13/06/2026
በ2018 ዓ/ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ፈተናዎች በሰላምና ከኩረጃ በፀዳ ሁኔታ እንዲጠናቀቁ የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ተገለጸ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰኔ 6/2018 ዓ.ም
የምስራቅ መስቃን ወረዳ ትምህርት ቤቶች ጽህፈት ቤት የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናዎችን በተሳካ ሁኔታ ለማስፈጸም ከፈተና አሰፈጻሚዎች እና ከጸጥታ አካላት እና ከትምህርት ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ጋር የውይይትና የኦሬንቴሽን መድረክ በእንሴኖ ከተማ አካሂዷል።
የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ እና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ከድር አብደላ እንደገለጹት የፈተና ሂደቱ በሙሉ ሰላምና ፍትሃዊነት እንዲጠበቅ የፈታኝ መምህራን፣
የሱፐርቫይዘሮች፣የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎችና የጸጥታ አካላት ትብብር ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል።
የዘንድሮው ክልላዊ ፈተና ከሰኔ 8 ጀምሮ በ ስምንት የፈተና ጣቢያ እንደሚሰጥ የገለጹት አቶ አድማሱ፣የ6ኛ ክፍል ፈተና ከተጠናቀቀ በኋላ በቀጣዩ ቀን የ8ኛ ክፍል ፈተና እንደሚጀምርም ጠቁመዋል።
የምስራቅ መስቃን ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ም/ኃላፊ አቶ አድማሱ አሰራት እንደገለጹት የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናዎች በሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ከኩረጃ በፀዳ መንገድ እንዲካሄዱ የፈታኝ መምህራን፣ የጸጥታ አካላትና የትምህርት ዘርፉ ባለድርሻዎች ሚና ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
ፈተናዎቹ የተማሪዎችን ዕውቀትና ብቃት ከመለካት ባለፈ የትምህርት ሥርዓቱን ተዓማኒነት የሚያሳዩ በመሆናቸው ሁሉም አካላት የተጣለባቸውን ኃላፊነት በተገቢው መወጣት አለባቸው ብለዋል።
ም/ኃላፊው አክለው ፈተናዎቹን ከኩረጃ በፀዳና ሰላማዊ መንገድ ለማካሄድ ዝግጅት መደረጉን ጠቅሰው በዚህም 1 ሺህ 252 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች እና 996 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ለፈተናው መዘጋጀታቸውን አስታውቋል።
በመድረኩ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናዎች አሰጣጥ ላይ የተዘጋጀ በአቶ ጀሚል ምትኩ የፈተናና ምዘና ስራ ሂደት ዳይሬክቶሬት አማካኝነት ሰነድ ቀርቦ ውይይት በማድረግ በውይይቱም የፈተና ሂደት አፈጻጸምን የተመለከተ የጋራ መግባባት ተፈጥሯል።
በመድረኩ ላይ የትምህርት ጽህፈት ቤቱ ማናጅመንት አባላት፣ አስፈታኝ መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮች፣ የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎችና የፖሊስ አባላት ተሳትፈዋል።
ዘገባው የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው
ወቅታዊና ፈጣን መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከታች ባለው ሊንካችን ገብታችሁ like shere commment እንድታደርጉ
https://www.facebook.com/profile.php?id=100065084628552