14/07/2018
"የተባረከ እና የተማረ መሪ ከለመንን ቆየን ባይማርም እንኳ የተባረከ መሪ ይስጠን!! "ቴዎድሮስ ካሳሁን
ኑ የፍቅር ጀግናችንን ኤርፓርት ተገኝተን እናክብረው!!!
Teddy Afro ዛሬማታ በልደቱ ቀን ከምሽቱ በ 3 ሰዓት ወደ ሚናፍቃት ሀገሩ ኢትዮጵያ ይገባል::
ኢትዮጵያ ፍቅር ያሸንፋል ኤርትራ!!
ሳልሳዊ ቴዲ አፍሮ _ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ሁለት ሀገራት ሆነው ከተለያዩ ጀምሮ ስለ ሁለቱ ሀገራት መለያየት ካሳዘናቸው እና ካሳሰባቸው ግንባር ቀደሙ ብቻ ሳይሆን መለያየታቸውም አግባብ የሌለው የአንድ ሀገር ልጆች መሆናቸው በዳህላክ ፣ ፊዮሪና ጓል አስመራ ዜማዎቹ እንዲሁም በየመድረኩ ሁሌም ኢትዮጵያ እና ኤርትራ እያለ ፍቅር ፣ ሰላም ፣ አንድነትን ፣ ብሩህ ተስፋን ሰንቆ ሲያቀነቅን ቆይቷል:: ለኢትዮጵያ ኤርትራ አንድነትን ትልቁን ሚና ከመጫወቱም ባሻገር እስካሁን ድረስ በልቡ አንድ አድርጓቸው ኖሯል:: ቴዲ አፍሮ ዛሬ ላይ ይህ የፍቅር ጊዜ እሱ በህይወት ቆሞ ስንት መከራ ያየበትን ፣ የታሰረበትን ፣ ኮንሰርት የተሰረዘበትን ፣ አልበም እንዳያስመርቅ እና የውጪ ጉዞዎቹ የተስተጓገሉበት ያን የመከራ እና የግፍ ዘመን አልፎ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በፍቅር በአንድነት #ወደፍቅርጉዞ ሲዘምሩ ፣ ያንተን የሁልግዜም ህልም #በፍቅርያሸንፋል መርህ ተሳስበው ተዋደው ስናይ ትልቅ ትርጉም ይሰጠናል::
እና ቴዲ አፍሮ ዛሬ ቅዳሜ ማታ ሀገሩ ሲገባ መላው የቴዲ አድናቂዎች፣ ኢትዮጵያዊያን ኤርትራዊያን አክባሪዎቹ ይህን የፍቅር ንጉስ እና ሐዋሪያ ቦሌ ኤርፖርት በመገኘት ደማቅ አቀባበል ልናደርግለት ተዘጋጅተናል።
እርሶስ ተጋጅተዋል የፍቅር ንጉሱን ለማክበር???
ማሳሰቢያ _ ኤርፖርት ስትመጡ ከቻላችሁ የእሱ ምስል ያለበት ቲሸርቶች እና ለንጉሱ ያለንን አክብሮት የምንገልፅበት መልዕክቶችን ይዘን ብንመጣ ይመረጣል::
ፍቅር አሸንፏል!!!
ረጅም እድሜ ለሳልሳዊ ቴዲ አፍሮ!
ጃ ያስተሰርያል!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ፍቅር ያሸንፋል!