደጋፊ በመምሰልና የፓርቲዎችን አርማ (Logo) በመጠቀም "ለፓርቲያችን ድጋፍዎን እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን ይግለጹ" ወይም "የምርጫ ቅስቀሳ ቡድናችንን ይቀላቀሉ" የሚሉ አሳሳች መልዕክቶችን ይልካሉ።
የምርጫ መረጃ አቅራቢ በመምሰል፦ "የምርጫ ጣቢያዎትን ለማወቅ"፣ "የዕጩዎችን ዝርዝር ለማየት" ወይም "የምርጫ ውጤቶችን በቅድሚያ ለማግኘት" የሚሉ አሳሳች ማስፈንጠሪያዎችን (Links) በመጠቀም የተጠቃሚዎችን የዋትስአፕ አካውንት በቁጥጥራቸው ስር ያውላሉ።
2. ተከታታይ ጠለፋ እና የማንነት ስርቆት: ይህ ስልት እጅግ አደገኛ የሆነው ጥቃቱ የሚመጣው ከሚታወቅና ከቅርብ ሰው በመሆኑ ነው። የአንድ ግለሰብ አካውንት አንዴ ከተጠለፈ በኋላ አጥፊዎቹ የሚከተሉትን ድርጊቶች ይፈጽማሉ፦
የገንዘብ ማጭበርበር፦ የተጠለፈውን ሰው ማንነት በመጠቀም በስልክ አድራሻ ዝርዝሩ ውስጥ ላሉ ወዳጆች "ድንገተኛ የጤና ችግር አጋጥሞኝ ነው" ወይም "ከምርጫ ስራ ጋር በተያያዘ ገንዘብ በአስቸኳይ አስፈልጎኝ ነው" በማለት የባንክ አካውንት በመላክ ከፍተኛ የገንዘብ ማጭበርበር ይፈጽማሉ።
ተጨማሪ ጠለፋ፦ ለሌሎች የሥራ ባልደረቦችና ኃላፊዎች አሳሳች ሊንኮችን በመላክ የጥቃቱን ሰለባ ያስፋፋሉ። በዚህም ወሳኝ የሆኑ የመንግስት እና የተቋማዊ መረጃዎችን የመስረቅና የማጥፋት ስጋት ይፈጥራሉ።
3. ተማሪዎችን እና የከፍተኛ ትምህርት ተከታታዮችን ኢላማ ማድረግ፦ በውጭ ሀገር የሚማሩ ወይም በኢንተርኔት ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ዜጎችን ኢላማ በማድረግ፤ ከሚማሩበት ዩኒቨርሲቲ የተላከ በማስመስል (ለቪዛ እድሳት፣ ለትምህርት ክፍያ ቅናሽ ወይም ለፈተና መረጃ በሚል ሰበብ) ሊንኮችን ይልካሉ። ተማሪዎቹ መረጃቸውን ሲያስገቡ የግል መረጃቸውና የዋትስአፕ አካውንታቸው ወዲያውኑ ይረበሻል።
4. የባለ 6-አሃዝ ኮድ ማጭበርበር: አጥፊዎች የእርስዎን ስልክ ቁጥር በመጠቀም በሌላ ስልክ ዋትስአፕ ለመክፈት ይሞክሩና ወደ እርስዎ ስልክ በቴክስት (SMS) የሚመጣውን ባለ 6-አሃዝ ኮድ፤ "በስህተት ወደ አንተ የተላከ ኮድ ስለሆነ እባክህ መልሰህ ላክልኝ" በማለት ይጠይቃሉ። ይህንን ኮድ አሳልፈው ከሰጡ አካውንትዎ ወዲያውኑ ይጠለፋል።
ራስን እና ተቋምን ለመጠበቅ መወሰድ ያለባቸው እርምጃዎች
1. ባለሁለት-ደረጃ ማረጋገጫን ያብሩ፦ ይህ አካውንትዎን ከጠለፋ ለመጠበቅ ቁልፍ መከላከያ ነው።
እንዴት ይበራል? WhatsApp Settings > Account > Two-step verification > Turn On በመግባት የራስዎን ሚስጥራዊ ባለ 6-አሃዝ ቁጥር (PIN) እና የኢሜይል አድራሻ ያስገቡ።
2. የማረጋገጫ ኮድን በምንም ምክንያት አያጋሩ፦ ወደ ስልክዎ በሜሴጅ የሚላክን የዋትስአፕ ማረጋገጫ ኮድ (Verification Code) ለምንም አይነት አካል (ለጓደኛም ሆነ ለቤተሰብ) አሳልፈው አይስጡ።
3. አጠራጣሪ ሊንኮችን (Links) አይጫኑ፦ በተለይ ከምርጫና ወቅታዊ ጉዳዮች ጋር ተያይዞ ከማይታወቅም ሆነ ከሚታወቅ ሰው የሚላክልዎትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመጫንዎ በፊት ትክክለኛነቱን በሌላ የመገናኛ ዘዴ ያረጋግጡ።
4. የገንዘብ ጥያቄን በመደበኛ ስልክ ያረጋግጡ፦ ማንኛውም ሰው በዋትስአፕ በኩል የገንዘብ እርዳታ ሲጠይቅዎት፣ አካውንቱ ተጠልፎ ሊሆን ስለሚችል ገንዘብ ከመላክዎ በፊት በመደበኛ ስልክ በመደወል ድምፁን ሰምተው ትክክለኛነቱን ያረጋግጡ።
5. የመረጃ ጥንቃቄ ያድርጉ፦ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ወሳኝ የሆኑ ሀገራዊ እና ተቋማዊ መረጃዎችን በዋትስአፕ ከመለዋወጥ መቆጠብ አለባቸው። ለሥራ ጉዳይ ደህንነታቸው የተረጋገጡ (Secure) የውስጥ መገናኛ ዘዴዎችን መጠቀም ይመከራል።

ለቤት ዕጣ በትንሹ መቆጠብ የሚጠበቅብን የገንዘብ መጠን…
27/02/2026

ለቤት ዕጣ በትንሹ መቆጠብ የሚጠበቅብን የገንዘብ መጠን…

የ15ኛው ዙር የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ በዚህ ወር መጨረሻ እንደሚወጣ ይጠበቃል። የቤት ተመዝጋቢውች ዕጣ ውስጥ ለመካተት ቢያንስ ምን ያህል መቆጠብ እንደሚጠበቅባቸው ይህ ቪዲዮ ያስረዳና.....

ዕጣ መቼ ይወጣል ብላችሁ ለምትጠባበቁ!
25/02/2026

ዕጣ መቼ ይወጣል ብላችሁ ለምትጠባበቁ!

በቅርቡ የ20/80 እና 40/60 ፕሮግራም የኮንዶምኒየም ቤት ዕጣ እንደሚወጣ ከታማኝ ምንጮች የተገኙ መረጃዎች አረጋግጠዋል።

የተጀመረውን የመንገድ ሥራ ለማጠናቀቅ የአካባቢው ተወላጆች ድጋፍ አስፈልጓል***በምስራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ በአማውቴ ሞረጌ ቀበሌ ልዩ ስሙ ወተደር ተብሎ ከሚጠራው ሰፈር ወደ ጎቤኒ ቅድስት...
24/02/2026

የተጀመረውን የመንገድ ሥራ ለማጠናቀቅ የአካባቢው ተወላጆች ድጋፍ አስፈልጓል
***
በምስራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ በአማውቴ ሞረጌ ቀበሌ ልዩ ስሙ ወተደር ተብሎ ከሚጠራው ሰፈር ወደ ጎቤኒ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስትያን የጠጠር መንገድ ሥራ ተጀምሯል።
መንገዱ አማውቴ ከተማን በአቋራጭ ከጎቤኒ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስትያን እና ከጉራንዳ እሁድ ገበያ የሚያገናኝ ነው። የመንገዱ መሰራት በዓመታዊ የንግስ በዓል ወቅት መኪና እስከ ደጇ እንዲገባ፣ ከእሁድ ገበያ ጋር መገናኘቱ ደግሞ ምርቶችን ወደ ገበያ ለመውሰድና ለንግድ መሳለጥ እንዲሁም እናቶች ሲወልዱ በአንቡላንስመ ሆነ በሌላ ተሽከርካሪ በፍጥነት ወደ ሆስፒታል ለማድረስ በጣም አስፈላጊ ነው።
የመንገድ ሥራው የሚከናወነው በአካባቢው የጉራጌ ተወላጆች ትብብር ነው። የመንገድ ጠረጋው ተጀምሮ የቀሩ ሥራዎች አሉ።
ስለሆነም የጉራጌ ተወላጆች ለመንገድ ሥራው የሚችሉትን ድጋፍ እንዲያደርጉ ኮሚቴው ጥሪ አስተላልፏል።

“ጀፎረ” ትናንትን ከዛሬ ያጋመደ ፍልስፍና***ከንግድ ጋር ተያይዞ ሥማቸው በተደጋጋሚ ይነሳል። ታታሪነት መገለጫቸው ነው። በልዩ ሁኔታ የሚያዘጋጁት ክትፎ መታወቂያቸው ሆኖ ቀጥሏል። የቤት አሠ...
17/02/2026

“ጀፎረ” ትናንትን ከዛሬ ያጋመደ ፍልስፍና
***
ከንግድ ጋር ተያይዞ ሥማቸው በተደጋጋሚ ይነሳል። ታታሪነት መገለጫቸው ነው። በልዩ ሁኔታ የሚያዘጋጁት ክትፎ መታወቂያቸው ሆኖ ቀጥሏል። የቤት አሠራርና አያያዝ ጥበባቸው የብዙዎችን ቀልብ ይስባል። የበርካታ ባህላዊ ትውፊቶች ባለቤትም ናቸው- ጉራጌዎች።
ተጨማሪ ከፈለጉ ማስፈንጠሪያውን ተጭነው ያንብቡ።
👇

Explore categorized stories, bids, vacancies, E-Papers, and E-Magazines from Gazette Plus (also found by searching Gazetta). Browse curated media content including pictures and videos.

የኢቢኤስ ቴሌቪዥን መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ*** የተወዳጁ የኢቢኤስ(EBS)  ቴሌቪዥን ጣቢያ መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አማን ፍስሃጽዮን አረፉ።ለቤተሰቦቻቸ...
11/02/2026

የኢቢኤስ ቴሌቪዥን መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
***
የተወዳጁ የኢቢኤስ(EBS) ቴሌቪዥን ጣቢያ መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አማን ፍስሃጽዮን አረፉ።
ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን እንመሻለን።

የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚ ነዎት!?***Kare-Awude-Press (የካቲት 3/ 2018 ዓ.ም)የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚዎች እነዚህ ምክሮች ለእናንተ በጣም አስፈላጊ ስለሆኑ ተጠቁሙባቸው። ከ...
10/02/2026

የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚ ነዎት!?
***
Kare-Awude-Press (የካቲት 3/ 2018 ዓ.ም)
የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚዎች እነዚህ ምክሮች ለእናንተ በጣም አስፈላጊ ስለሆኑ ተጠቁሙባቸው። ከሞባይል ባንኪንግ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ ገንዘባችን ለስርቆት የሚያጋልጥ የማይመከሩ ልማዶች ስለተበራከቱ ልብ እንበል።
እነዚህን አታድርጉ
👉 ትራንስፖርት ውስጥ ሌሎች ሰዎች የይለፍ ቃላችንን ሊያዩ በሚያስችላቸው ሁኔታ ውስጥ ወደ የባንክ አካውንት ውስጥ መግባት፦ የይለፍ ቃሉን ያየው ሰው ሌባ ከሆነ ስልካችን እንደምንም ዘርፎ የባንክ ሂሳባችንን ሊያንቀሳቅስ ይችላል።
👉 የራሳችን ባልሆነ ዋይፋይ (Public Network) በመጠቀም ወደ ሞባይል ባንክ አካውንታችን መግባት፦ በሳይበር ጥቃት ፈፃሚዎች ወደ ባንክ ሂሳባችን የሚገቡበት ዕድል ሊፈጥር ይችላል።
👉 ወደ ሞባይል ባንክ አካውንታችን ገብተን መላላክ ከጨረስን በኋላ ሳይን አውት አለማድረግ፦ ወደ አካውንታችን ገብተን (ሳይን አነ አድርጎ) መተዉ ድንገት ስልኩ ሌላ ሰው እጅ ቢገባ አካውንታችንን ተጠቅሞ ብር ወደ ሌላ ሰው ሊያስተላልፍብን ይችላል።
👉 በቴሌግራም መልእክት ብቻ በቀረበ ጥያቄ ወደ ሌላ ሰው ገንዘብ ማስተላለፍ፦ የቴሌግራም አካውንትን በመጥለፍ ዘራፊዎች ኮንታክት ውስጥ በመግባት አስቸኳይ ገንዘብ አስተላልፉልኝ ጥያቄ ሊጠይቁ ይችላሉ። ብዙ ሰው እየተጥበረበረ ስለሆነ ስልክ ደውሎ ማረጋገጥ ያስፈልጋል።
👉 የይለፍ ቃልን ስልክ ላይ መዝግቦ መያዝ፦ የስልካችንን ፓተርን ማግኘት የቻለ ዘራፊ የባንክ ሂሳባችንን ያለማንም ከልካይ ማንቀሳቀስ ይችላል።

እነዚህን ግን አድርጉ
👉 በቀላሉ የማይገመትና ጠንካራ የይየለፍ ቃል መጠቀም፦ የልደት ቀናችሁ፣ ስልክ ቁጥራችሁ፣ ተከታታ ቁጥር የመሳሰሉት ያልሆነና ሌሎች በቀላሉ ሊገምቱት የማይችሉት መሆን አለባት
👉 ባለሁለት ደረጃ የይለፍ ቃል ተጠቀሙ፦ ፓስዋርድ፣ አሻራና ፓተርን በማጣመር መጠቀም
👉 በተወሰነ ጊዜ ልዩነት የይለፍ ቃል መቀየር፦ ባልጠበቅነው አጋጣሚ የይለፍ ቃላችን ሌላ ሰው እጅ ገብቶ ሊሆን ስለሚችል አካውንቱ ስንከፍተው የሰጠነው የይለፍ ቃል ለረዥም ጊዜ አለመጠቀም።
👉 ስልካችሁ ከተሰራቅችሁ በፍጥነት የባንክ ሂሳባችሁ እንዳይነቀሳቀስ ደንበኛ ለሆናችሁት ባንክ ሪፖርት ማድረግ።

በጋዜጠኛ ሶዶ ለማ አስተባባሪነት የዊልቸር ድጋፍ የተደረገለት ወጣት***በጉራጌ ዞን ቸሃ ወረዳ የሚገኝ አንድ አካል ጉዳተኛ ወጣትን ለመደገፍ ጋዜጠኛ ሶዶ ለማ በማህበራዊ ሚዲያ እንቅስቃሴ ጀም...
06/02/2026

በጋዜጠኛ ሶዶ ለማ አስተባባሪነት የዊልቸር ድጋፍ የተደረገለት ወጣት
***
በጉራጌ ዞን ቸሃ ወረዳ የሚገኝ አንድ አካል ጉዳተኛ ወጣትን ለመደገፍ ጋዜጠኛ ሶዶ ለማ በማህበራዊ ሚዲያ እንቅስቃሴ ጀምሮ ነበር:: በመጨረሻም ውጭ ሀገር ከሚኖር መስፍን ኃ/ማርያም ከሚባል በጎ አድራጊ በተገኘ ድጋፍ አካል ጉዳተኛው ወጣት የዊልቸር ድጋፍ ተደረጎለታል::

ጉራጌ❤️
05/02/2026

ጉራጌ❤️

መሬት አንቀጥቅጥ የፈረስ ጉግስ😍***የዘንድሮ ይለያል
05/02/2026

መሬት አንቀጥቅጥ የፈረስ ጉግስ😍
***
የዘንድሮ ይለያል

በአዊ ብሔረሰብ ዞን በየዓመቱ ጥር ወር ደማቅ ፌስቲቫል ይካሄዳል። ዘንደሮ በልዩ ድምቀት በ100 ሺዎች የሚቆጠሩ ታዳሚዎች በተገኙበት የፌስቲቫሉ ዋና አካል የሆነው መሬት ያንቀጠቀጠ የፈረ....

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኬር አውድ ፕሬስ Kere-Awed Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share