ዐዋዲ - Awadi

ዐዋዲ - Awadi ነገርን ከምንጩ
Straight from the horse's mouth

ይህን ፎቶግራፍ ሳየው የእናቴ ጉብዝና ነው የሚታየኝ:: So proud of her:: ፎቶግራፉ የተነሳው በኛ በ1950 አካባቢ ነው:: ከዚህ ቀደም አይቼዋለሁ ነገር ግን እንዴት ሆነ ብዬ ጠይቄ...
23/12/2025

ይህን ፎቶግራፍ ሳየው የእናቴ ጉብዝና ነው የሚታየኝ:: So proud of her:: ፎቶግራፉ የተነሳው በኛ በ1950 አካባቢ ነው:: ከዚህ ቀደም አይቼዋለሁ ነገር ግን እንዴት ሆነ ብዬ ጠይቄ አላውቅም ነበር:: አሁን እዚህ ሆኜ ከእናቴ ጋር ብዙ ጊዜ ስለማሳለፍ ልጅ ነበርሽ እንዴት ልትሄጂ ቻልሽ? ብዬ ጠየኳት:: በጊዜው እናቴ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልክ የመጀመሪያ ዓመት እንደጨርሰች ነበር:: የአባቴ የጋብቻ ጥያቄ በቤተሰቦቿ ተቀባይነት እያገኘ ስለመጣ ዩኒቨርሲቲ መቀጠል አልቻለችም:: ታዲያ እናቴ ያስገረመኝንና ያስደስተኝን ውሳኔ ወሰነች:: ከማግባቴ በፊት ውጭ አገር መሄድ አለብኝ ብላ ወሰነች:: ፈረጆች I have to see the world እንደሚሉት:: ልጅ ስለነበረችና አገሩን ስለማታውቀው የእናቷን ቤት የተከራዩ ጋሪሰን ከሚባሉ አሜሪካዊ ባልና ሚስት ጋር አሜሪካ ለመሄድ ወሰነች:: ለእናቷ አንድ ልጅ ስለበረች በመከራ ነው ልትሄድ የቻለችው:: ኒው ዮርክ እንደደረሰች ሆቴል ገብታ የቅርብ ዘመድዋን ያኔ ገና አምባሳደር አልነበሩም ወይዘሪት ዮዲት እምሩን አግኝታ ከሳቸው ጋር ብዙ ጥሩ ጊዜ አሳለፈች:: በሳቸውም አማካኝነት የተባበሩት መንግስታትን ጎበኘች:: ኒው ዮርክን በደንብ አድርጋ ከጎበኘች በኋላ ወደ እነ ጋሪሰን ከተማ ወደ ማዲሰን ዊስኮንስን ሄደች:: ባጠቃላይ የእናቴ የአሜሪካ አድቬንቸር ወደ ዓመት ያህል ነበር:: ደፋርነቷን ስለወደድኩት ነው ያካፈልኳችሁ::

ኢትዮጵያ ሃገር በቀል እውቀቶችን ጥቅም ላይ ለማዋል ተግባራዊ እንቅስቃሴ ጀምራለችከመላ አገሪቱ የተውጣጡ የትምህርት አመራሮች፣ የዩኒቨርሲቲዎች መምህራን፣ ተመራማሪዎች እና የህብረተሰብ ጤና ሊ...
23/12/2025

ኢትዮጵያ ሃገር በቀል እውቀቶችን ጥቅም ላይ ለማዋል ተግባራዊ እንቅስቃሴ ጀምራለች

ከመላ አገሪቱ የተውጣጡ የትምህርት አመራሮች፣ የዩኒቨርሲቲዎች መምህራን፣ ተመራማሪዎች እና የህብረተሰብ ጤና ሊቃውንት የኢትዮጵያን ሃገር በቀል እውቀቶች እና ጥበባት ማሰባሰብ፣ ማደራጀት እና መሰነድ ብሎም ትምህርት እና ጤናን ጨምሮ በበርካታ ዘርፈች የሚስተዋሉ ችግሮችን ማከሚያ ለማድረግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ በአዲስ አበባ እየመከሩ ነው።

በጤና ሚኒስቴር የሚንስትሯ የህብረተሰብ ጤና ከፍተኛ አማካሪ ፕሮፌሰር መንገሻ አድማሱ “ሃገር በቀል እውቀት የአንድ ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ኃብት ነው። ኢትዮጵያ በአገር በቀል እውቀቶች የታደለች ጥንታዊት ሃገር ብትሆንም የአያት ቅድመ አያቶቻችንን ጥበብ እየተጠቀምንበት አይደለም። አሁንም ቢሆን ካከበርከው እና በእቅድ ከተጠቀምክበት ብዙ ችግሮቻችንን ይፈታልናል።” ብለዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህብረተሰብ ጤና መሞህር እና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ሚርጊሳ ካባ “በኢትዮጵያ ሆነ እንደ አህጉር በአፍሪካ ደረጃ ሃገር ቨቀል እውቀቶች ተገቢው ትኩረት አልተሰጣቸውም። አሁን ግን ባህላችንን፣ ጥበባችንን እና ሃገር በቀል እውቀቶቻችንን ጥቅም ላይ ለማዋል አሉ የሚባሉ የአገሪቱ ተመራማሪዎች በአንድ መድረክ ተሰባስበዋል። ይህ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ተደርጎ ይወሰዳል።” ሲሉ ተደምጠዋል።

እንደ ደብረ ብርሃን እና ደብረ ማርቆስ ያሉ ዩንቨርሲቲዎች በመቶዎች የሚቆጠሩ መድሃኒታዊ እጽዋትን በማልማት ወደ የባህላዊ መድሃኒቶች የሙከራ ምርት ሂደት መሸጋገራቸው ይታወቃል።

በአለማችን ቻይና፣ ህንድ፣ ጃፓን እና ኮሪያ በባህላዊ መድሃኒት ዘርፍ ቀዳሚዎቹ ሃገራት ናቸው።

telegram - https://t.me/addisfnot

🇪🇹🇷🇺 ኢትዮጵያ እናስ ሩሲያ የኑክሌር ልማት ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረሙ ሩሲያ እና ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ልማት ዙሪያ በሮሳቶም እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃ...
25/09/2025

🇪🇹🇷🇺 ኢትዮጵያ እናስ ሩሲያ የኑክሌር ልማት ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረሙ

ሩሲያ እና ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ልማት ዙሪያ በሮሳቶም እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን መካከል የድርጊት መርሃ ግብር ተፈራረመዋል።

የሮሳቶም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሌክሲ ሊካቼቭ እና የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ፣ ቭላድሚር ፑቲን እና ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት የተፈረመውን ሰነድ ተለዋውጠዋል።

የፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ የበክሬምሊን የመጀመሪያ ሕንጻ በሚገኘው የተወካይ ጽሕፈት ቤት በሩሲያው መሪ እና በኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር መካከል የተደረገው ውይይት አካል ነው።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ
゚viralシfypシ゚

28/08/2025

በዘመን አመጣሹ የቴክኖሎጂ ትሩፋት የተነሳ በቻይና ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ህይወት ሳይንስ ፊክሽን ፊልሞች ላይ የሚታዩ ትዕይንቶችን መስሏል፡፡ በዠጂያንግ ዩኒቨርሲቲ የሮቦት ውሻዎች የአዲስ ገቢ ተማሪዎችን ሻንጣ ተሸክመው የተመደቡበት ማደሪያ ክፍል ድረስ ይውስዳሉ፡፡ “ቻይናዎች መጪውን ጊዜ ዛሬ እየኖሩት ነው” ሲል ከስር የምትመለከቱትን ቪዲዮ ያጋራው አር ቲ ቴሌቪዥን ነው፡፡ ይህን ቪዲዮ ካያችሁ በኋላ ‘አዋዲ’ እንዲወዳጁ በትህትና እንጠይቆታለን፡፡

, , , , , , , , ゚viralシfypシ゚ , ,

25/08/2025

አፍሪካውያን የኦርቶዶክስ ካህናት በሩሲያ ሥልጠና እና ሐይማኖታዊ ጉዞ ጀመሩ

ለመጀመሪያ ጊዜ በሚካሄደው የሰሜንና ደቡብ አፍሪካ ሀገረ ስብከቶች ጉባኤ፤ ከ22 ሀገራት የተውጣጡ 30 ከፍተኛ ካህናት እየተሳተፉ እንደሚገኙ በሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን የአፍሪካ ሀገረ ስብከት አስታውቋል፡፡

ተሳታፊዎቹ እርስ በርስ እና ከሩሲያ ቀሳውስት ጋር ልምድ ከመለዋወጣቸው ባሻገር የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናትን “ውጫዊና ውስጣዊ ውበት” ቃኝተዋል።

“ሩሲያውያን በጣም ጥሩ እና እንግዳ ተቀባይ ሕዝቦች ናቸው። ለዚህም ምስጋና ይግባና ፍርሃትና ጥርጣሬዎች ሙሉ በሙሉ ይወገዳሉ፡፡ ልጆቻችንን ለትምህርት ወደ ሩሲያ ለመላክም ከእንግዲህ አንፈራም” ሲሉ የኬንያው ናንዲ ሀገረ ስብከት ዋና ኃላፊ ቄስ ቲቶስ ኪፕንጌኒ ተናግረዋል።

https://t.me/sputnik_ethiopia

በአለም ከመጠን በላይ የወፈሩ ሰዎች ብዛት አንድ ቢልየን አልፏል ተባለበዓለም አቀፍ ደረጃ ከመጠን ያለፈ ውፍረት ያላቸው ሰዎች ቁጥር ከአንድ ቢሊዮን በላይ መድረሱን ዘ ላንሴት በተባለ ሳይንሳ...
28/07/2025

በአለም ከመጠን በላይ የወፈሩ ሰዎች ብዛት አንድ ቢልየን አልፏል ተባለ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ከመጠን ያለፈ ውፍረት ያላቸው ሰዎች ቁጥር ከአንድ ቢሊዮን በላይ መድረሱን ዘ ላንሴት በተባለ ሳይንሳዊ መጽሔት ላይ የወጣ አንድ ጥናት አመለከተ።

ትንታኔው በፈረንጆቹ 1990 እስከ 2022 ባለው ጊዜ ውስጥ ከ190 በሚበልጡ አገሮች የተገኘውን መረጃ ያካተተ ሲሆን በዚህ ጊዜ ውስጥ ከመጠን ያለፈ ውፍረት በልጆችና በአዋቂዎች ላይ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል።
ይህም በሴት ልጆች ከ1.7% ወደ 6.9% እንዲሁም በወንድ ልጆች ከ2.1% ወደ 9.3% ከፍ ብሏል።

እ.ኤ.አ. በ2022 ወደ 160 ሚሊዮን የሚጠጉ ታዳጊዎች ከመጠን በላይ ውፍረው ነበረ።

በአዋቂዎችም ዘንድ ችግሩ ተባብሷል። ከመጠን ያለፈ ውፍረት ያለባቸው ሴቶች መጠን ከ 8.8% ወደ 18.5% ሲጨምር፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረት ያለባቸው ወንዶች መጠን ደግሞ ከ 4.8% ወደ 14% ከፍ ብሏል።

በቅርቡ በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ ሼፎች ጉባኤና የስርዓተ ምግብ የፖሊሲ ምክክር ላይ የተሳተፉ አፍሪካውያን ባለሙያዎች የተጠበሱ፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩ እና ከውጭ የሚገቡ ምግቦች ከመጠን ላለፈ ውፍረት እና ለወሰስብስበሰ የጤና ጠንቆች እንደሚዳርጉ አሳስበዋል።

28/05/2025

“ለብዙ ጓደኞቼ ለመኖር እድል አግኝቼ 84 ዓመት ቀላል ጊዜ አይደለም፡፡ ይህንን ማክበር ብቻ ሳይሆን አገር አቋርጣችሁ ከአገር ወጥታችሁ ይህን በማድረጋችሁ አመስግ/ናችኋለሁ” ሲሉ የቀድሞው ረእሰ ብሄር መንግስቱ ሃይለማሪያም Ethiopian Society Partnership Advocacy የተባለው ድርጅት እና አባላቱ ስለሰጧቸው እውቅና ምስጋና አቅርበዋል፡፡
Video: Guenet Ayele



በሃገር ባህል መስተንግዶ ፍላጎትዎን የሚያሟላልዎ ሰሜን ሸዋ ሆቴል ሁሉንም አሟልቶ ይጠብቆታል። አድራሻ ላምበረት 02 መገንጠያ
17/05/2025

በሃገር ባህል መስተንግዶ ፍላጎትዎን የሚያሟላልዎ ሰሜን ሸዋ ሆቴል ሁሉንም አሟልቶ ይጠብቆታል። አድራሻ ላምበረት 02 መገንጠያ

በኒው ዚላንድ የበጎች ቁጥር ከአገሪቱ ዜጎች ቁጥር እጅጉን እንደሚልቅ የዓለም መገናኛ ብዙሃን በመዘገብ ላይ ይገኛሉ፡፡ ኒው ዚላንድ ዜጎች የበርካታ በጎች መኖሪያ ተብለው ከተመደቡ ጥቂት አገራ...
14/05/2025

በኒው ዚላንድ የበጎች ቁጥር ከአገሪቱ ዜጎች ቁጥር እጅጉን እንደሚልቅ የዓለም መገናኛ ብዙሃን በመዘገብ ላይ ይገኛሉ፡፡ ኒው ዚላንድ ዜጎች የበርካታ በጎች መኖሪያ ተብለው ከተመደቡ ጥቂት አገራት ተርታ ተቀምጣለች፡፡

የአገሪቱ መንግስት የስታቲስቲክስ ኤጀንሲ መረጃዎች እንደሚያሳዩት በኒው ዚላንድ 23.6 ሚሊዮን በጎች የሚገኙ ሲሆን የነዋሪዎች ቁጥር ደግሞ ከ5.3 ሚሊዮን አይበልጥም፡፡ ለአንዱ ነዋሪ በአማካይ 4.5 በግ ይደርሰዋል ማለት ነው፡፡

በጎችን ለስጋ እና ለሱፍ በግ ማርባት የኒውዚላንድ ነዋሪዎች ትልቁ የገቢ ምንጭ ሆኖ መቆየቱን የዘገበው አሶሼትድ ፕሬስ ነው፡፡

ፈረንሳይ ጉራራ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ሹፌርና ረዳቱን ብቻ የጫነ አውቶቡስ ከቀኝ መስመር ወጥቶ በግራ መስመር ላይ ወድቋል። ሁለቱም ተርፈዋል። አውቶቡሱ በርካታ ሰዎችን አሳፍሮ ቢሆን ኖሮ በር...
06/05/2025

ፈረንሳይ ጉራራ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ሹፌርና ረዳቱን ብቻ የጫነ አውቶቡስ ከቀኝ መስመር ወጥቶ በግራ መስመር ላይ ወድቋል። ሁለቱም ተርፈዋል። አውቶቡሱ በርካታ ሰዎችን አሳፍሮ ቢሆን ኖሮ በርካቶችን ለሞት የሚዳርግ አደጋ ይከሰት እንደነበር በስፍራው የነበሩ የፖሊስ ባልደረቦች ተናግረዋል።
ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

ወመዘክር አዳራሹን  በብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ስም ሰየመየብሄራዊ ቤተ መዛግብትና መጽሀፍት( ወመዘክር )ዋና ዳይሬክተር ይኩኑአምላክ መዝገቡ እንደገለጹት፤ ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ...
03/04/2025

ወመዘክር አዳራሹን በብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ስም ሰየመ

የብሄራዊ ቤተ መዛግብትና መጽሀፍት( ወመዘክር )ዋና ዳይሬክተር ይኩኑአምላክ መዝገቡ እንደገለጹት፤ ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ብዙ ሰአታቸዉን ለጽሁፍ በመስጠት ግዙፍ ስራዎችን አበርክተዋል።
ወመዘክር መታሰቢያ ሆኖ ከመቋቋሙ በፊት እርሳቸዉ ነገ ትዉልድ የሚፈልጉ ነገሮች ሲዘክሩ የኖሩ የሀገር ባለዉለታ መሆናቸዉን ገልጸዋል።
የወመዘክር አንዱ ስራ ባለዉለታዎቻችንን መዘከር ነዉ ያሉት ዳይሬክተሩ እንደነዚህ ያሉ ስራዎች እንደሚቀጥሉ አስታዉቀዋል።
የብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ልጅ የሆኑት አምሀ መርስዔ ኀዘን በበኩላቸዉ አባታቸዉ ብዙዉን ጊዜያቸዉ በመጽሀፍ ያሳለፉ መሆናቸዉ በመግለጽ ለስራቸዉ እዉቅና በመሰጠቱ መደሰታቸዉን ገልጸዋል።
የብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ የእጅ ጽሁፍ ስራዎች ሳይቀር ለቤተመጽሀፉ ማስረከባቸዉን የገለጹ ሲሆን እንደነዚህ ያሉ ተግባሮች ሊለመዱ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
‘የ20ኛው መቶ ክፍል ዘመን መባቻ’ የተሰኘ አይተኬ መዝገበ ታሪክ እና በርካታ ሃይማኖታዊ፣ ስርዓተ መንግስታዊ እና ማህበራዊ ይዘት ያላቸውን መጻህፍት ለትውልዱ ያበረከቱት ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ጉልህ አሻራቸውን ካሳረፉ የሃያኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድንቅ ምሁራን መካከል ዋነኛው ናቸው፡፡
Ethiopian Press Agency /የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት/


31/03/2025

አስጨናቂ ትዕይንት

ዛሬ ከሰዓት በሩሲያ ሴንትፒተርስበርግ ከተማ በአንድ አፓርታማ ላይ የተከሰተ የእሳት አደጋን ተከትሎ አንድ ታናሽ ብላቴና ከሶስተኛ ፎቅ ላይ ሲዘል ይታያል። ሆኖም ጎረቤቶቹ ብርድልብስ በመዘርጋት ከመከስከስ አትርፈውታል።

በአሁን ሰዓት በሆስፒታል ውስጥ ህክምና በመከታተል ላይ መሆኑን የአር ቲ ሪፖርት ያመለክታል።

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዐዋዲ - Awadi posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share