Tena adam Promotion/ጤና አዳም ፕሮሞሽን

Tena adam Promotion/ጤና አዳም ፕሮሞሽን ጤና አዳም ፤ ጤና አዳም
ደስተኛ ጤናማ የአኗኗር ዘዴ ላይ ያተኮረ አስተማሪና አዝናኝ ፕሮግራም
Happy Healthy Life Style

የኩላሊትህ ጤና ያሳስብሃል? ሐብሐብናሴሊሪን በአንድ ላይ ተመገብ!፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ሐብሐብና ሴሊሪ  በፈሳሽ የበለጸጉ በመሆናቸው ሰውነትን ለማደስና አጠቃላይ የኩላሊትን...
10/06/2026

የኩላሊትህ ጤና ያሳስብሃል? ሐብሐብና
ሴሊሪን በአንድ ላይ ተመገብ!
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ሐብሐብና ሴሊሪ በፈሳሽ የበለጸጉ በመሆናቸው ሰውነትን ለማደስና አጠቃላይ የኩላሊትን ጤና ለመደገፍ የሚረዱ ምርጥ ጥምረቶች ናቸው። ሐብሐብ በተፈጥሮው ከፍተኛ የውሃ ይዘት ያለው እና እንደ ሊኮፔን ያሉ አንቲኦክሲዳንቶችን የያዘ ሲሆን፣ ሴሊሪ ደግሞ ተጨማሪ ፈሳሽና ፖታሲየምን ይገኝበታል። ፖታሲየም በሰውነታችን ውስጥ ያለውን የፈሳሽ መጠን በትክክል ለመቆጣጠር የሚረዳ ወሳኝ ማዕድን ነው።

በቂ ፈሳሽ በሰውነታችን ውስጥ መኖሩ ኩላሊቶቻችን ቆሻሻዎችን በቀላሉ እንዲያጣሩና መደበኛ የሰውነት ተግባራትን በተገቢው ሁኔታ እንዲያከናውኑ ይረዳል። ይህ ተስማሚና ጭማቂ ጥምረት ጠቃሚ የሆኑ ንጥረ ነገሮችን እያገኙ የውሃ ፍላጎትዎን በቀላሉ ለማሟላት የሚረዳ ድንቅ መንገድ ነው።

እንደ ሐብሐብና ሴሊሪ ያሉ በፈሳሽ የበለጸጉ ፍራፍሬዎችንና አትክልቶችን በዕለታዊ የምግብ ዝርዝርዎ ውስጥ ማካተት፣ ጤናማ የሰውነት ፈሳሽ መጠንን ለመጠበቅና የኩላሊት ሥራን ለመደገፍ የሚረዳ ቀላል ግን በጣም ውጤታማ እርምጃ ነው።

አዲስ አድማስ

ያለመውለድ ችግር (መካንነት) 10 ዋና ዋና ምክንያቶች ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ጥንዶች ጋብቻ ከፈፀሙ በኋላ በቀጣዩ የህይወት ምዕራፍቸው የሚጠብቁት ነገር  ልጅ መውለድ ...
10/06/2026

ያለመውለድ ችግር (መካንነት) 10 ዋና ዋና ምክንያቶች
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ጥንዶች ጋብቻ ከፈፀሙ በኋላ በቀጣዩ የህይወት ምዕራፍቸው የሚጠብቁት ነገር ልጅ መውለድ ነው። አንድ ሴት ምንም የመውለድ ችግር ሳይኖርባት እና የወሊድ መከላከያ ሳትጠቀም በአንድ ወር ውስጥ የማርገዝ እድሏ 20% ሲሆን 6 ወር ውስጥ 60% እንዲሁም በ1 ዓመት 85% ነው። ለሁለት አመት ቢሞክሩ ደግሞ 95% የማርገዝ እድል አላቸው።

15% የሚሆኑ ጥንዶት በአንድ አመት ውስጥ ምንም አይነት የወሊድ መከላከያ ሳይጠቀሙ ቋሚ የግብረስጋ ግንኙነት እያደረጉ የማርገዝ ችግር ያጋጥማቸዋል። ይህም መካንነት ወይም ያለመውለድ ችግር አጋጥሟቸዋል ተብሎ ህክምና ይጀመርላቸዋል።

የሴቷ እድሜ ከ35 አመት በላይ ከሆነ ለ6ወር ሙከራ አድርጋ እርግዝና ካልተፈጠረ የመካንነት ህክምና መጀመር አለባት።

መውለድ ያለመቻል እጅግ በርካታ ምክንያቶች ሲኖሩት አንዳንዶቹ ወደ 20% የሚሆኑት ይህ ነው የሚባል ምክንያት የላቸውም።

ያለመውለድ ችግር (መካንነት) ዋናዋናዎቹ ምክንያቶች እነሆ

1. ከወንድ በኩል የሚኖር መካንነት (male factor infertility)

እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ መሰረት 20% የሚሆነው ያለመውለድ ችግር (መካንነት) ከወንድ በኩል የሚኖር ነው።ይህም በጭንቅላት ውስጥ የሚመረት ሆርምሞን ማነስ, በዘር ፍሬ ላይ የሚያጋጥም ሰፐርም የማምረት ችግር (primary testicular defect in spermatogenesis), የወንድ የዘር ትቦ መዘጋት, እንዲሁም ምክንያቱ የማይታወቅ የወንድ መካንነት (idiopathic male infertility) ዋና ዋናዎቹ ናቸው።

ከ70-80% የሚሆነው በወንዶች በኩል የሚያጋጥም መካንነት በዘር ፍሬ (te**es) በተለያዩ ምክንያቶች ዘር ያለማምረት ችግር የሚመጣ ነው። ይህም በዘር (genetics) ፣ በኢንፌክሽን ፣ በአደጋ፣ ጨረር መጋለጥ፣ ለሙቀት መጋለጥ እንዲሁም የሆርሞን ማነስ ምክንያት ሊሆን ይችላል።

2. በሴቶች ላይ እንቁላል የመለቀቅ ችግር (ovulatory dysfunction)

25% የሚሆነው ያለመውለድ ችግር (መካንነት) ምክንያት የእንቁላል ያለመለቀቅ ችግር ነው። አንዲት ሴት ስትወለድ ከ1-2 ሚሊየን የሚጠጉ እንቁላሎች በኦቫሪ ውስጥ ይኖራሉ። አነዚህ እንቁላሎች እድሜዋ አየጨመረ ሲሄድ እየቀነሱ ይመጣሉ። እርግዝና እንዲፈጠር እንቁላል ከኦቫሪ ወደ ማህፀን ግድግዳ መለቀቅ አለበት ይህ የመለቀቅ ሂደት በተለያየ ሆርሞኖች ቁጥጥር ስር የወደቁ ናቸው። የእነዚህ ሆርሞኖች መዛባት እንቁላል እንዳይለቀቅ ሊያደርጉ ይችላሉ።
PCOS ፣ ከአንጎል የሚመነጭ ሆርሞን ማነስ፣የፕሮላክቲን መብዛት ፣ የታይሮይድ ሆርሞን ማነስ/መብዛት እንደምክንያትነት ይጠቀሳሉ።

3. የማህፀን ቱቦ መዘጋት

በግራና በቀኝ በኩል የሚገኙ እንቁላል አስተላላፊ ትቦዎች በተለያየ ምክንያት ሊዘጉ ይችላሉ። በሰርጀሪ፣ በኢንፌክሽን፣ ከማህፀን ውጭ በሚያጋጥም እርግዝና እንዲሁም በሆድ እቃ ውስጥ በሚያጋጥም ጠባሳና መጣበቅ ሊዘጋ ይችላል።

4. በማህፀን ግድግዳ ላይ የሚያድግ እጢ

በማህፀን ግድግዳ ላይ የሚፈጠር እጢ እንቁላልና ስፐርም ሴል እንዳይገናኙ እንዲሁም እርግዝና ከተፈጠረ በኋላም ምቹ ሁኔታ እንዳይኖር ሊያደርጉ ይችላሉ።

5. የማህፀን አፈጣጠር ችግር

በተፈጥሮ ለሁለት የተከፈለ ማህፀን (septated uterus) ተደጋጋሚ ውርጃ እንዲኖር እንዲሁም ምንም ማህፀን ያለመፈጠር ችግር የመካንነት ችግር ሊያመጡ ይችላሉ።

6. ኢንዶሜትሪዮሲስ (endometriosis)

ጠባሳና መጣበቅን በመፍጠር የማህፀን ትቦ እንዲዘጋ እንዲሁም በኦቫሪ ውስጥ እጢ (endometrioma) በመፈጠር የእንቁላል ማምረት ሂደትን በማወክ መካንነትን ሊያመጣ ይችላል።

7. የዘረ መል (chromosome) ችግር

Turner syndrome, down syndrome, Kallman syndrome, የተባሉ የዘረመል ችግሮች ያለመውለድ ችግር ያመጣሉ።

8. ምክንያቱ የማይታወቅ (unexplained infertility)

ብዙ ምርመራዎች ተደርገውም ምንም ምክንያት ላይገኝ ይችላል።ይህም 20% የሚሆኑት ያለመውለድ ችግር ያለባቸው ጥንዶች ላይ ያጋጥማል።

9. የግብረ ስጋ ግንኙነት አደራረግ ችግር

እርግዝና እንዲፈጠር እርግዝና የሚፈጠርበትን የወር አበባ ኡደት ጊዜ ጠብቆ የማድረግ ችግር፣ ማለስለሻ ጄሎችን መጠቀም ያለማርገዝ እድልን ይጨምራሉ። እንቁላል የሚለቀቅበትን ወቅት ጠብቆ (Fertile period) ተደጋጋሚ ግንኙነት ማድረግ የማርገዝ እድልን ይጨምራል።

10. እድሜና የአኗኗር ሁኔታ

የሴቶች እድሜ ሲጨምር የእንቁላል መጠን እየቀነሰ ይሄዳል። በተጨማሪም ሲጋራ ማጨስ ፣ ለተለያዪ ኬሚካሎች መጋለጥ፣ ለጨረር መጋለጥ፣ የክብደት መጨመር፣ ጭንቀት፣ ከፍተኛ መጠን ያለው አልኮል መውሰድ ለመካንነት ያጋልጣል።

ዶ/ር በላይ አለሙ የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት

Big shout out to my new rising fans! Yewubnesh Berhanemeskel
05/06/2026

Big shout out to my new rising fans! Yewubnesh Berhanemeskel

67 በመቶው አምራች ኃይል በልጅነቱ የቀንጨረ እንደነበረ ተገለፀ :- የኢትዮጵያን ትውልድ ይታደጋል ተብሎ የቀረበው አዲስ ረቂቅ አዋጅ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ በሀገሪቱ "...
05/06/2026

67 በመቶው አምራች ኃይል በልጅነቱ የቀንጨረ እንደነበረ ተገለፀ :- የኢትዮጵያን ትውልድ ይታደጋል ተብሎ የቀረበው አዲስ ረቂቅ አዋጅ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

በሀገሪቱ "አሳሳቢ" ደረጃ ላይ ያለውን የመቀንጨር ችግር ለመፍታት የትምህርት ሚኒስቴር ከቅድመ አንደኛ እስከ መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ ተማሪዎች የተመጣጠነ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም እንዲተገብር ግዴታ የሚጥል ረቂቅ አዋጅ ለቋሚ ኮሚቴ ተመራ፡፡

ረቂቅ አዋጁ በሀገሪቱ "አሳሳቢ" ደረጃ ላይ ያለውን የመቀንጨር ችግር ለመፍታት 13 ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ላይ ከፍተኛ ግዴታ የሚጥል ነው፡፡

ለረቂቅ አዋጁ መተግበር ማንኛውም ሰው የመተባበርን ግዴታ እንዳለበት በረቂቁ ተደንግጓል፡፡

የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ትናንት ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው ለጤና፣ ማህበራዊ ልማት ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመራው የምግብ ስርዓት እና የስርዓት ምግብ ረቂቅ አዋጅ ይሰኛል።

ረቂቁ የቃላቱን ትርጉም ሲያስረዳ የምግብ ስርዓት ማለት አካባቢን፣ ግብዓትን፣ አመራረትን፣ ማቀነባበርን ብክነት እና አወጋገድን አንድ ላይ የያዘ ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊና አካባቢያዊ ውጤቶን አጣምሮ ያያዘ ነው ይላል።

ስርዓተ ምግብ ደግሞ አገልግሎት እና ተግባራትን በመተግበር ማህበረሰብ ከስርዓተ ምግብ ችግር ነጻ እንዲሆን የሚስችል ስርዓት እንደሆነ ዘርዝሯል።

የረቂቁ ማብራሪያ መግቢያ ላይ መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያ በማንኛውም ጊዜ እና ቦታ የምግብ ዋስትና እንዲኖራቸው በበቂ ሁኔታ ጥራት ያለው ምግብ ማግኘታቸውን የማረጋገጥ ህገ መንግስታዊ ሃላፊነት እንዳለበት አስረድቷል።

ኢትዮጵያ መካከለኛ ገቢ አካላቸው ሀገራት ተርታ ለመሰለፍ እየሰራች እንዳለ የዘረዘረው ረቂቁ ይህን ግብ ማሳካት የሚቻለው የተስተካከለ እና የተመጣጠነ ምግብ ማግኘት ሲቻል ነው ብሏል።

በ2018 ዓ.ም ይፋ በተደረገው የጤናና የስነ ህዝብ ዳሰሳ ጥናት መሰረት በኢትዮጵያ ያሉት 40 በመቶ (6.6ሚሊዮን ) የሚሆኑት ህጻናት የቀነጨሩ መሆናቸውን ማብራሪያው አካቷል።

በተጨማሪም አሁን በአዋቂነት እድሜ ላይ ያለው አምራች ሃይል የሚገኘው 67 በመቶ የሚሆነው ከአምስት ዓመት በታች እያለ የቀነጨረ ነበር ይላል የምግብ ስርዓት እና የስርዓት ምግብ ረቂቅ አዋጅ ማብራሪያ መግቢያ።

በሀገሪቱ ከመቀንጨር እና ስርዓት ምግብ መዛባት ጋር የተያያዙ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታ መጠን መጨመር በጤና፣ ትምህርት ፣ በአካባቢው እና በምርታማነት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩም በረቂቁ ተመላክቷል።

ይህን ችግር ለመቅረፍ በረቂቅ አዋጁ ክፍል አራት ስር ለ13 ሚኒስቴር መስሪያቤቶች እና ለአንድ ኮሚሽን መስሪያ ቤት ከፍተኛ ሃላፊነት ተሰጥቷል።

በዚህም መሰረት የትምህርት ሚኒስቴር፤ ለሀገር በቀል ምርቶች ትኩረት በመስጠት ሁሉም የመንግስት የቅደመ አንደኛ፣ የመጀመሪያ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች የተመጣጠነ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም እንዲተገብር ያዝዛል።

በተጨማሪም የምግብ ስርዓት እና የስርዓተ ምግብ ስርዓትን በትምህርት ውስጥ ያካትታል፣ ትምህርት ቤቶች በንጥረ ምግብ የበለፀጉ ምርቶች እንዲመረቱ ያደርጋል እና በትምህርት ቤቶቹ በንጥረ ምግብ የበለጸጉ ምግቦችን ዝርዝርን ያዘጋጃል።

የጤና ሚኒስቴር ደግሞ የስርዓተ ምግብ ግብዓቶች በሀገር ውስጥ እንዲመረቱ ከውጪ ባለሃብቶች ጋር ይመክራል፤ጥራቱን ይቆጣጠራል ፣ ስረዓተ ምግብ በትምህር ስርዓቱ ውስጥ እንዲካተት እንዲደግፍ፣ የቪታሚን ኤ(A) እንክብል እና ፎሊክ አሲድ አገልገሎት እንዲያገኙ ያደርጋል፣ መምህራን እና ተማሪዎች ወቅታዊ የጤና ምርመራ እንዲያገኙ የማድረግን ግዴታ ይጥላል።

በንጥረ ነገር የበለጸጉ ምርቶች አንዲመረቱ የግብርና ሚኒስቴር፣ በምግብ ሴከተር የተሰማሩ አነስተኛ የንግድ ማጠናከር ለንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ በፋብሪካ ደረጃ የሚመረቱት የምግብ አይነቶችን ጥራት መቆጣጠር ለኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ፣ ለትምህርት ቤቶቹ ንጹሁ ውሃ ማቅረብን ደግሞ ለውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ረቂቁ ይሰጣል።

ለትምህርት ቤት ምገባ የፋይናንስ ስርዓት እንዲዘረጋ፣ የትምህርት ቤት ምገባ የሀብት ፍላጎትን የሀገሪቱ የበጀት አዋጅ አካል እንዲደርግ ፣ ለትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር የሚያስፈልገውን የበጀት ርዕስ እንዲኖረው የማድረግ ሃላፊነትን ደግሞ ለገንዘብ ሚኒስቴር ሰጥቷል፡፡

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ጨምሮ ሌሎችም ተቋማት ሃላፊነት የተሰጣቸው ሲሆን የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽንም ተካቷል።

ረቂቅ አዋጁ በክፍል 20 ትብብርን በተመለከተም ለአዋጁ አፈጻጸም ማንኛውም ሰው የመተባበር ግዴታ አለበት ይላል።

Via:- ሸገር Fm

ከ50 በላይ የልብ ሕክምና ባለሞያዎችን የያዘ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ከ50 በላይ የልብ ሕክምና በጎ ፈቃደኛ ባለሞያዎችን የያዘ የሕክምና ...
04/06/2026

ከ50 በላይ የልብ ሕክምና ባለሞያዎችን የያዘ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ከ50 በላይ የልብ ሕክምና በጎ ፈቃደኛ ባለሞያዎችን የያዘ የሕክምና ቡድን ከአንድ ወር በኋላ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጣ ተነግሯል። ከዚህ ቀደም በተለያዩ ጊዜያት አራት መሰል ቡድኖች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የሕክምና አገልግሎት እንዲሰጡ ያደረገው 'ኸርት አታክ ኢትዮጵያ' የተሰኘው ግብረሰናይ ድርጅት፤ በቀጣዩ ሰኔ ወር መጨረሻ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣው ቡድን የልብ ሕክምና ለማግኘት ወረፋ እየተጠባበቁ ለሚገኙ ሕጻናት እና አዋቂዎችን ሕክምና እንደሚሰጥ ገልጿል።

የሕክምና በጎ ፈቃደኛ ባለሞያዎች ቡድኑ የልብ ስፔሻሊስት ሃኪሞች እና ነርሶች፣ እንዲሁም ሌሎች ባለሞያዎችን ያካተተ መሆኑ ተነግሯል። የሕክምና በጎ ፈቃደኛ ባለሞያዎቹ ከህንድ፣ ካናዳ፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ሩዋንዳ እና ቦትስዋና የተወጣጡ መሆናቸውንም የኸርት አታክ ኢትዮጵያ መሥራች ዶክተር ተስፋዬ ተሊላ ገልጸዋል።

ኸርት አታክ ኢትዮጵያ በየጊዜው ተመሳሳይ ሥራዎችን በማከናወን የልብ ሕመም ህክምና ለማግኘት ወረፋ እየተጠባበቁ ለሚገኙ ሕጻናት ሕክምና መስጠቱን እንደሚቀጥልም ዶክተር ተስፋዬ አረጋግጠዋል ሲል ሀገሬ ቴሌቪዥን ነው።

ያለ ማዘዣ አንቲባዮቲክስ መሸጥ ሙሉ በሙሉ ተከለከለየኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ከግንቦት ወር 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተፈጻሚ የሚሆን አዲስ የመድኃኒት አጠቃቀም ቁጥጥር መመሪያ (ቁጥር...
04/06/2026

ያለ ማዘዣ አንቲባዮቲክስ መሸጥ ሙሉ በሙሉ ተከለከለ

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ከግንቦት ወር 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተፈጻሚ የሚሆን አዲስ የመድኃኒት አጠቃቀም ቁጥጥር መመሪያ (ቁጥር 1138/2026) አውጥቷል። ይህ መመሪያ ፋርማሲዎች ያለ ሐኪም ትክክለኛ ማዘዣ ማንኛውንም የፀረ-ተህዋሲያን (አንቲባዮቲክስ) እና በሕግ የተገደቡ መድኃኒቶችን ለደንበኞች እንዳይሸጡ በጥብቅ ይከለክላል። በተጨማሪም ሆስፒታሎች የክትትል ኮሚቴ እንዲያቋቁሙ የሚያስገድድ ሲሆን፣ ሐኪሞች በአንድ ወረቀት ላይ ከሦስት መድኃኒት በላይ እንዳያዙና የአንቲባዮቲክስ ማዘዣዎችም ከ7 ቀናት በላይ እንዳያገለግሉ ገደብ ጥሏል።

ይህ አሠራር ዜጎች ያለ ሐኪም ትዕዛዝ መድኃኒት በመውሰድ ለከፍተኛ የመድኃኒት መላመድ (Drug Resistance) አደጋ እንዳይጋለጡና ትክክለኛውን ሕክምና በትክክለኛው መጠን እንዲያገኙ ለማስቻል የተዘረጋ ነው። ፋርማሲስቶች መድኃኒት ከመስጠታቸው በፊት ጥራቱንና የአገልግሎት ማጠናቀቂያ ቀኑን የመፈተሽ እንዲሁም ለታካሚው በቂ የምክር አገልግሎት የመስጠት ግዴታ አለባቸው። የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ ይህንን አዲስ ሕግ በሚጥሱ ባለሙያዎችና ተቋማት ላይ እስከ ሥራ ፈቃድ መሰረዝ የሚደርስ ጥብቅ ቅጣት እንደሚጣል አስጠንቅቀዋል።

የ2026 ዓለም ዋንጫ አዳዲስ ሕጎች    የ5 ሰከንድ ገደብ፦ ተጫዋቾች ከሜዳ ውጭ የሆነን ኳስ በእጅ ለመወርወር እና የግብ ጠባቂ ምት  ለመምታት 5 ሰከንድ ብቻ ነው የሚሰጣቸው።    አፍን ...
04/06/2026

የ2026 ዓለም ዋንጫ አዳዲስ ሕጎች

የ5 ሰከንድ ገደብ፦ ተጫዋቾች ከሜዳ ውጭ የሆነን ኳስ በእጅ ለመወርወር እና የግብ ጠባቂ ምት ለመምታት 5 ሰከንድ ብቻ ነው የሚሰጣቸው።

አፍን የመሸፈን ክልከላ፦ ከተጫዋቾች ወይም ከዳኞች ጋር በሚፈጠር ጭቅጭቅ ወቅት አፋቸውን በእጃቸው የሚሸፍኑ ተጫዋቾች በቀጥታ የቀይ ካርድ ቅጣት ይገጥማቸዋል።

ሜዳን ጥሎ የመውጣት ቅጣት፦ ማንኛውም ብሔራዊ ቡድን ጨዋታውን ተቃውሞ ሜዳውን ጥሎ ከወጣ ከባድ ቅጣት እና ውሳኔ ይተላለፍበታል።

የግዴታ የህክምና ጊዜ፦ አንድ ተጫዋች ተጎድቶ ሕክምና ካገኘ በኋላ ጨዋታው ሳይቋረጥ ከሜዳ ውጭ ለ1 ደቂቃ ቆይቶ መግባት አለበት።

የቫር (VAR) ጣልቃ ገብነት፦ ኳስ በቆመበት ሰዓት (የማዕዘን፣ የቅጣት ምት ከመመታቱ በፊት) የሚሰሩ ጥፋቶችን የቪዲዮ ዳኛው (VAR) አይቶ ቅጣት የመስጠት ሥልጣን ይኖረዋል።

የቫር (VAR) ምርመራ መስፋፋት፦ የቪዲዮ ዳኛው (VAR) በስህተት የተሰጡ የማዕዘን ምቶችን እና በስህተት የተሰጡ ሁለተኛ ቢጫ ካርዶችን አይቶ የመሻር መብት አለው።

ምንጭ አዲስ አድማስ

ጎግል 32 ሚ. ላብራቶሪ ውስጥ ያደጉ የወባ ትንኞችን ሊለቅ ነው፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የቴክኖሎጂው ግዙፍ ኩባንያ ጎግል በወባ ትንኝ አማካኝነት የሚመጡ በሽታዎችን ለመቀነስ 3...
04/06/2026

ጎግል 32 ሚ. ላብራቶሪ ውስጥ
ያደጉ የወባ ትንኞችን ሊለቅ ነው
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የቴክኖሎጂው ግዙፍ ኩባንያ ጎግል በወባ ትንኝ አማካኝነት የሚመጡ በሽታዎችን ለመቀነስ 32 ሚሊዮን በላብራቶሪ ውስጥ ያደጉ ተባዕት ጾታ ትንኞችን በፍሎሪዳና በካሊፎርኒያ ግዛቶች ውስጥ ለመልቀቅ ፍቃድ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል። ይህ ፕሮጀክት እ.ኤ.አ. በ2014 የተጀመረውና በሽታ አምጪ የትንኝ ዝርያዎችን ለመቆጣጠር አዳዲስ መንገዶችን የሚያጠናው የጎግል "ዲበግ" የተባለ ተነሳሽነት አካል ነው። ኩባንያው በየዓመቱ 16 ሚሊዮን ትንኞችን ለመልቀቅ ያቀደ ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ፕሮፖዛሉ በአሜሪካ የአካባቢ ጥበቃ ኤጀንሲ እየተገመገመ ይገኛል።

እነዚህ ወንድ ትንኞች "ዎልባቺያ" በተባለ የባክቴሪያ ዝርያ የተበከሉ በመሆናቸው፥ ከተፈጥሮአዊ ሴት ትንኞች ጋር በሚጣመሩበት ጊዜ እንቁላሎቹ ሳይፈልቁ እንዲቀሩ ያደርጋሉ፤ ይህም የትንኞችን ቁጥር በሂደት በእጅጉ ይቀንሰዋል። በላብራቶሪ የተዘጋጁት ወንድ ትንኞች ብቻ ሲሆኑ፥ ወንድ ትንኞች ደግሞ ሰውን ፈጽሞ እንደማይነክሱ ታውቋል። ይህ አዲስ የሳይንስ አካሄድ ስኬታማ ከሆነ በትንኞች አማካኝነት የሚመጡ ገዳይ በሽታዎችን ለመከላከል ትልቅ እፎይታን ይዞ ይመጣል ተብሎ ይገመታል።

የዶናልድ ትራምፕ የጤና ምርመራ ውጤት ይፋ ሆነ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ​የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዎልተር ሪድ ወታደራዊ የህክምና ማዕከል ያደረጉትን ዝ...
31/05/2026

የዶናልድ ትራምፕ የጤና ምርመራ ውጤት ይፋ ሆነ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

​የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዎልተር ሪድ ወታደራዊ የህክምና ማዕከል ያደረጉትን ዝርዝር የጤና ምርመራ ተከትሎ፣ የግል ሃኪማቸው ሙሉ ጤንነት ላይ እንደሚገኙና ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ብቁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

​በ22 ስፔሻሊስቶች የተከናወነው ይህ ምርመራ እንደሚያሳየው፣ ትራምፕ 108 ኪሎ ግራም የሚመዝኑ ሲሆን የሰውነት ብዛት ማውጫቸው (BMI) 29.7 ደርሷል።

ይህም ከመጠን ያለፈ ውፍረት ጠርዝ ላይ የሚያስቀምጣቸው በመሆኑ ሃኪሞች የአመጋገብና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማሻሻያ ጠቁመዋል።

​በእጆቻቸው ላይ የታዩ የመሰማበር ምልክቶች በአስፒሪን አጠቃቀም ምክንያት የመጡ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፣ የልብ፣ የሳንባ እና የነርቭ ምርመራዎቻቸው ግን መደበኛ ናቸው።

በተጨማሪም በትራምፕ ላይ የተደረገው የእውቀት ማስተዋል (cognitive) ፈተና ሙሉ ውጤት ያስመዘገበ ሲሆን፣ የኮሌስትሮል መጠናቸውም መሻሻል አሳይቷል።

እንደ ፊደል ፖስት ዘገባ እድሜያቸው ወደ 80 እየተቃረበ የመጣው ትራምፕ፣ የታሪክ አንጋፋው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ናቸው ።

ምንጭ:- ጌጡ ተመስገን)

 " ወንድ አይደለህ ? "በማህበረሰባችን ለወንድነት ከሰጠነው መለኪያዎች መካከል የማያለቅስ፣ ስሜት አልባ፣ ምንም እንኳን ጫና ቢደርስበትም ወንድ ስለሆነ ብቻ ዋጥ እና ቻል አድርጎ እዲያልፍ ...
30/05/2026



" ወንድ አይደለህ ? "

በማህበረሰባችን ለወንድነት ከሰጠነው መለኪያዎች መካከል የማያለቅስ፣ ስሜት አልባ፣ ምንም እንኳን ጫና ቢደርስበትም ወንድ ስለሆነ ብቻ ዋጥ እና ቻል አድርጎ እዲያልፍ ይጠበቅበታል። ይህ በተለምዶ ለወንዶች የተሰጠ ማንነት ነው።

በአጋጣሚ ከአቅሙ በላይ ሆኖ ካለቀሰ " ወንድ አይደለህ ጠንከር በል እንጂ የምን መልፈስፈስ ነው " ይባላል። ታዲያ ይህ የማህበረሰብ ጫና የሚሰማውን እና እያሳለፈ ያለዉን ከመናገር በራሱ እንዲወጣው እና እልፍ ሲል እራሱ ላይ እርምጃ እንዲወስድ ይገደዳል።

በዓለማችን በየዓመቱ ራሳቸውን ከሚያጠፉ 700,000 በላይ ሰዎች መካከል ከ450,000 በላይ የሚሆኑት ወንዶች ናቸው።

በሰዓት 60 ወንዶች፣ በቀን 1,500 ወንዶች ፣ በሳምንት 12,000፣ በወር 45,000 በላይ ወንዶች ራሳቸውን ያጠፋሉ። ይሄ ቁጥር ታዲያ ሙከራ የሚያደርጉትን ሳይጨምር ነው፡፡

ማልቀስ እና ስሜትን በግልጽ መናገር ሰው የመሆናችን ተፈጥሯዊ መገለጫዎች እንጂ የወንድነት መለኪያዎች አይደሉም። የሚሰማንን ለሌሎች ማጋራት የደካማነት መገለጫ አይይለም፤ እርዳታ መጠየቅ እና የአዕምሮ ህክምና ማድረግም ከወንድነት ጋር አይገናኝም።

ስለዚህ ወንዶች በየትኛውም የህይወት ጫና ዉስጥ እያለፍቹ ቢሆንም ብቻችሁን አይደላችሁም፤እርዳታ መጠየቅ ደግሞ የሽንፈት ወይም ያለመቻል ምልክት አይደለም።

የአዕምሮ ጤና ለሁሉም!!

ምንጭ:- ቲክቫህ ኢትዮጵያ

Address

Addis Abeba
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tena adam Promotion/ጤና አዳም ፕሮሞሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share