22/05/2026
የአእምሮ ህመም እክል ያለባትን ግለሰብ መፀዳጃ ቤት ውስጥ አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ !🤔
#አሪፍመዝናኛ ◆ በቦረና ዞን ያቤሎ ከተማ አስተዳደር ውስጥ የአእምሮ ሕመም እክል ያለባትን ግለሰብ በመፀዳጃ ቤት አስገብቶ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት መቀጣቱን ፖሊስ አስታወቀ።የቦረና ፖሊስ ዋና መምርያ የወንጀል ምርመራ ክፍል ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ዲባባ ዲዳ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት ተከሳሽ አብረሃም ጭርቆ ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ረፋድ አራት ሰዓት ላይ በያቤሎ ከተማ ውስጥ ድርጊቱን መፈጸሙ ተገልጿል።
ተከሳሹ የአዕምሮ ህመም እክል ያለባትን እና በተከሰተባት ሕመም ምንም አይነት የማገናዘብ እና የመረዳት ችሎታ የሌላትን በመፀዳጃ ቤት አስገብቶ እጅግ አስነዋሪ በሆነ መንገድ የመድፈር ጥቃቱን መፈፀሙን የተመለከቱ የአካባቢ ሰዋች ለፖሊስ በሰጡት መረጃ ከመፀዳጃ ቤቱ ሳይወጣ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።ፖሊስም ተከሳሹን በቁጥጥር ስር በማዋል የአእምሮ ህመም እክል ያለባትን ሴት በጥንቃቄ በማስመርመር የመደፈር ጥቃት እንደተፈፀመባት ከጤና ተቋም በአገኘው ማስረጃ፣ ማረጋገጡን ገልፀዋል። የምርመራ መዝገቡም በተለያዩ ማስረጃዎች በማጠናከር ለአቃቢ ህግ ተልኳል።
አቃቢ ህግም አእምሮአቸውን በሳቱ እና ድርጊቱን መቃወም በማይችሉ ላይ የሚፈፀም የግብረ ስጋ ድፍረት በደል ክስ የመሰረተ መሆኑን ገልፀዋል።ክሱን የተመለከተው የቦረና ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓም በዋለው ችሎት ተከሳሹ ለመልካም ጸባይ ተቃራኒ የሆነ ተግባር በመፈጸሙ 12 ዓመት እስራት እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን ዋና ኢንስፔክተር ዲባባ ዲዳ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል።
አሪፍ መዝናኛ j fm 106.7 📻✨