The Dove

The Dove ማንኛዉንም ማስታወቂያ በነጻ ለአድማጭ እናደርሳለን፡፡

ለሥራ ፈላጊዎች የወጣ ማስታወቂያበተለያዩ የውጭ አገራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ለምትፈልጉ ዜጎች የኢትዮጵያ መንግስት ከአገራቱ ጋር በፈጠረው ስምምነት እድሉ ተመቻችቷል።በዚህም እስከ ሚያዚ...
28/04/2026

ለሥራ ፈላጊዎች የወጣ ማስታወቂያ

በተለያዩ የውጭ አገራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ለምትፈልጉ ዜጎች የኢትዮጵያ መንግስት ከአገራቱ ጋር በፈጠረው ስምምነት እድሉ ተመቻችቷል።

በዚህም እስከ ሚያዚያ 26/2018 ዓ.ም ባሉት የሥራ ቀናት በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እና በሁሉም የአስተዳደሩ ወረዳ የሥራና ክህሎት ማስተባበሪያዎች በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ድንች የት ተገኘ ወደ ኢትዮጵያስ እንዴት ገባ?ድንች ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በደቡብ አሜሪካ አንዲስ ተራሮች አካባቢ ማለትም አሁን ፔሩ እና ቦሊቪያ በሚባሉት አገሮች መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ...
28/04/2026

ድንች የት ተገኘ ወደ ኢትዮጵያስ እንዴት ገባ?
ድንች ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በደቡብ አሜሪካ አንዲስ ተራሮች አካባቢ ማለትም አሁን ፔሩ እና ቦሊቪያ በሚባሉት አገሮች መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ።
የጥንት የአንዲስ ተራራ ነዋሪዎች (ኢንካዎች) ድንችን ማላመድና ማምረት የጀመሩት ከዛሬ 7,000 እስከ 10,000 ዓመታት በፊት እንደነበረ ይገመታል።
በ16ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ የስፔን አሳሾች ከደቡብ አሜሪካ ወደ አውሮፓ ይዘውት ገቡ። መጀመሪያ ላይ አውሮፓውያን እንደ ምግብ ሳይሆን እንደ ጌጥ ተክል ያዩት ነበር።
በኋላ ላይ ግን ድንች በየትኛውም የአየር ሁኔታ በቀላሉ ስለሚበቅልና ከፍተኛ ጉልበት ስለሚሰጥ በዓለም ዙሪያ ተስፋፋ።
ድንች ወደ ኢትዮጵያ የገባው በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ በጀርመናዊው ተጓዥ ዊልሄልም ሺምፐር አማካኝነት እንደሆነ የታሪክ መዛግብት ያመለክታሉ።
ዛሬ ላይ ድንች ከበቆሎ፣ ከስንዴ እና ከሩዝ በመቀጠል በዓለም ላይ በብዛት ጥቅም ላይ የሚውል የሰብል ዓይነት ነው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ድንችን በከፍተኛ መጠን የሚያመርቱ አገራት ቻይና ፥ ሕንድ ፥ ዩክሬን ፥ ሩሲያ እና አሜሪካ ናቸዉ።
በአፍሪካ ደግሞ ግብፅ፣ አልጄሪያ እና ደቡብ አፍሪካ ቀዳሚዎቹ አምራቾች ናቸው።
ኢትዮጵያ አቅሟ ከፍተኛ ሲሆን በተለይ በደጋማው ክፍለ ሀገር፣ አሁንም ምርታማነትን ለማሳደግ በምርጥ ዘር አቅርቦት እና በዘመናዊ የመስኖ አጠቃቀም ላይ ሰፊ ሥራዎችን እየሰራች ትገኛለች።
ድንች በዓለም አቀፍም ሆነ በኢትዮጵያ ለምግብ ዋስትና እና ለጤና እጅግ አስፈላጊ ከሆኑ ሰብሎች አንዱ ነው።
የአመራረት ጥቅሞች፡- ድንች በአነስተኛ መሬት ላይ ከፍተኛ ምርት የሚሰጥ ሰብል በመሆኑ ለገበሬዎችና ለኢኮኖሚው ትልቅ ዕድል ይፈጥራል፡
•ድንች በአጭር ጊዜ (ከ3 እስከ 4 ወራት) ውስጥ የሚደርስ ሰብል በመሆኑ፣ በዓመት ሁለት እና ሦስት ጊዜ ማምረት ይቻላል።
•በተለያዩ የአየር ንብረት እና የአፈር አይነቶች ላይ ሊበቅል ይችላል። በተለይም በደጋማና በወይና ደጋ አካባቢዎች ላይ በከፍተኛ ሁኔታ ይመረታል።
•ከሌሎች ጥራጥሬዎች ጋር ሲነጻጸር፣ ድንች ለሚያመርተው ካሎሪ የሚጠቀመው የውኃ መጠን አነስተኛ ነው።
የምግብ ዋስትና፡- ድንች ረሃብን ለመከላከል እና የተመጣጠነ ምግብን ለማቅረብ ቁልፍ ሚና ይጫወታል፦
•በውስጡ በያዘው ካርቦሃይድሬት ምክንያት ለሰውነት ፈጣን ጉልበት ይሰጣል።
•ሌሎች ሰብሎች (እንደ ስንዴ እና በቆሎ) ሳይደርሱ ድንች ቀድሞ ስለሚደርስ፣ በቤተሰብ ውስጥ ሊከሰት የሚችለውን የምግብ እጥረት ይሞላል። ይህም ድልድይ ነዉ ያስብለዋል፡፡
•ድንች ከመሬት ሳይወጣ ለተወሰነ ጊዜ መቆየት ስለሚችል፣ እንደ "ሕያው መጋዘን" በማገልገል ምግብ በሚያስፈልግበት ጊዜ ብቻ እየተቆፈረ ጥቅም ላይ ይውላል።
የጤና ጥቅሞች ፡- ድንች ከተገቢው አዘገጃጀት ጋር (ሳይጠበስ ወይም ጨው ሳይበዛበት) ሲወሰድ ለጤና በጣም ጠቃሚ ነው፦
•ከፍተኛ የቪታሚን C፣ ቪታሚን B6 እና ፖታስየም ምንጭ ነው። ፖታስየም የልብ ምትን እና የደም ግፊትን ለማስተካከል ይረዳል።
•በውስጡ የሚገኘው ፋይበር ለምግብ መፈጨት ሥርዓት ጤንነት እና ለሆድ ድርቀት መፍትሄ ይሆናል።
•በተፈጥሮው ስብ እና ኮሌስትሮል የሌለው በመሆኑ ለልብ ጤንነት ተመራጭ ነው።
•በውስጡ ያሉት አንቲኦክሲዳንቶች የሰውነት ሴሎች እንዳይጎዱና ለተለያዩ በሽታዎች እንዳይጋለጡ ይከላከላሉ።
ማሳሰቢያ፦ ድንችን በዘይት ከመጥበስ ይልቅ ቀቅሎ ወይም በእንፋሎት አብስሎ መመገብ የጤና ጥቅሙን ሙሉ በሙሉ ለማግኘት ይረዳል።

የ5 ሚሊዮን ብር ታሪካዊ የኤምኤምኤ (MMA) ግጥሚያ - ሁለቱም ተስማምተዋል! የሴዶ እና የጆኒ የኤምኤምኤ (MMA) ፍልሚያ ይፋ ሆኗል! ትልቁ ዜና ደግሞ ሁለቱም ተፋላሚዎች ለግጥሚያው ፍቃደ...
28/04/2026

የ5 ሚሊዮን ብር ታሪካዊ የኤምኤምኤ (MMA) ግጥሚያ - ሁለቱም ተስማምተዋል!
የሴዶ እና የጆኒ የኤምኤምኤ (MMA) ፍልሚያ ይፋ ሆኗል! ትልቁ ዜና ደግሞ ሁለቱም ተፋላሚዎች ለግጥሚያው ፍቃደኛ መሆናቸውን ገልጸው መስማማታቸው ነው።
ይህ በሀገራችን ለሁለተኛ ጊዜ የሚካሄደው የኤምኤምኤ ፍልሚያ፣ በኢትዮጵያ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ታሪክ ከፍተኛውን የገንዘብ ሽልማት የሚያስገኝ ታላቅ የስፖርት ኩነት ሆኖ ተመዝግቧል።
የሽልማት ዝርዝር፦
ለአሸናፊው፦4,000,000 (አራት ሚሊዮን) ብር
ለተሸናፊው፦1,000,000 (አንድ ሚሊዮን) ብር
ይህ ግጥሚያ በኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ መዘጋጀቱ ስፖርቱ በሀገራችን እያደገ መሆኑን የሚያሳይ ሲሆን፤ ወጣቶች ወደ ስፖርቱ እንዲሳቡ እና ፕሮፌሽናል ስፖርተኞች ተገቢውን ክፍያ የሚያገኙበትን መንገድ ለመክፈት ትልቅ ምሳሌ ነው።
የውድድሩ ቀን፦በቀጣዮቹ 4 ወራት ውስጥ
ተፋላሚዎች፦ሴዶ VS ጆኒ (ሁለቱም እሺ ብለዋል)
ፍልሚያው እጅግ ብርቱ እንደሚሆን ይጠበቃል። እናንተስ የዚህ ታሪካዊ ግጥሚያ አሸናፊ ማን ይሆናል ብላችሁ ትገምታላችሁ? ሀሳባችሁን በኮሜንት አጋሩን!
Via Getachew Melese
ጉርሻ page
🌴🌴

28/04/2026

ቢኬጂ የገጣጠማቸው ሀገር አቋራጭ
የሐበሻ ባሶች ለስራ ዝግጁ ናቸው።
ቢኬጂ
የታታሪዋ ኢትዮጵያ ተምሳሌት

ሞት የተፈረደበት ወጣት‼️ተቆጣሽኝ በሚል ምክንያት አክስቱን የገደለው ግለሰብ የሞት ቅጣት ውሳኔ ተላልፎበታል።በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ክልል ልዩ ቦታው ኢካ ሳይት ብሎክ 705 የቤት ቁጥ...
28/04/2026

ሞት የተፈረደበት ወጣት‼️

ተቆጣሽኝ በሚል ምክንያት አክስቱን የገደለው ግለሰብ የሞት ቅጣት ውሳኔ ተላልፎበታል።

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ክልል ልዩ ቦታው ኢካ ሳይት ብሎክ 705 የቤት ቁጥር 59 ውስጥ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ/ም ከምሽቱ 4 ሠዓት ነው ወንጀሉ የተፈፀመው።

በአካባቢው ላይ የሟች ማንነት የማይታወቅና የተወሰነ የሰው ቅሪት አካል በመገኘቱ ከአካባቢው ነዋሪዎች ለፖሊስ ጥቆማ ይደርሳል። ፖሊስም የደረሰውን ጥቆማ መነሻ በማድረግ የሟችን ማንነት ለመለየት እና የወንጀል ፈፃሚውን ማንነት ለመለየት በተደረገው ጥረት በሠዓታት ውስጥ ሟችን መለየት እና በወንጀሉ የተጠረጠረውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ሊያውል መቻሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ም/ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል።

ፖሊስም በተከሳሽ ሻምበል ሙሉጌታ ላይ በተደረገ ምርመራ ሟች ወርቅነሽ ኃይሌ የተባለችው የ36 ዓመት ጎልማሳ ስትሆን በጉምሩክ አስተላላፊነት የስራ መስክ ላይ እየሰራት የነበረች ስትሆን በተገለፀው አካባቢ መኖር ከጀመረች 4 ወራትን አስቆጥራለች።

ሐምሌ 20 ቀን 2016 ዓ/ም የወንድሟ ልጅ የሆነውን ተከሳሽ ሻምበል ሙሉጌታ እሷ ጋር ተቀምጦ የቀን ስራ ለመስራት ከክፍለ ሀገር መምጣቱንና አብረው መኖር መጀመራቸውን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የሰው መግደል ወንጀል ምርመራ መምሪያ ለማወቅ ችሏል።

መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ/ም ከምሸቱ 12 ሰአት አካባቢ ስራ ውላ ወደ ቤቷ ገብታ ከወንድሟ ልጅ ጋር እራት በልተው አመሻሹ ላይ በተፈጠረ አለመግባባት ተቆጣችኝ በሚል ሰበብ አንገቷን በማነቅ መሬት ላይ በመጣል ህይወቷ እንዲያልፍ ካደረገ በኋላ በሽንኩርት መክተፊያ ቢላዋ የተለያዩ የሰውነት ክፍሏን በመቆራረጥና በመለያየት በሦስት ፊስታል ነጣጥሎ በማሰር ጨለማን ተገን በማድረግና ማንም እንደማያየው በማረጋገጡ አንዱን ፌስታል መፀዳጃ ቤት ሁለተኛውን ደግሞ ለግንባታ የተቆፈረ ቦታ ላይ በመጣል አፈር በማልበስና ሦስተኛውን ፌስታል ግንብ ስር ሊጥልም ችሏል፡፡

ፖሊስ የተለያዩ ማስረጃዎችን በመሰብሰብ ወንጀሉን ፈፅሟል ተብሎ የተጠረጠረውን ግለሰብ በመያዝ ቅሪተ አካሎችን የጣለበት ቦታ መርቶ እንዲያሳይ አድርጓል፡፡

የሟችን አስክሬን በመሠብሰብ ለቤተሰብ በመስጠት በተከሳሹ ላይ የምርመራ ስራውን በሰው እና በሰነድ ማስረጃ ያጠናቀቀው ፖሊስ የተጠናቀቀውን የምርመራ መዝገብ ለዐ/ህግ በማቅረብና ክስ በማስመስረት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሁለተኛ ወንጀል ችሎት ተከሳሽ ሻምበል ሙሉጌታን ጥፋተኛ ሆኖ በማግኘቱ የሞት ፍርድ ውሳኔ ወስኖበታል፡፡

Via- Addisababa Police

27/04/2026

21ኛ የልደት በአል

27/04/2026
በጣም የገረሙኝ 5 ነገሮች1ኛ የጦር ትግል ሀገር ይጎዳል በነጻ ሀሳብ ታገሉ ይሉና በዘፈን ሀሳቡን ሲገልጽ እንደ ትልቅ ሀገር አጥፊ መቁጠር2ኛ አንድ አዝማሪ አጀንዳችን አይደለም ይሉና በቀጥታ...
27/04/2026

በጣም የገረሙኝ 5 ነገሮች
1ኛ የጦር ትግል ሀገር ይጎዳል በነጻ ሀሳብ ታገሉ ይሉና በዘፈን ሀሳቡን ሲገልጽ እንደ ትልቅ ሀገር አጥፊ መቁጠር
2ኛ አንድ አዝማሪ አጀንዳችን አይደለም ይሉና በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የለት ከለት አጀንዳቸው ሲያደርጉት መታየት
3ኛ ማንንም አንፈራ ይሉና ቴዲን ብቻ ሳይሆን ሙዚቃውን የሚያዳምጡትንም ፍርሀት በተሞላበት ጥላቻ እያፈሱ ማሰር
4ኛ ቴዲ ሀሳቡን ከገለጸ በኋላ ትዝብት በሚመስል መልኩ በሱ ዙሪያ ለሚሰነዘሩ ስድብ አዘል ሀሳቦችና ምንም አይነት የሞ #ራል ልዕ*ልና በሌላቸው ዘፋኞች የመልስ ምት ላይ ዝምታን በመምረጥ እንደንስር ከፍታውን መቀጠሉ
4ኛ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ዘፈኑን በደንብ ካደመጡ በኋላ የዘፈን መንፈስ የተወጋ ይሁን ሲሉ መታየት። ለማየታቸውም ማሳያው አልበሞችን በመምረጥ ለምሳሌ የዳስ ጣል መንፈስ የተወጋ ይሁን ሲሉ መታየት።
Mikias Abate

“ እሺ" ተብሏል እንኳን ደስ አለህ ያሬዶ! 💍❤️ተወዳጅ ድምፃዊ ያሬድ ነጉ የሕይወቱን አጋር ለመምረጥ ሽምግልና ልኮ በስኬት "እሺ" ተብሏል። በሙዚቃው ሁሌም የሚያስደስተን ያሬዶ፣ አሁን ደግ...
27/04/2026

“ እሺ" ተብሏል እንኳን ደስ አለህ ያሬዶ! 💍❤️
ተወዳጅ ድምፃዊ ያሬድ ነጉ የሕይወቱን አጋር ለመምረጥ ሽምግልና ልኮ በስኬት "እሺ" ተብሏል።
በሙዚቃው ሁሌም የሚያስደስተን ያሬዶ፣ አሁን ደግሞ የራሱን የፍቅር ታሪክ በአዲስ ምዕራፍ ሊጀምር ነው።
ለሁለታችሁም እጅግ የሚያምር፣ የሰላምና የደስታ የፍቅር ዘመን ይሁንላችሁ! አዲሱ ሕይወትህ እንደ ዜማዎችህ ያማረና የተባረከ ይሁን።

" አካባቢው ላይ ያለውን ማህበረሰብ እዚሁ እናስገባለን። ... ያልተዘጋጀንበትን ቃል አንገባም " - ከንቲባ አዳነች አቤቤየአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ መርካቶ አካባቢ የሚገኘው በተለምዶ " ቅ...
27/04/2026

" አካባቢው ላይ ያለውን ማህበረሰብ እዚሁ እናስገባለን። ... ያልተዘጋጀንበትን ቃል አንገባም " - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ መርካቶ አካባቢ የሚገኘው በተለምዶ " ቅጠል ተራ " እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ዘመናዊ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ አስጀመሩ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፤ አካባቢው የተጨናነቀና ምቹ ያልሆነ በመሆኑ እሳት አደጋ ሲከሰት እንኳን ለመከላከል አዳጋች ሆኖ ቆይቷል ብለዋል።

ከዚህ ቀደም ከፍተኛ የእሳት አደጋ ተከስቶ የመኪና መግቢያ ጠፍቶ እሳቱን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ፈተና አጋጥሞ እንደነበር አስታውሰዋል።

10 ሺህ ካሬ ላይ ያረፈው አዲስ የሚገነባው መኖሪያ መንደር ምቹ ፤ ህጻናት እና ወጣቶች የሚጫወቱባቸው መሰረተ ልማቶች ጭምር የሚገነባበት የአካባቢውን ገጽታ ሙሉ በሙሉ የሚቀየር እንደሆነ ገልጸዋል።

ከንቲባ አዳነች የሚገነባው 9 ህንጻ መሆኑንና ከአካባቢው የተነሱ ነዋሪዎች እዛው ወደ ሚነገቡት መኖሪያ ቤቶች እንደሚገቡ ይፋ አድርገዋል።

" 9 ህንጻ ባለ ስምንት ወለል ነው። ከ500 በላይ ቤቶች ይገነባል። ሲገነባ ከዚህ የምትነሱትን ብቻ አይደለም የሚይዘው በርካታ ህዝብ ይይዛል። አካባቢው ላይ ያለውን ማህበረሰብ እዚሁ እናስገባለን። ስናስገባ ሰፋ ያለ አካባቢ ይቀየራል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ከዚህ የተነሳችሁትን የቅድሚያ ቅድሚያ ሰጥተን እዛም ሳትደርሱ ወደ ቤታችሁ መግባት እንድትችሉ እንጥራለን " ብለዋል።

" እናተ የነበራችሁበት አካባቢ ለብዙዎች ተመልሶ በረከት እና መትፈር ይሆናል " ያሉት ከንቲባ አዳነች መንገድ ዳር ያሉት ህንጻዎች የንግድ ቤት ያላቸው እንደሆኑና ተጨማሪ የንግድ ህንጻዎች እንደሚኖሩ አሳውቀዋል።

" በደምብ ያላሰብንበትን ያልተዘጋጀንበትን ቃል አንገባም ፤ ተዘጋጅተን ነው ቃል የምንገባላችሁ " ብለዋል።

የቤቶቹ ግንባታ እስከመጪው አዲስ አመት ድረስ እንደሚጠናቀቅ የገለጹ ሲሆን " አዲሱ አመት በዚህ አካባቢ አዲስ መንፈስ ፣ አዲስ አኗኗር፣ ዘመናዊ አኗኗር ለህጻናት፣ ለወጣቶች ለአረጋውያን የሚመች መንደር ይኖራል " ሲሉ ቃል ገብተዋል።

አዲስ አበባ
ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ/ም

27/04/2026

ሀብቴ ሩብ ቢልየን ብር ይሆናል...ከተማ አይመቸኝም ሚሊየነሩ ገበሬ እስክንድር ዮሴፍ part 8

"MMA Fight ከጆኒ ጋር ለማድረግ ተዘጋጅቻለሁ።" ቲክቶከሩ ሴዶ ማርሻልአስተያየታችሁ ጨዋነት እንዲኖረዉ እናሳስባለን(ከአክብሮት ጋር)
27/04/2026

"MMA Fight ከጆኒ ጋር ለማድረግ ተዘጋጅቻለሁ።" ቲክቶከሩ ሴዶ ማርሻል
አስተያየታችሁ ጨዋነት እንዲኖረዉ እናሳስባለን(ከአክብሮት ጋር)

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when The Dove posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to The Dove:

Share