23/12/2025
ይህን ፎቶግራፍ ሳየው የእናቴ ጉብዝና ነው የሚታየኝ:: So proud of her:: ፎቶግራፉ የተነሳው በኛ በ1950 አካባቢ ነው:: ከዚህ ቀደም አይቼዋለሁ ነገር ግን እንዴት ሆነ ብዬ ጠይቄ አላውቅም ነበር:: አሁን እዚህ ሆኜ ከእናቴ ጋር ብዙ ጊዜ ስለማሳለፍ ልጅ ነበርሽ እንዴት ልትሄጂ ቻልሽ? ብዬ ጠየኳት:: በጊዜው እናቴ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልክ የመጀመሪያ ዓመት እንደጨርሰች ነበር:: የአባቴ የጋብቻ ጥያቄ በቤተሰቦቿ ተቀባይነት እያገኘ ስለመጣ ዩኒቨርሲቲ መቀጠል አልቻለችም:: ታዲያ እናቴ ያስገረመኝንና ያስደስተኝን ውሳኔ ወሰነች:: ከማግባቴ በፊት ውጭ አገር መሄድ አለብኝ ብላ ወሰነች:: ፈረጆች I have to see the world እንደሚሉት:: ልጅ ስለነበረችና አገሩን ስለማታውቀው የእናቷን ቤት የተከራዩ ጋሪሰን ከሚባሉ አሜሪካዊ ባልና ሚስት ጋር አሜሪካ ለመሄድ ወሰነች:: ለእናቷ አንድ ልጅ ስለበረች በመከራ ነው ልትሄድ የቻለችው:: ኒው ዮርክ እንደደረሰች ሆቴል ገብታ የቅርብ ዘመድዋን ያኔ ገና አምባሳደር አልነበሩም ወይዘሪት ዮዲት እምሩን አግኝታ ከሳቸው ጋር ብዙ ጥሩ ጊዜ አሳለፈች:: በሳቸውም አማካኝነት የተባበሩት መንግስታትን ጎበኘች:: ኒው ዮርክን በደንብ አድርጋ ከጎበኘች በኋላ ወደ እነ ጋሪሰን ከተማ ወደ ማዲሰን ዊስኮንስን ሄደች:: ባጠቃላይ የእናቴ የአሜሪካ አድቬንቸር ወደ ዓመት ያህል ነበር:: ደፋርነቷን ስለወደድኩት ነው ያካፈልኳችሁ::