10/12/2025
ልማት ባንክ ስለሰጠው ማስተባበያ ትንሽ እንበላችሁ❗️
--------------------------------------------
በዶክመንቱ እውነትነት ላይ የሚያጠራጥር ነገር የለም። ዶክመንቱ 100% እውነተኛ ዶክመንት ነው። ባንኩ ሳይታሰብ መረጃው ሊክ ስለተደረገበት በተፈጠረው ጫና ምክኒያት ማስተባበየውን በቀድሞው ኮሙኒኬሽን ዳይክተር በኩል ተፅፎ በፍጥነት እንዲወጣ ተደርጓል።
የቀድሞው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ የአብስራ ከበደ የሚባል ሲሆን የዶ/ር ዮሃንስ ዋና ሰው እንደሆነ ይነገርለታል። የሚውቁት አብዛኛዎቹን የዶ/ር ዮሃንስ ወንጀሎች የሚያመክን ስውሩ ሰው ይሉታል። የፋና ቲቪ ጋዜጠኛ የነበረ ሲሆን የግለሰብ ግንባታ ላይ ጎበዝ ነው ይባልለታል።
ዶ/ር ዮሃንስ ልማት ባንክ ላይ ወንጀሎችን አጣጥሞ ሰርቶ ሲበቃው ወደ አማራ ባንክ ከመጣ በኋላ ልማት ባንክ ብዙ አልቆየም። ልጁ የዶ/ሩ ቀኝ እጅ እና ገመና ከታች በመሆኑ ከልማት ባንክ ወደ አማራ ባንክ እንዲመጣ አድርጎታል። የአብስራ ከበደ ከመጋረጃ ጀርባ ሁኖ በዶ/ር ዮሃንስ እያንዳንዷ ውሳኔ ላይ አጁ አለበት ይባላል።
ሰሞኑን ከልማት ባንክ በደረሰን በዶ/ር ዮሃንስ ላይ ያጠነጠነውን ዶኩመንት በተመለከተ የነበረውን access ተጠቅሞ ማስተባበያውን የፃፈው እሱ ነው የሚል ጥርጣሬ እየመጣ ነው። በነገራችን ላይ ይሄም ሌላ ወንጀል፣ ሌላም ቅሌት ነው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ገለልተኛ ተቋም ተጋብዝ እንዲያጠና በተደረገው መሰረት ዶ/ር ዮሃንስ ልማት ባንክ በነበረባቸው ጊዜዎች 32 ሕጎችን የጣሰባቸው አሰራሮችን የያዘ ባለ 16 ገፅ ዶክመንት አጃችን ይገኛል። በዚህ ዶክመን ውስጥ ስለተበላሸ ብደርም ብዙ ተብሏል። በዶ/ር ዮሃንስ 4% ሪፖርት ተደርጎ አገለልተኛ አጣሪ ቡድን በኩል 52% ገደማ የተበላሸ ብድር እንዳጋጠመ ተረጋግጦ ልማት ባንክም ቅጣት እንዲተላለፍበት ተደርጓል።