በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Awassa
  • በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት''Prosperity Party Office"

በ2018 ዓ/ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ፈተናዎች በሰላምና ከኩረጃ በፀዳ ሁኔታ እንዲጠናቀቁ የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ተገለጸ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ሰኔ 6/2018 ዓ.ም...
13/06/2026

በ2018 ዓ/ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ፈተናዎች በሰላምና ከኩረጃ በፀዳ ሁኔታ እንዲጠናቀቁ የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ተገለጸ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰኔ 6/2018 ዓ.ም

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ትምህርት ቤቶች ጽህፈት ቤት የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናዎችን በተሳካ ሁኔታ ለማስፈጸም ከፈተና አሰፈጻሚዎች እና ከጸጥታ አካላት እና ከትምህርት ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ጋር የውይይትና የኦሬንቴሽን መድረክ በእንሴኖ ከተማ አካሂዷል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ እና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ከድር አብደላ እንደገለጹት የፈተና ሂደቱ በሙሉ ሰላምና ፍትሃዊነት እንዲጠበቅ የፈታኝ መምህራን፣
የሱፐርቫይዘሮች፣የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎችና የጸጥታ አካላት ትብብር ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል።

የዘንድሮው ክልላዊ ፈተና ከሰኔ 8 ጀምሮ በ ስምንት የፈተና ጣቢያ እንደሚሰጥ የገለጹት አቶ አድማሱ፣የ6ኛ ክፍል ፈተና ከተጠናቀቀ በኋላ በቀጣዩ ቀን የ8ኛ ክፍል ፈተና እንደሚጀምርም ጠቁመዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ም/ኃላፊ አቶ አድማሱ አሰራት እንደገለጹት የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናዎች በሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ከኩረጃ በፀዳ መንገድ እንዲካሄዱ የፈታኝ መምህራን፣ የጸጥታ አካላትና የትምህርት ዘርፉ ባለድርሻዎች ሚና ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

ፈተናዎቹ የተማሪዎችን ዕውቀትና ብቃት ከመለካት ባለፈ የትምህርት ሥርዓቱን ተዓማኒነት የሚያሳዩ በመሆናቸው ሁሉም አካላት የተጣለባቸውን ኃላፊነት በተገቢው መወጣት አለባቸው ብለዋል።

ም/ኃላፊው አክለው ፈተናዎቹን ከኩረጃ በፀዳና ሰላማዊ መንገድ ለማካሄድ ዝግጅት መደረጉን ጠቅሰው በዚህም 1 ሺህ 252 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች እና 996 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ለፈተናው መዘጋጀታቸውን አስታውቋል።

በመድረኩ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናዎች አሰጣጥ ላይ የተዘጋጀ በአቶ ጀሚል ምትኩ የፈተናና ምዘና ስራ ሂደት ዳይሬክቶሬት አማካኝነት ሰነድ ቀርቦ ውይይት በማድረግ በውይይቱም የፈተና ሂደት አፈጻጸምን የተመለከተ የጋራ መግባባት ተፈጥሯል።

በመድረኩ ላይ የትምህርት ጽህፈት ቤቱ ማናጅመንት አባላት፣ አስፈታኝ መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮች፣ የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎችና የፖሊስ አባላት ተሳትፈዋል።

ዘገባው የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው

ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንካችን ገብታችሁ like shere commment እንድታደርጉ

https://www.facebook.com/profile.php?id=100065084628552

የምስራቅ መስቃን ወረዳ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ጽ/ቤት የገጠር መሬት መረጃ ማጥራት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ሰኔ 6/2018 ዓ/ምየገ...
13/06/2026

የምስራቅ መስቃን ወረዳ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ጽ/ቤት የገጠር መሬት መረጃ ማጥራት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰኔ 6/2018 ዓ/ም

የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ሥርዓትን ለማጠናከር እንዲሁም የመሬት መረጃዎችን ትክክለኛነትና ተዓማኒነት ለማረጋገጥ ያለመ የገጠር መሬት መረጃ ማጥራት ስልጠና ለባለድርሻ አካላት ተሰጠ።

በስልጠናው የዞን፣ የወረዳና የቀበሌ ባለሙያዎች፤የቀበሌ ሊቀመናብርት፤ ስራአስኪያጆች፤የመሬት አስተዳደር ባለሙያዎች ተሳትፈው በመሬት መረጃ ማጥራት ሂደት፣ በመረጃ ጥራት ቁጥጥር፣ በNRLAIS ሥርዓት ውስጥ የሚገኙ የጽሑፍና የካርታ መረጃዎች ማስተካከያ እንዲሁም በመረጃ አያያዝ ዙሪያ ሰፊ ግንዛቤ ተሰጥቷል።

ስልጠናውን የመሩት የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ፅ/ቤት ሀላፊው አቶ ሳቢር አማን እንደገለጹት የመሬት መረጃ ማጥራት የባለይዞታዎችን መብት ከማስጠበቅ ባለፈ የመሬት ግጭቶችን ለመቀነስ፣ የመንግሥት ዕቅድና የልማት ሥራዎች በትክክለኛ መረጃ ላይ እንዲመሰረቱ ያግዛል ብለዋል።

የመሬት መረጃ ማጥራት ሂደት በመዝገቦች ውስጥ ያሉ ስህተቶችን፣ ድግግሞሽ መረጃዎችን፣ የጎደሉ መረጃዎችን እና ያልተጣጣሙ መረጃዎችን መለየትና በማስተካከል በጽሑፍ መረጃዎች የባለይዞታ ስም፣ መታወቂያ ቁጥር፣ የይዞታ መለያ ቁጥር በካርታ መረጃዎች የመሬት ወሰኖች መደራረብ፣ ክፍተቶች (Gaps)፣ የተሳሳቱ አቀማመጦች እና ሌሎች የጂኦሜትሪ ስህተቶች እንደሚስተካከሉ አብራርተዋል።

ሀላፊው አክለው የገጠር መሬት መረጃን በየጊዜው ማዘመን የአርሶ አደሮችን የመሬት ይዞታ መብት በማረጋገጥ፣ የመሬት አስተዳደር አገልግሎትን በማቀላጠፍ እና የልማት ሥራዎችን በተሻለ ሁኔታ ለማከናወን ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልፀዋል።

በወረዳው የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ፅ/ቤት የሲስተም ባለሙያ የሆኑት አቶ ተካልኝ አስፋው እንደገለፁት ይህ ሂደት የመሬት ምዝገባን ተዓማኒነት በማጠንከር ፣ የባለይዞታዎችን መብት በማስከበርና የመሬት ግጭቶችን በመቀነስ ለእቅድ ዝግጅትና ለውሳኔ አሰጣጥ ትክክለኛ መረጃ እንዲገኝ ያግዛል ብለዋል።

የወረዳው የግብርና ፅ/ቤት ምክ/ሀላፊና የእርሻ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሁሴን ሙስጠፋ ጥራት ያለው የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ካርታ ሰርተፍኬት የይዞታ መብትን በትክክል የሚያረጋግጥ ሰነድ በመሆኑ የፋይናንስ ተቋማት ለአርሶ አደሮች ብድር ለመስጠት የሚያስችል አስተማማኝ መሰረት ይፈጥራል ብለዋል ።

ይህም አርሶ አደሮች ለግብርና ግብዓቶች፣ ለመስኖ ልማት፣ ለእንስሳት እርባታና እና ለሌሎች ገቢ አመንጪ ስራዎች የሚያስፈልጋቸውን ፋይናንስ በቀላሉ እንዲያገኙ የሚያግዝ በመሆኑ በዚህ አገልግሎት አማካኝነት የሚገኘው ብድር የተሻሻሉ ዘሮችን፣ ማዳበሪያዎችን እና ዘመናዊ የእርሻ መሳሪያዎችን ለመግዛት የሚያስችል በመሆኑ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል።

የግብርና ፅ/ቤት ምክ/ሀላፊና የተፈጥሮ ሀብት ዘርፍ ሀላፊው አቶ አዲሱ እንዳለ እንደገለጹት የተዘመነ የመሬት መረጃ መኖሩ የአርሶ አደሮችን የይዞታ መብት በህጋዊ መንገድ ለማስከበር ከፍተኛ ሚና አለው። በተጨማሪም በወሰን እና በይዞታ መብት ዙሪያ የሚነሱ ግጭቶችን በመቀነስ በማህበረሰቡ ውስጥ ሰላምና መተማመን እንዲጠናከር ያግዛል።

የዘመነ የመሬት መረጃ ለመንግሥት እና ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ትክክለኛ ውሳኔ ለመስጠት እንዲሁም የእርሻ ልማት፣ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና የመሰረተ ልማት እቅዶችን በትክክል ለማቀድ ጠቃሚ መሆኑ ጠቁመዋል።

በስልጠናው ተገኝተው ማብራሪያ የሰጡት የምስራቅ ጉራጌ ዞን የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ፅ/ቤት ባለሙያ አቶ ጫሊ አብደላ እንደገለፁት በመሬት መረጃ ላይ የሚገኙ ስህተቶችን፣ የተደጋገሙ መዝገቦችን እና ያልተሟሉ መረጃዎችን በማስተካከል የመሬት ምዝገባና ሰርተፊኬት አሰጣጥ አገልግሎት ቀልጣፋና ተዓማኒ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።

በመድረኩ የተገኙ ተሳታፊዎችም ከስልጠናው ያገኙትን ግንዛቤ ወደ ሥራ በመቀየር በየአካባቢያቸው የመሬት መረጃ ጥራትን ለማሻሻል በሚሰሩ እንቅስቃሴዎች አጋዥ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።

ዘገባው የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው

በምስራቅ መስቃን ወረዳ 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የታዩ ጥንካሬዎች እና በቀጣይ በቀሪ ቀናት በሚሰሩ ስራዎች ዙርያ የወረዳው አጠቃላይ አመራር በተገኙበት ገመገመ።።።።።።።።።።።።።።።።።...
06/06/2026

በምስራቅ መስቃን ወረዳ 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የታዩ ጥንካሬዎች እና በቀጣይ በቀሪ ቀናት በሚሰሩ ስራዎች ዙርያ የወረዳው አጠቃላይ አመራር በተገኙበት ገመገመ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ግንቦት 29/2018 ዓ/ም
የወረዳው አመራሮች በተገኙበት 7ተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በተመለከተ የነበረው ወረዳዊ ነባራዊ ሁኔታ እና በቀጣይ በቀሪ ቀናቶች በሚሰሩ ስራዎች ያተኮረ የግምገማ መድረክ ተካሄደ።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር መሀመድ ሰብራላ የ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ አፈፃፀም በተመለከተ የነበረው ሂደትና የምርጫ ሚና ምን ይመስል እንደነበር በመተንተን በየምርጫ ጣቢያው የነበሩ ተግዳሮቶች በመቋቋም ምርጫው በወረዳው በሁሉም የምርጫ ጣቢያ ሰላማዊ በሆነ መልኩ መጠናቀቅ መቻሉ የሁሉም ቁርጠኝነትና ትጋት ታሪካዊ ማሳያ መሆኑ ገልጸዋል።

በምርጫው ወቅት የነበረው ፈጣንና ቀልጣፋ የመረጃ ልውውጦች እጅግ የሚበረታቱ እንደነበሩ እና አመራሩ ይህን የምርጫ ተግባር ለማሳካት ያሳየው ቁርጠኝነት እጅግ የሚደነቅ እንደሆነ ተናግረዋል።

በቀጣይ በቀሪ ቀናት በትኩረት የሚከናወኑ:-የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ፣የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ሰርቲፋይ ማድረግ፣በአንድ ወረዳ አንድ ኘሮጅክት፣የገጠር ኮሊደር፣የገቢ አማራጭ ተጠቅሞ ማሰባሰብ፣የሰንበት ገበያ ማጠናከር፣የኑሮ ውድነት ማረጋጋት፣የግብርና ስራ ትኩረት መስጠት፣

ከትምህርት ጋር ተያይዞ የተማሪዎች ውጤት ትኩረት መስጠት፣ከፀጥታ ጋር በተያያዘ በሁሉም ቀበሌ ሮንድ ማጠናከር፣የመንግስት ሰራተኛ መረጃ ማጥራት፣E-LMIS ከኢንተርኘራይዝ ጋር በተያያዘ እና ከነዳጅ ቺፍቼ ነጋዴዎች ጋር በተያያዘ በትኩረት ሊመሩ እንደሚገባ ዋና አስተዳዳሪው አቅጣጫ ሰጥተዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሀላፊ እና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ከድር አብደላ እንደገለፁት በወረዳችን 7ተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በመደማመጥ እና በመቀናጀት የተመራ ውጤታማ ምርጫ እንደነበረም ገልጸዋል።

‎ምርጫው ፍፁም ሰላማዊ እንዲሆን የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ የነበረበት ነው ያሉት አቶ ከድር ለዚህም የወረዳችን ማህበረሰብ ሚና በጉልህ የሚጠቀስ እንደሆነ ተናግረዋል።

‎የፀጥታ አካላት ምርጫው በሰላማዊ ሁኔታ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ የአንበሳውን ድርሻ ተወጥተዋል ሲሉም ሀላፊው ጠቁመዋል።

በመጨረሻ 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የሁሉም ከወረዳ አመራር ጀምሮ እስከ ቀበሌ አመራር ቅንጅትና ትብብር የታየበትና ውጤታማ ምርጫ እንደነበር ተገለፀ።

በመድረኩ የወረዳ አስተባባሪ አካላት እና የወረዳ አጠቃላይ አመራሮች ተሳትፈዋል።

ዘገባው የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

የ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የመስቃን እና ማረቆ ቁጥር ሁለት  ምርጫ ክልል ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት ይፋ ሆነ።ግንቦት 29/2018 ዓ.ምየ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የመስቃን እና ማረቆ ቁጥር...
06/06/2026

የ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የመስቃን እና ማረቆ ቁጥር ሁለት ምርጫ ክልል ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት ይፋ ሆነ።

ግንቦት 29/2018 ዓ.ም

የ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የመስቃን እና ማረቆ ቁጥር ሁለት ምርጫ ክልል ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት ይፋ ሆኗል።

የመስቃን ማረቆ ምርጫ ክልል አስተባባሪ የሆኑት አቶ
አድማሱ መኮንን ግንቦት 24/የተደረገው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ በዛሬው ዕለት አጠቃላይ የምርጫ ክልሉ ውጤት ይፋ መሆኑን አሳውቀዋል።

የመስቃንና ማረቆ የምርጫ ክልል ውስጥ 122 የምርጫ ጣቢያዎች እንደነበሩ ገልፀው ከድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ከተጠናቀቀ በኃላ 122 የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ወረቀቶች ተሰብስቦ የማጠቃለል ስራ ሲሰራ እንደነበረ ተናግረዋል ።

በዛሬው ዕለትም የመደመርና የማጠቃለል ስራ በማጠናቀቅ ጊዜያዊ ውጤት ይፋ መደረጉን ገልፀዋል።

በዚህም በምርጫ ክልሉ ውስጥ 165,000 ህዝብ የምርጫ ካርድ እንደወሰዱ ገልፀው ከዚህ ውስጥ 134,048
ህዝብ ድምፅ እንደሰጠ ተናግረዋል።

በዚህም መሠረት በመስቃን እና ማረቆ ምርጫ ክልል

✅ለክልል ምክር ቤት እጩ ከቀረቡት መካከል
የተመዘገበው ውጤት
✅አቶ ጀማል አማሮ ብልፅግና ____117,099
✅አቶ አሰፋ ደቼ ብልፅግና _____115,849
✅ኢንጂነር ሲቲ ሙስጠፋ ብልፅግና _____105,849
✅ወ/ሮ ዮዲት አህመድ ብልፅግና _____104,195
✅ዶ/ር መሐመድ ሰብራላ ብልፅግና ______102,366

✅አቶ መቻል ሎሜሮ ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ_____3121
✅አቶ ቁፋ ሜጤቦ ሁንዲቶ___1675 ነእፓ
✅አቶ መሐመድ ሙስጤ___2810 ነእፓ
✅አቶ ሳቢር ሽፋ___3002 ነእፓ
✅አቶ ጉልላት አበበ___2181 ጎጎት
✅አቶ ተመስገን አለሙ___1798 ጎጎት
✅አቶ ሙሉጌታ አበራ አያሌው___669 ኢዜማ
✅አቶ ከድር ባዱሎ__906 ኢዜማ
ድምፅ ማግታቸውን ተገልጿል።

✅ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብልፅግና ፒርቲ

ዶ/ር መለሰ ጡሚሶ ብልፅግና ፓርቲ_____113,164
✅አቶ እንዳልካቸው አወል ሁሴን___13377 ጎጎት
✅አቶ ትግሉ ይልማ____478 ኢዜማ
✅ወሮ አሚና አብዱ ____1475 ነእፓ
✅አቶ ደረጀ ታምሩ_____512 የወሎ ህዝቦች

ድምፅ ማግታቸውን ተገልጿል።

ዘገባው የማረቆ ልዩ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው፡፡

በምስራቅ መስቃን ወረዳ እና በእንስኖ ከተማ አስተዳደር በሴቶች እና ህፃናት ጽ/ቤት እና በሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት አስተባባሪነት"የምርጫ ቅስቀሳ እና የቡና ጠጡ" መርሃ-ግብር ተካሄደ ::።።።።።...
25/05/2026

በምስራቅ መስቃን ወረዳ እና በእንስኖ ከተማ አስተዳደር በሴቶች እና ህፃናት ጽ/ቤት እና በሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት አስተባባሪነት"የምርጫ ቅስቀሳ እና የቡና ጠጡ" መርሃ-ግብር ተካሄደ ::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ግንቦት 17/2018 ዓ/ም

‎በምስራቅ መስቃን ወረዳ እና በእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ በሴቶች አስተባባሪነት "የምርጫ ቅስቀሳና ቡና ጠጡ"መርሐ ግብር በእንሴኖ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተካሂዷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ም/ዋና ዳይሬክተርና የመንግስት ፕሮጄክቶች ግንባታ ክትትልና ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር እና በመስቃን እና ማርቆ ቁጥር 2 ምርጫ ክልል የክልል ዕጩ ተወዳዳሪ ኢንጂነር ሲቲ ሙስጠፋ እንደገለፁት ምርጫ ያለ ሴቶች ተሳትፎ እንደማይሆን ገልፀዋል። ሴቶች ለምርጫ የእኩልነት ሚና እንዲኖራቸዉ እና የምርጫ ድርሻቸው ጎልቶ እንዲወጣ የሴቶች ተሳትፎ ወሳኘ መሆኑን ተናግረዋል።

‎በምርጫው የብልጽግና ፓርቲ ምልክት የሆነውን ''የስንዴ ነዶ'' በመምረጥ የተጀመረውን ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ መላው ሴቶች ድምጻቸውን ለብልጽግና ፓርቲ እንዲሰጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምርያ ኃላፊ ወ/ሮ ረሂማ ሳይድ ‎ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች በማህበራዊ፣በኢኮኖሚና በፖለቲካ ዘርፎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራበት መሆኑን በመግለፅ ሴቶችም ከፓርቲ ጎን በመሆን የተጀመሩ ልማታዊና ፖለቲካዊ ለውጦችን ማስቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል ።

አክለውም ብልጽግና ፓርቲን መምረጥ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ዕድገት ማረጋገጥ በመሆኑ ሁሉም ካርድ የወሰዱ ሴቶች የምርጫ ምልክት የሆነውን ስንዴ ነዶ በመምረጥ ከፓርቲ ጎን እንዲቆሙ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን አመራሮች፣የምስራቅ መስቃን ወረዳ እና የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር አስተባባሪ አካላቶች፣የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ዋና አፈ ጉባኤ እና የክልል ዕጩ ተወዳዳሪ ወ/ሮ ዮዲት አህመድ፣የምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ክብርት መዲና ኤርጎሻ፣እንዲሁፍ የሴቶች አደረጃጀት አመራሮች እና ሌሎችም ባለ ድረሻ አካላት ተሳትፈዋል።

‎"የምርጫ ቅስቀሳና የቡና ጠጡ" ፕሮግራም በእንሴኖ ከተማና በምስራቅ መስቃን ወረዳ ሴቶችና ህጻናት፤በሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት አሰተባበሪነት በድምቀት ተካሂደዋል።(ግንቦት 17/18/ዓም)‎በምስራቅ...
25/05/2026

‎"የምርጫ ቅስቀሳና የቡና ጠጡ" ፕሮግራም በእንሴኖ ከተማና በምስራቅ መስቃን ወረዳ ሴቶችና ህጻናት፤በሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት አሰተባበሪነት በድምቀት ተካሂደዋል።

(ግንቦት 17/18/ዓም)

‎በምስራቅ መስቃን ወረዳ እና በእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ህፃናት የሴቶች ክንፍ አስተባባሪነት "የምርጫ ቅስቀሳና ቡና ጠጡ" ፕሮግራም መረሃ ግብረ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብረዋል ።

‎በቡና ጠጡ ፕሮግራም የሴቶች ክንፍ 7ተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲን እንዲመርጡ የቅስቀሳ ተግባር በእንሴኖ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ዝግጅቶች አካሄደዋል።

‎በምርጫው የብልጽግና ፓርቲ ምልክት የሆነው ''የስንዴ ነዶ'' በመመረጥ የተጀመረውን ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ መላው ሴቶች ድምጻቸውን ለብልጽግና ፓርቲ እንዲሰጡ የምስራቅ መስቃን ወረዳ ና የእንሴኖ ከተማ ሴቶችእና ህፃናት ፤ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት በጋራ በመሆን
‎በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተካሂዶዋል፡፡

በምስራቅ መስቃን ወረዳ  የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ አካል የሆነዉ የ"ቡና ጠጡ" ፕሮግራም በብልፅግና  ቤተሰብና በመንደር ደረጃ  ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።ግንቦት 15/2018 ዓ/ምበም...
23/05/2026

በምስራቅ መስቃን ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ አካል የሆነዉ የ"ቡና ጠጡ" ፕሮግራም በብልፅግና ቤተሰብና በመንደር ደረጃ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

ግንቦት 15/2018 ዓ/ም

በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ቅስቀሳ አካል የሆነዉ የ"ቡና ጠጡ" መርሃ ግብር በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎቾና መንደሮችናበብልፅግና በቤተሰብ ደረጃ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

ይህ በብልጽግና ህብረት እና በቤተሰብ ደረጃ የተከናወነው የሚገኘው የቡና ጠጡ መርሃ ግብር፤ ፓርቲው ባለፉት ዓመታት ያስመዘገባቸውን የልማትና የሰላም ስኬቶች ለህብረተሰቡ ለማስተዋወቅ ያለመ እንደሆነም ተመላክቷል።

በዛሬው ዕለትም በወረዳው በይመርዋጮ1ኛ ቀበሌ የወጣቶች ክንፍ ብልፅግና ህብረት እና በሀሙስ ገበያ በመስኖ ብልፅግና ቤተሰብ ደረጃ የምርጫ ቅስቀሳና የቡና ጠጡ ፕሮግራም ተካሂዷል።

በፕሮግራሙ ደጋፊ አመራሮች የቀበሌ አስተዳዳሪና በየቀበሌው ኮር አመራሮች በየአደረጃጀቶቹ በመገኘት የፓርቲውን የምርጫ ምልክት (የስንዴ ነዶ) እና ዕጩ ተወዳዳሪዎችን የማስተዋወቅ ስራ ሰርተዋል።

በዚህም "ኑ ቡና ጠጡ" መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉ ነዋሪዎችና የፓርቲው አባላት ለፓርቲው ያላቸውን ድጋፍ የገለጹ ሲሆን፣ በቀጣይም ለሀገር ብልጽግናና ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ከፓርቲው ጎን እንደሚቆሙ አረጋግጠዋል።

ብልፅግናን ይመረጡ
ምልክታችን የስንዴ ነዶ ነው
ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር

‎ሴቶች በመጪው 7ተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ ያላቸውን ዝግጁነትና ለብልጽግና ፓርቲ ያላቸውን ድጋፍ ለመግለጽ በድጋፍ ሰልፍ አሳይተዋል። ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ግንቦት 14/2...
23/05/2026

‎ሴቶች በመጪው 7ተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ ያላቸውን ዝግጁነትና ለብልጽግና ፓርቲ ያላቸውን ድጋፍ ለመግለጽ በድጋፍ ሰልፍ አሳይተዋል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ግንቦት 14/2018 ዓ.ም
ድምፃችን ለብልጽግና ነው፣ ምርጫየን ከሚያደናቅፍ ጠላት አልተባበርም፣ብልጽግናን መምረጥ የተሻለ ነው የሚሉና ሌሎችንም መፈክሮች በሰልፉ ላይ አሰምተዋል።

ምርጫ የዜግነት መብትን የመጠቀም ብቻ ሳይሆን ሂደቱን ነፃ፣ፍትሀዊና ዲሞክራሲያዊ በማድረግ የሀገርን የነገ ብሩህ ተስፋ የምንወስንበት ነው ሲሉ በነበረው በድጋፉ ሰልፍ ድምፃቸው አሰምተዋል።

ለዚህ ደግሞ የሴቶች ሚና ከፍተኛ ስለሆነ በምርጫ ሂደቱ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ሰላማዊና ፍትሀዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እንደሚሰሩ በድጋፍ ሰልፍ አረጋግጠዋል።

22/05/2026
22/05/2026

ሀገራዊ ለውጡን እውን የሆነበት 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫን አስመልክቶ የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ እና የድጋፍ ሰልፍ በምስራቅ መስቃን መስቃን ወረዳ እና እንሴኖ ከተማ አስተዳደር አስተባባሪነት በእንሴኖ ከተማ የተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ በምስል ፦

Address

Awassa

Telephone

+251964476649

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት:

Share