ETHIO SAT DISH TEC

ETHIO SAT DISH TEC Et

አስቸኳይ የፍለጋ ጥሪ ሙባረክ ሰይድ እንድሪስ ⭐️⭐️⭐️ ሼር ሼር ሼር***ለሰው ልጅ በሙሉ ይድረስ! አንድን እናት ከጭንቅ፣ አንድን ህፃን ከጥፋት ለመታደግ ሰከንዶችን እንጠቀም። ከአቃቂ ቃሊ...
04/03/2026

አስቸኳይ የፍለጋ ጥሪ ሙባረክ ሰይድ እንድሪስ ⭐️⭐️⭐️ ሼር ሼር ሼር
***
ለሰው ልጅ በሙሉ ይድረስ! አንድን እናት ከጭንቅ፣ አንድን ህፃን ከጥፋት ለመታደግ ሰከንዶችን እንጠቀም።

ከአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው መብራት ሀይል አካባቢ የጠፋው ህፃን ሙባረክ ሰይድ እንድሪስ ይባላል በቀን 23/06/2018ዓ/ም ከቀኑ 11:0 ሰዓት አካባቢ ከመኖሪያ አካባቢው የጠፋው እድሜው 6 ዓመት ቀይ በእለቱ ጥቁር ትሸርት እና ነጭ ሱሪ ለብሷል

* ስም ሙባረክ ሰይድ እንድሪስ
* እድሜ 6 ዓመት

* ይህ መረጃ ለብዙ ሰው እንዲደርስ በማድረግ በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን። የእርስዎ አንድ ሼር የህፃኑን ህይወት ሊታደግ ይችላል።

* ይህን ህፃን ያያችሁ ወይም ያለበትን የምታውቁ በነዚህ ስልኮች በአስቸኳይ ደውሉልን፦

* 0921635499
* 0912714945
* 0912268653

ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በአያቶላህ አሊ ኻሜኒ ሞት ሀዘናቸዉን እንደገለጹ ተደርጎ የተሰራጨው ስክሪን ቅጂ ሀሰተኛ ነው ሲል ኢትዮጵያ ቼክ አጋርቷል።ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በኢራ...
04/03/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በአያቶላህ አሊ ኻሜኒ ሞት ሀዘናቸዉን እንደገለጹ ተደርጎ የተሰራጨው ስክሪን ቅጂ ሀሰተኛ ነው ሲል ኢትዮጵያ ቼክ አጋርቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ሞት ሀዘናቸዉን እንደገለጹ የሚያሳይ ስክሪን ቅጂ (screenshot) በተለያዩ በማህበራዊ ትስስር ገጾች እየተጋራ ይገኛል።

ይህ ስክሪን ቅጂ “በወንድሜ አያቶላህ አሊ ኻሚኒ ሞት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እገልጻለሁ። ኻሚኒ ላለፉት 40 አመታት ኢራንን በለዉጥ ጎዳና የመሩ ብርቱ ሰው ናቸዉ” የሚል መልዕክት ይዟል። በተጨማሪም “ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለመላ ኢራናዊያን መጽናናትን እመኛለሁ” ይላል።

ኢትዮጵያ ቼክ በብዙዎች ጥቆማ መሰረት የዚህን ስክሪን ቅጂ ትክክለኛነት ለማጣራት በመጀመርያ መልዕክቱ የጠ/ሚሩ የማህበራዊ ሚድያ ገፆች ላይ እንዳለ ቅኝት አድርጎ እንደዚህ አይነት መልዕክት እንደሌለ ተመልክቻለሁ ብሏል።

በሁለተኛነት ይዘታቸው የተቀየሩ ፎቶዎችን ለመመርመር የሚረዳውን ‘Fotoforensics’ ድረ-ገጽን መጠቀሙን ኢትዮጵያ ቼክ ገልጿል።

ይህ ድረ-ገጽ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፌስቡክ ስም የሚገኝበት የስክሪን ቅጂዉ ክፍል የተነካካ ወይም በኮፒ ፔስት (Copy and Paste) ይዘቱ የተቀየረ እንደሆነ አሳይቷልም ብሏል።

በሌላ በኩል በስክሪን ቅጂዉ ላይ የሚገኘው ይዘቱ የተለጠፈበትን ጊዜ የሚያሳይ መግለጫ (Time Stamp) የፊደላት ቅርጽ (Font) ስህተት እንዲሁም ከበስተቀኙ የሚገኘው የግላዊነት ቅንብር የአለም ምስል (Public Privacy Setting Globe Icon) ደግሞ የአቀማመጥ ግድፈት (Misalignment) ያለበት መሆኑንም መመልከቱን ኢትዮጵያ ቼክ ገልጿል።

በተጨማሪም የስክሪን ቅጂዉ ዋና ይዘት ጽሁፍም በተመሳሳይ መልኩ የተለያዩ ግድፈቶች ያሉበት ሲሆን ይህም በቅንብር የተሰራ እንደሆነ የሚጠቁም ነው ብሏል።

በመጨረሻም፣ መረጃው በተለጠፈ በ14 ደቂቃ ውስጥ 44,500 ግዜ ሪአክሽን እንዳገኘ ማሳየቱ በጠ/ሚሩ የፌስቡክ ገፅ ላይ ያለውን መስተጋብር እንደማያሳይ አይተናል ሲል ኢትዮጵያ ቼክ ጨምሮ ገልጿል።

በሌላ በኩል ግን ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ኢራን በኩዌት ላይ የፈጸመችውን ጥቃት ተከትሎ ከኩዌት ልዑል አልጋ ወራሽ ጋር በስልክ መወያየታቸው እንዲሁም በአገሪቱ ላይ የሚፈጸም ጥቃትን በጽኑ ማውገዛቸውን የኩዌት የዜና ወኪል መዘገቡም ተገልጿል።

ምንጭ- ኢትዮጵያ ቼክ

አስቸኳይ የፍለጋ ጥሪ፡ ህፃን ሙባረክ ሰይድ እንድሪስ 🙏በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12፣ ልዩ ቦታው መብራት ሀይል ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ የጠፋው ህፃን ሙባረክ ሰይድ እንድሪስ ይባላል።...
03/03/2026

አስቸኳይ የፍለጋ ጥሪ፡ ህፃን ሙባረክ ሰይድ እንድሪስ 🙏

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12፣ ልዩ ቦታው መብራት ሀይል ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ የጠፋው ህፃን ሙባረክ ሰይድ እንድሪስ ይባላል።

* የጠፋበት ቀን 23/06/2018 ዓ.ም.
* የጠፋበት ሰዓት ከቀኑ 11፡00 ሰዓት አካባቢ
* እድሜ 6 ዓመት
* መለያ፡ መልኩ ቀይ ሆኖ በጠፋበት ወቅት ጥቁር ቲሸርት እና ነጭ ሱሪ ለብሶ ነበር።

ይህ መረጃ ለብዙ ሰው እንዲደርስ በማድረግ የህፃኑን ህይወት ለመታደግ ተባበሩን።

የእርስዎ አንድ "ሼር" ትልቅ ትርጉም አለው።

ህፃኑን ያያችሁ ወይም ያለበትን የምታውቁ በነዚህ ስልኮች በአስቸኳይ ደውሉልን፦

* 0921635499
* 0912714945
* 0912268653

"ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም!"

Via ቤተሰብ

ጉርሻ page

🌴🌴🌴

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ሳውዲን ለቆ ወጣ።‎‎በሳውዲ አረቢያ ዋና ከተማ ሪያድ ላይ፣ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ፣ የዓለማችን ውድ ተጫዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ፣ ቤተሰቡን ይዞ  በግል ጄቱ ሀገሪቱ...
03/03/2026

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ሳውዲን ለቆ ወጣ።

‎በሳውዲ አረቢያ ዋና ከተማ ሪያድ ላይ፣ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ፣ የዓለማችን ውድ ተጫዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ፣ ቤተሰቡን ይዞ በግል ጄቱ ሀገሪቱን ለቆ ወጥቷል።

‎የክርስቲያኖ ሮናልዶ 61 ሚሊዮን ዩሮ ዋጋ የሚያወጣው ቅንጡ የግል ጄት በሌሊት ሳውዲ አረቢያን ለቆ በመውጣት ወደ ማድሪድ አቅንቷል።

‎ሮናልዶ እዚህ ውሳኔ ላይ ያደረሰው በሪያድ የአሜሪካ ኤምባሲ ላይ የሰው አልባ አውሮፕላኖች ጥቃት ተከትሎ የቀጠናው ውጥረት ከፍተኛ ደረጃ ላይ በመድረሱ ነው።

‎የ41 አመቱ የእግር ኳስ ኮከብ ክርስትያኖ ሮናልዶ በሳዑዲ ዋና ከተማ ሪያድ ከባለቤቱ ጆርጂና ሮድሪጌዝ እና ከአምስት ልጆቹ ጋር እንደሚኖሩ የሚታወቅ ቢሆንም፣ ልጆቹና ባለቤቱ በአውሮፕላኑ ውስጥ ስለመሳፈራቸው ግን የተረጋገጠ ነገር የለም።

ዙሩ ከርሯል !" ኢራን 50 ሰሜን ኮሪያዎችን ትሆናለች "       ኔታንያሁ በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ወታደራዊ ግጭት አዲስ መልክ እየያዘ መጥቷል። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ...
03/03/2026

ዙሩ ከርሯል !

" ኢራን 50 ሰሜን ኮሪያዎችን ትሆናለች "
ኔታንያሁ

በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ወታደራዊ ግጭት አዲስ መልክ እየያዘ መጥቷል።

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ኢራን ከሰሜን ኮሪያ በበለጠ ለዓለም አደገኛ መሆኗን ገልጸዋል፡፡

የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን በበኩላቸዉ እስራኤልን በአንድ ሚሳኤል ለማጥፋት ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ኔታንያሁ ‹‹ኢራን 50 ሰሜን ኮሪያዎችን ትሆናለች›› ሲሉ ባስተላለፉት የቪዲዮ መልእክት ተደምጠዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የኢራንን አደገኝነት ሲያስረዱ ሰሜን ኮሪያን እንደ ማነፃፀሪያ ተጠቅመዋል።

ኔታንያሁ በንግግራቸው ሰሜን ኮሪያ የባለስቲክ ሚሳኤል እና የኒውክሌር ጦር ቢኖራትም፤ እንደ ኢራን "ሞት ለአሜሪካ" የሚል መፈክር ግን የላትም ብለዋል።

ነገር ግን ኢራን በዓላማዋ እና በአጥፊነት አቅሟ ‹‹50 ሰሜን ኮሪያዎችን›› እንደምትመጥን ገልጸዋል።

ኢራን የአሜሪካን እና የእስራኤልን ጥፋት እንደ ዋና ግብ ይዛ የተነሳች ሀገር መሆኗንም አጽንኦት ሰጥተዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ለቴህራን ያላቸውን የጸና ድጋፍ በይፋ ገልጸዋል።

መሪው በሰጡት መግለጫ፤ እስራኤልን ከዓለም ካርታ ላይ ለማጥፋት ‹‹አንድ ሚሳኤል ብቻ በቂ ነው›› በማለት የፒዮንግያንግን የኒውክሌር አቅም ለዛቻ ተጠቅመውበታል።

አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ እስራኤልን መምታት የሚያስችሉ የላቁ ሚሳኤሎችን ለኢራን ለማቅረብ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የሰሜን ኮሪያ መግለጫ የወጣው አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱት "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ" በተፋፋመበት እና የኢራኑ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸው በተረጋገጠበት ወቅት ነው።

በአሁኑ ወቅት ቻይና ለኢራን የላቁ ሚሳኤሎችን እያቀረበች እንደሆነ ይነገራል።

ቻይና ግን ለኢራን ወታደራዊ ድጋፍ እንደምታደርግ የሚገልጹ ሪፖርቶችን አስተባብላለች፡፡

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቀደም ሲል ‹‹ትልቁ›› ጦርነት ሊመጣ ይችላል ብለው የሰጡትን ማስጠንቀቂያ ይህ አዲስ አሰላለፍ ይበልጥ እያጠናከረው ይገኛል።

ይህ በኢራን፣ ሩሲያ፣ ቻይና እና ሰሜን ኮሪያ መካከል እየተፈጠረ ያለው ወታደራዊ አሰላለፍ የቀጣናውን ግጭት ወደ ዓለም አቀፍ ጦርነት ሊቀይረው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ እና በጂኦ-ፖለቲካዊ መረጋጋት ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል።

# Fm 107.8

አንዳንዴ ኑሮ ምርጫ ታሳጣለች። ብዙዎቻችን እንደ ቀላል ነገር የምናየው፣ ምናልባትም "ለቁምነገር አይበቃም" ብለን የምንተወው ነገር፣ ለሌሎች የዕለት ጉርስ፣ የህይወት መግፊያ ይሆናል።​ይህቺን...
03/03/2026

አንዳንዴ ኑሮ ምርጫ ታሳጣለች። ብዙዎቻችን እንደ ቀላል ነገር የምናየው፣ ምናልባትም "ለቁምነገር አይበቃም" ብለን የምንተወው ነገር፣ ለሌሎች የዕለት ጉርስ፣ የህይወት መግፊያ ይሆናል።
​ይህቺን እናት ተመልከቱ። እጃቸው ላይ ያለው ሀብት ቢቆጠር፣ ምናልባት የሳንቲሞች ዋጋ እንኳን የለውም። ነገር ግን ተስፋ አልቆረጡም። ቤታቸው ተቀምጠው፣ እጃቸውን አጣጥፈው የሰው ፊት ከማየት፣ በዚያችው አቅማቸው የፈቀደላትን፣ የጨርቅ ኳስ ሰርተው በመሸጥ፣ ክቡር ህይወታቸውን በክብር ይመራሉ።
​ይህ ምስል፣ የሀገራችንን ጥልቅ የድህነት መልክ ብቻ ሳይሆን፣ የማይበገረውን የኢትዮጵያዊ እናት ጠንካራ መንፈስም ያሳያል። የጨርቅ ኳስ ሸጠው በሚያገኙት ትንሽ ሳንቲም፣ ምናልባት የራሳቸውን ወይም የቤተሰባቸውን ሆድ ይሞላሉ። ለኛ ቀላል የሚመስለው የጨርቅ ኳስ፣ ለሳቸው ግን የህልውና መሰረት ነው።
​ህይወት እንዲህ ናት። አንዳንዱ በምቾት ሲኖር፣ አንዳንዱ ደግሞ ቀዳዳውን ለመድፈን ይታገላል። ግን ያስታውሱ፣ ክብር በስራ እንጂ በስራው አይነት አይለካም። ይህቺ እናት ለኛ ትልቅ ትምህርት ናቸው።

የእስራኤል ጦር የሄዝቦላህ የስለላ አዛዥን መግደሉን አስታወቀ***የእስራኤል ጦር የሄዝቦላህ የስለላ ዋና መሥሪያ ቤት ኃላፊ ሆኖ ያገለገለውን ሁሴን ማክሌድን በአንድ ሌሊት መግደሉን አስታውቋል...
03/03/2026

የእስራኤል ጦር የሄዝቦላህ የስለላ አዛዥን መግደሉን አስታወቀ
***
የእስራኤል ጦር የሄዝቦላህ የስለላ ዋና መሥሪያ ቤት ኃላፊ ሆኖ ያገለገለውን ሁሴን ማክሌድን በአንድ ሌሊት መግደሉን አስታውቋል።

በሊባኖስ ዋና ከተማ ቤይሩት ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት መገደሉን ወታደሮቹ አስታውቀዋል።

የሄዝቦላህ ታጣቂ ቡድን የኢራኑን ሉዓላዊ መሪ አያቶላ አሊ ካሜኒን ግድያ "ለመበቀል" በሚል በእስራኤል የጦር ሰፈር ላይ ጥቃት መሰንዘሩ ይታወቃል።

​የሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሄዝቦላህ በኢራን ላይ የተሰነዘረውን ጥቃት ለመመከት ወደ ጦርነቱ መግባቱንና የመጀመሪያዎቹን ሮኬቶች ወደ ሰሜን እስራኤል መተኮሱን አረጋግጧል።

የቡድኑ መሪ ናይም ቃሲም "ወረራውን የመመከት ግዴታችንን እንወጣለን፤ የክብርና የጥንካሬ ሜዳውንም አንለቅም" ሲሉ ዝግጁነታቸውን ገልጸዋል።

ሄዝቦላህ ወደ እስራኤል ሮኬቶችን መተኮሱን ተከትሎ፥ የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት ከ50 በላይ ከሚሆኑ የሊባኖስ መንደሮች ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ለቀው እንዲወጡ አዟል።

እስካሁን በስለላ አዛዡ ግድያ ዙሪያ ከቡድኑ የተሰጠ ምንም አይነት አስተያየት የለም።

08/03/2022
Manchester United defence in photo shoot 🤔🤔🤔
07/03/2022

Manchester United defence in photo shoot 🤔🤔🤔

ይህን ጨዋታ በጉጉት እንደምጠብቅ ምንም እየጠበኩ አይደለም።
03/03/2022

ይህን ጨዋታ በጉጉት እንደምጠብቅ ምንም እየጠበኩ አይደለም።

Address

Asco
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ETHIO SAT DISH TEC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ETHIO SAT DISH TEC:

Share