Maysh Media.Com

Maysh Media.Com የአራት ማዕዘናት የመረጃ ማዕከል

4 ሎሚ  ገበያ ይዘው የወጡት እናት ( እመትገሎ ኮበሺህ)!"በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አራት ፍሬ ሎሚ ይዘው ለመሸጥ ገበያ ወጥተው በነበሩበት ምስላቸው የብዙዎችን ልብ የሰበሩትና ከፍተኛ መነጋገሪ...
08/06/2026

4 ሎሚ ገበያ ይዘው የወጡት እናት ( እመትገሎ ኮበሺህ)!

"በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አራት ፍሬ ሎሚ ይዘው ለመሸጥ ገበያ ወጥተው በነበሩበት ምስላቸው የብዙዎችን ልብ የሰበሩትና ከፍተኛ መነጋገሪያ የሆኑት እናት እመት ገሎ ኮበሺህ፣ ሰይፉ ፋንታሁን አጊንቷቸዋል።

እመት ገሎ (Gelo Kebeshi) ይባላሉ። በአዲስ አበባ ከተማ ከ20 ዓመታት በላይ ኖረዋል። አማርኛ ቋንቋ ብዙም ስለማይችሉ የሚግባቡት በጉራጊኛ ነው።

ህይወታቸውን በጉሊት ንግድ እየደገፉ፣ በዚህ እድሜአቸው ዛሬም ድረስ በላስቲክ በተሰራ ጎጆ (መጠለያ) ውስጥ ነው የሚኖሩት።

እማማ ወደ ገበያ የወጡት 4 ፍሬ ሎሚ ብቻ ይዘው ነበር። የያዟት 4 ሎሚ ተሸጣላቸው፣ ለልጆቻቸውና ለልጅ ልጆቻቸው የሚሆን አንድ እንጀራ ገዝተው ለመግባት... የቤት ነገር ቢያስጨንቃቸው እንጂ በዚህ በደከመ እድሜአቸው ድጋፍ እንጂ ድካም አይገባቸውም ነበር።

እማማ ሰው እጅ ከመጠባበቅና ከመለመን ይልቅ፣ በወዛቸው ሰርተው ለመኖር የሚያሳዩት ተጋድሎ ለእኛ ለወጣቶቹ ትልቅ የሥራ ፍቅርና የጽናት ትምህርት ነው። ነገር ግን አቅማቸው የደከመ አረጋዊ እናት በመሆናቸው የሁላችንም ሰብአዊ ድጋፍ አሁን ያስፈልጋቸዋል።

የእማማን እንባ ማበስ የሁላችንም ድርሻ ነው።የባንክ አካውንት፦1000769117125 Gelo Kebeshi (የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)"

''ሐይማኖቱን እንኳ ተዉለት! ዮናስ ዘውዴ ከበደ''በዓለም ከድካም በቀር ምንም ላልተረፈው፤ የዕለት ተዕለት ሕይወቱን ለማሸነፍ ብርቱ ትግል ለሚያደርገው፤ መሠረታዊ የሚባሉ ነገሮችን ለሟሟላት ...
05/06/2026

''ሐይማኖቱን እንኳ ተዉለት! ዮናስ ዘውዴ ከበደ''

በዓለም ከድካም በቀር ምንም ላልተረፈው፤ የዕለት ተዕለት ሕይወቱን ለማሸነፍ ብርቱ ትግል ለሚያደርገው፤ መሠረታዊ የሚባሉ ነገሮችን ለሟሟላት ብቻ ሲለፋ ዘመኑን ለሚፈጀው፤ ቢከፋው፣ ቢያዝን፣ ቢመረው በምድር ምንም መጽናኛ ለሌለው፣ ለዚህ ምስኪን ሕዝብ... ልቡ ሲበርደው፤ አንጀቱ አልችል ሲለው የሚጽናናበትን ሃይማኖት እንኳ ተዉለት እንጂ።

በብዙ መከራ ውስጥ ለሚያልፍ፤ ከፀሐይ በታች ሁሉም ዓይነት የመከራ ዶፍ ለዘነበበት፤ አለኝ ብሎ የሚማጸንበትን፣ ይኽን ዓለም የሚንቅበትን፤ የተጓደለበትን ምድራዊ ፍትሕ በትዕግሥት እንዲያሳልፍ ምክንያት የሆነውን እምነቱን እንዴት አይተዉለትም?

እንደ ሕዝብ ከቀዬው ተፈናቅሏል፣ በቋንቋው ተሰዷል፣ በሰውነቱ ተጎሳቁሏል፣ በቅድመ አያቶቹ ታሪክ ምንም የማያውቀው ሰው፤ ላልነበረበት ጊዜ በመካካሻነት በጠላትነት እየተፈራረጀ እንዲኖር ተፈርዶበታል። ይኽ በሕዝቦች መካከል የተዘራ እንክርዳድ ነው። በፓለቲካው ዓለም በጸብ ለሚነግዱ አካላት ይኽ እንክርዳድ እንደ ትልቅ የኃይል መሣርያ በማገልገል ዘልቋል።

ሃይማኖት ግን መነካት የሌለበት እሳት ነው። ሃይማኖት የምትጫወትበት ምድራዊ እሳት አይደለም። ለሚያምኑት የመለኮት እሳት ነው። ከቅጽሩ ወዳልተቀደሰ የፖለቲካ ሜዳ ልታወጣው ብትሞክር ቅድሚያ የሚፈጅህ አንተኑ ነው። ሃይማኖት ሀገር እንደ ሀገር እንድትቀጥል ሕዝብን ከሕዝብ አንድ አድርጎ አያይዞ በኅብረት አቆይቷል።

ፈርሀ እግዜርም ከትውልዱ ላይ እንዳይጠፋ ግብረገብን በማሥረጽ “moral compass” ሆኖ ያገለገለውም ሃይማኖት ነው። ኅሊናውን በጥላቻ የታወረ ሰው ሊገድልህ ቢመጣ ቢያንስ “በእግዜር፥ በጌታ፣ በማርያም፥ በአሏህ፥ በዋቃ... ብቻ በፈጠረህ!” ትለዋለህ። እንደ ሕዝብ ተከባብረን የኖርነው የሠለጠነ ሕግና ሥርዓት ስላለን አልነበረም። ይልቁንም በፈጠረን አምላክ በኩል አንድ እንደሆንን ስለሚሰማን ነበር።

እንደ ሕዝብ የሥልጣኔ ታሪክ ቢኖረንም ቅርብ ጊዜ ያስተናገድናቸው ቀውሶችና የሰማናቸው ዜናዎች ባለአእምሮዎች ለመሆን ብዙ እንደሚቀረን፤ ሥልጡን ነን ብለን የምንመጻደቀውን ያህል ሥልጡን እንዳልሆንን ይናገራሉ። የትምህርት፣ የጤና፣ የፍትሕ... ሥርዓቶቻችን በስብራት የተሞሉ ናቸው። ምንን ተማምነን ምንን እንደምናፈርስ አናውቅም።

በርሀብ ብዛት ከአንጀቱ የተጣበቀ ሆዱ እስኪቀደድ ድረስ እያከከ የፒያሳን ወርቅ ቤቶች ያለስርቆት ውልብታ ደክሞት የሚደገፍ የ'ኔ ቢጤና ምንዱባን ያላጣነው በእንተ ስማ ለማርያም ብሎ የሚላስ የሚቀመስ በማምሻ እንደማያጣ ተስፋ ስለሚያደርግ ነው። እንጂማ የሚበላው ያጣ ሕዝብ መሪውንም እስከ መብላት ይደርሳል።

የሃይማኖትን አንድነትን የነጠቅከውን ሕዝብ በምን አንድ ታደርገዋለህ? ነገ ከነገ ወዲያ የእንትን ክልል እግዜር ከእንትን ክልል እግዜር ጋር ኅብረት እንደሌለው በግልጽ የሚሰበክበት ጊዜ ይመጣል። የሃይማኖት አንድነትን ማዳከም (ሲዳከምም በዝምታ ማየት) እያደር ቅጥ ላጣ ዓለማዊነት፣ ግብረሰዶማዊነት... አውሮፓ እየተሰቃየ ላለበት የስመ ሥልጣኔ በሽታና ውጥንቅጥ ሁሉ በር እንደመክፈት ነው። በቀሪው ዓለም ሲቀደስባቸው የነበሩ ትላልቅ ካቴድራሎች መጠጥ ቤትና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ሆነዋል።

በክርስትና ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና።
አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችንም በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ነን። (ገላ. 3፥27-28) ክርስቶስ በሞቱ ያላስታረቀው የለም። አንድ በየቀኑ በአባታችን ሆይ ጸሎቱ “ይቅር በለን... እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል” እያለ የሚጸልይ ሰው እንዴት እና ከመቼው ? የሀጢአት ማወራረድ ውስጥ ይገባል?

በክርስቶስ ስም የተመሠረተች ቤተ ክርስቲያንን ለመከራ አዲስ አይደለችም። የመከራ ዘመናቶች አሏት። ነገር ግን ክርስትና ሥር የሚሰደው ደግሞ በመከራ ውስጥ ነው። ሊቁ ጠርጡለስ “The blood of the Martyrs is the seed of the church” ይላል። ሰማዕታት የቤተ ክርስቲያን ምርጥ ዘር ናቸው። በዚህ ሁሉ መሃል ግን ቤተ ክርስቲያንን የነኳት ኔሮን እና ማርከስ ኦሬሊየስ የት ናቸው?

ቤተ ክርስቲያን ግን ይኸው አለች። ትኖራለችም። ይኽች ቤተ ክርስቲያን በየሆስፒታሉ ለወደቁ ሕሙማን፣ በየወኅኒው ለታሰሩ፣ አርሰው ዝናምን ለሚጠብቁ፣ በስደት በሰው ሀገር ላሉ፣ ለአእዋፋትና ለአራዊት፣ ይልቁንም ደግሞ ስለአገር ሰላም ሌሊት ተቀን የምትጸልይና የምትማልድ እመቤት ናት። በደመራ ዕለት እኔ በጥምቀት ዕለት ብቻ ሳይሆን በመከራዋ ቀን የሚመጡላት እልፍ ልጆች አሏት። ኖረው ብቻ ሳይሆን ሞተው የሚያከብሯት አዕላፍ ልጆች አሏት። የድረሱልኝ ጥሪዋን ሰምተው ልጅ የእናቱን ድምፅ ሰምቶ እንደሚገሰግስ በጓቿ ድምፃን ሰምተው በቅጥር ግቢዋ ይሰበሰባሉ። በክንፎቿ ይጋረዳሉ ይጋርዱማል።

ቤተ ክርስቲያን ሆይ እንደ አንድ ዜጋ በአንቺ ወቅታዊ ጉዳይ ከመጨነቅ የሚይዘኝ ነገር የለም። እናም ስለሰላምሽ እጸልያለሁ!

አገሬ ሆይ እንደ አንድ ከምድርሽ እንደ በቀለ ዜጋ በአንቺ ወቅታዊ ጉዳይ ከመተከዝ የሚይዘኝ ነገር የለም። እናም ስለሰላምሽ አጥብቄ አነባለሁ !

ዮናስ ዘውዴ ከበደ

 " በሆለታ ፍርድ ቤት ውስጥ የተፈጸመ የተኩስ ጥቃት ሁለት ሰዎችን ለሞት ዳርጓል ተባለበኦሮሚያ ክልል ሆለታ ከተማ፣ በወልመራ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ውስጥ ዛሬ ረፋድ የተፈጸመ የ...
04/06/2026



" በሆለታ ፍርድ ቤት ውስጥ የተፈጸመ የተኩስ ጥቃት ሁለት ሰዎችን ለሞት ዳርጓል ተባለ

በኦሮሚያ ክልል ሆለታ ከተማ፣ በወልመራ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ውስጥ ዛሬ ረፋድ የተፈጸመ የተኩስ ጥቃት ሁለት ሴቶችን ለሞት እንዳዳረሰ መረጃዎች ያመለክታሉ።

እንደ ተሰማው መረጃ፣ አንድ ተከሳሽ በቤተሰብ ጉዳይ ከሚስቱ ጋር በሚካሄድ ክርክር ላይ በፍርድ ቤት ተገኝቶ ሳለ፣ ዳኛዋ ውሳኔ በምታነብበት ወቅት በሽጉጥ ተኩስ ከፍቶ ሚስቱንና ዳኛዋን መግደሉ ተነግሯል።

በጥቃቱ ሕይወቷን ካጣችው ዳኛ መካከል ወርቄ ፈካንሳ የተባለች መሆኗም ተጠቅሷል። የተጠቀሰው ተከሳሽ እንዴት መሣሪያ ይዞ ወደ ፍርድ ቤት መግባት እንደቻለ እና ከጥቃቱ በኋላ በምን ሁኔታ እንደተያዘ ወይም እንዳመለጠ እስካሁን በይፋ የተገለጸ መረጃ የለም።

ክስተቱ በፍርድ ቤቶች የደህንነት አጠባበቅና የሕግ የበላይነት ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ጥያቄዎችን አስነስቷል። ባለሥልጣናት በጉዳዩ ላይ ምርመራ እያካሄዱ መሆኑ ተገልጿል።"(ማሀበራዊ ድህረገጽ )

22 ዓመት ዛሬ ተሸነፈ የፅናት ጉዞ በክብር ተሞሸረ
24/05/2026

22 ዓመት ዛሬ ተሸነፈ
የፅናት ጉዞ በክብር ተሞሸረ

አርሰናል ከ20 ዓመታት በኋላ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ደረሰ!ከሁለት አስርተ ዓመታት ረጅም ጥበቃ በኋላ አርሰናል ዳግም የአውሮፓ እግር ኳስ ቁንጮ ወደሆነው የሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ መድረሱን በ...
05/05/2026

አርሰናል ከ20 ዓመታት በኋላ ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ደረሰ!

ከሁለት አስርተ ዓመታት ረጅም ጥበቃ በኋላ አርሰናል ዳግም የአውሮፓ እግር ኳስ ቁንጮ ወደሆነው የሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ መድረሱን በታላቅ ድምቀት አረጋግጧል።

ዛሬ ምሽት በኤምሬትስ ስታዲየም በተደረገው ተጠባቂ የግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ አርሰናል የስፔኑን ጠንካራ ክለብ አትሌቲኮ ማድሪድን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

የለንደኑ ኮከብ ቡካዮ ሳካ በግሩም ሁኔታ ያስቆጠራት ብቸኛ ግብ መድፈኞቹን ለዚህ ታላቅ ድል አብቅታለች።

ክለቡ በመጀመሪያው ጨዋታ በነበረው ውጤት ታክሎበት በድምር 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አትሌቲኮን በመርታት ለፍፃሜው ማለፉን አረጋግጧል።

ይህም ውጤት አርሰናል ከ20 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአውሮፓ መድረክ ለታላቁ የሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ መድረስ የቻለበት አዲስ ታሪክ ሆኖ ተመዝግቧል።

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አሁን የቀረው አንድ እርምጃ ብቻ ነው፤ የአውሮፓን ክብር በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመጨበጥ ወደ ወሳኙ የፍፃሜ ጨዋታ ያመራል።

ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የትግራይ መንግስት ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ​በትግራይ ክልል ለሦስት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው የክልሉ ምክር ቤት በድጋሜ በመሰባሰብ ባካሄደው ጉባኤ ዶ/ር ደብረፅዮ...
05/05/2026

ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የትግራይ መንግስት ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

​በትግራይ ክልል ለሦስት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው የክልሉ ምክር ቤት በድጋሜ በመሰባሰብ ባካሄደው ጉባኤ ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤልን የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ መረጠ። ምክር ቤቱ ወ/ሮ ኪሮስ ሓጎስን አፈ ጉባኤ፣ ወ/ሮ ምህረት በርሄን ደግሞ ምክትል አፈ ጉባኤ አድርጎ በመሾም ጉባኤውን አጠናቋል።

የክልሉ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት እና የፌዴራል መንግስት በጉዳዩ ላይ እስካሁን ያሉት ነገር የለም።(ማህበራዊ ድህረገጽ )

  በባለሥልጣናትና በአርቲስቶች የተዘረፈው የ98 ቢሊዮን ብር ቅሌት በኦዲት ምርመራ መረጋገጡ ተነገረ::የፌዴራል ፖሊስ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ባቀረበው ...
04/05/2026



በባለሥልጣናትና በአርቲስቶች የተዘረፈው የ98 ቢሊዮን ብር ቅሌት በኦዲት ምርመራ መረጋገጡ ተነገረ::

የፌዴራል ፖሊስ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ባቀረበው አስደንጋጭ ሪፖርት፣ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ታዋቂ አርቲስቶች በጋራ በመሆን በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ግዙፍ የሙስና ወንጀል መፈጸማቸውን ይፋ አድርጓል።

በኦዲት ምርመራ የተረጋገጠው ይህ የዘረፋ መጠን 78 ቢሊዮን ብር እና 134 ሚሊዮን ዶላር ሲሆን፣ በወቅታዊ ምንዛሬ በአጠቃላይ ከ98 ቢሊዮን ብር በላይ የሀገር ሀብት መመዝበሩ ተረጋግጧል።

የወንጀል ምርመራ ኦፕሬሽን መምሪያ ምክትል ኮሚሽነር ሙሊሳ አብዲሳ እንደገለጹት፣ ወንጀለኞቹ ዝርፊያውን የፈጸሙት እጅግ በረቀቀ ዘዴና የተዘረፈውን ንብረት ወደ ውጭ ሀገራት በማሸሽ ቢሆንም፣ ከዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ጋር በተደረገ የተቀናጀ ጥረት ማስረጃዎችን ማሰባሰብ ተችሏል።

እንዲህ ያለ ግዙፍ የውስጥ ዝርፊያ መጋለጡ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል። ፖሊስ የምርመራ ሂደቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አሳውቋል።

ዘገባው የሪፖርተር ነው::

02/02/2026

" "!

የሰሞኑ አነጋጋሪ ተንቀሳቃሽ ምስል፣ የሚገርም ትወና ፣የሚገርም መልዕክት ።

የነጻነት ወርቅነህን ሕጋዊ የቤተሰብ ተወካይን ስለማሳወቅበአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ድንገተኛ ሕልፈት ምክንያት ሐዘናችንን ሐዘናችሁ በማድረግ ላፅናናችሁን በሙሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን...
28/01/2026

የነጻነት ወርቅነህን ሕጋዊ የቤተሰብ ተወካይን ስለማሳወቅ

በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ድንገተኛ ሕልፈት ምክንያት ሐዘናችንን ሐዘናችሁ በማድረግ ላፅናናችሁን በሙሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን። የአርቲስት ነፃነት ቤተሰብ ወደመጡበት ሃገር ከመመለሳቸው በፊት ለቤተሰቡ የቅርብ ሰዎች ሕጋዊ ውክልና ሰጥተዋል ።

በመሆኑም ፣ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህን የተመለከቱ ማናቸውንም የሥራ ጉዳዮች እንዲከታተሉና እንዲያስፈጽሙልን በማለት አቶ አስናቀ ንጉሴን የወከልን መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን።

ከአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ስም ጋር በተያያዘ ማንኛውም ጉዳይ ቢኖራችሁ አቶ አስናቀ ንጉሴን ማነጋገር እንደምትችሉ እንገልፃለን።

ከዚህ በተጨማሪም ፣ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ እና ቤተሰቡን የተመለከተ የትኛውንም ዓይነት መረጃ ማግኘት ስትፈልጉ ተወካዩን በአካል ወይም በስልክ ማነጋገር ትችላላችሁ። በተለይ የሟችንም ሆነ የቤተሰቡን ስም የሚያጠፉ እንዲሁም ክብር የሚያጎድፉ ስሁት ትርክቶችን በማህበራዊ ሚዲያ እንዳይዘዋወሩ ለማስቀረት እንዲቻል ፣ ትክክለኛ መረጃዎችን ከሕጋዊ ተወካያችን ብቻ እንዲቀበሉ ፤ የተወካያችንን ቃል ብቻ ጠቅሰው እንዲጠቀሙ እንጠይቃለን።

ከዚህ ውጭ በሆነ መንገድ የሟችንም ሆነ የቤተሰቡን መልካም ስም የሚያጎድፍ ስሁት የፈጠራ ታሪክ ማሰራጨት በሕግ የሚያስጠይቅ መሆኑንም እናስታውሳለን።

ስልክ :- 0903886870 ( አስናቀ ንጉሴ )

#ቤተሰቡ

በማድረግ መልዕክቱን እንድታዳርሱልን እንጠይቃለን ።

በ240 ሚሊዮን ብር የተገነባው የሲኤምሲ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ለምረቃ በቃ ​በአዲስ አበባ ከተማ በልዩ ውበቱ በሚታወቀው ሲኤምሲ (CMC) አካባቢ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክ...
25/01/2026

በ240 ሚሊዮን ብር የተገነባው የሲኤምሲ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ለምረቃ በቃ

​በአዲስ አበባ ከተማ በልዩ ውበቱ በሚታወቀው ሲኤምሲ (CMC) አካባቢ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ታላቅነት የሚመጥን አዲስና ግርማ ሞገስ ያለው ቤተ መቅደስ ግንባታው ተጠናቆ ዛሬ ተመርቋል ።

​💰 የ240 ሚሊዮን ብር መንፈሳዊ ኢንቨስትመንት

ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ከ240,000,000 ብር በላይ ወጪ የተደረገበት ሲሆን፣ ገንዘቡም በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር በሚኖሩ ምእመናን፣ በበጎ አድራጊ ባለሀብቶችና በታላቅ የሕዝብ ተሳትፎ የተሰበሰበ ነው።

​🏗️ የሕንጻው ልዩ ገጽታዎች
አዲሱ ቤተ መቅደስ ጥንታዊ የኢትዮጵያ የኪነ-ህንጻ ጥበብን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር አዋህዶ የያዘ ሲሆን የሚከተሉትን አካቷል፦

​ሰፊ ቤተ መቅደስ፦ በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናንን የሚይዝ፣ በቅዱሳን ስዕላትና ጥበቦች ያሸበረቀ።

​ዘመናዊ የአስተዳደር ማዕከል፦ ቢሮዎች፣ የካህናት መቆያና የመሰብሰቢያ አዳራሾች።

​የወጣቶች ማዕከል፦ የሰንበት ትምህርት ቤት ክፍሎችና ቤተ-መጻሕፍት።

​አረንጓዴ ልማት፦ ለጸሎት ምቹ የሆኑ ስፍራዎችና ሰፊ የመኪና ማቆሚያ።(ማህበራዊ ድህረገፅ)

Address

Bole Road/Africa Avenue
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Maysh Media.Com posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Maysh Media.Com:

Share