25/05/2026
ብልፅግናን መምረጥ ማለት በከተማችን የተጀመሩ በርካታ የልማት ዕቅዶችና ፕሮግራሞች ከማጠናቀቅም ባሻገር በሀገር ደረጃ ተወዳዳሪና ሁለንተናዋ ብልፅግና የተረጋገጠላት የኢንዱስትሪ ማእከል የሆነች ከተማን መገንባት ማለት ነው!! ክቡር ከንቲባ አቶ በለጠ ጫካ።
ግንቦት17/2018 ዓ/ም
=====ቡኢ======
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡኢ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ቅስቀሳ አካል የሆነዉ የ"ቡና ጠጡ" መርሃ ግብር በከተማው በተለያዩ መንደሮችና በቤተሰብ ደረጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የቡኢ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ በለጠ ጫካ ብልፅግና ፓርቲ ከተመሰረተ ጊዜ ጀምሮ በብዙ ፈተናና ውስብስብ የፀጥታ ችግር ውስጥ ሆኖ ብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ መርን በመከተል በተመረጡ አምስት ዘርፎች ማለትም በቱሪዝሙ፣ በማእድንና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በግብርናው ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ ያስመዘገበ ፓርቲ እንደሆነ በዝርዝር አስረድተዋል።
ክቡር ከንቲባው አክለውም ከተማችን ቡኢ ከተማ አስተዳደርም የብልፅግና ትሩፋት ነች ስንል ቀድሞ በማዘጋጃ ቤት ሲመራ ቆይቶ ከለውጡ መንግስት በኃላ በብልፅግና መንግስት መሪነት የከተማ አስተዳደርነት መዋቅር አግኝቶ የበርካታ የመሰረተ ልማትና የኢንደስትሪ ማእከል መሆኗን በተጨባጭ ስለተረጋገጠባት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
ከለውጡ መንግስት በኃላ ዘመን ተሻጋሪና የማህበረሰቡ ችግር ፈቺ የሆኑ በርካታ የልማት ስራዎች በፓርቲው መሪነት ከተፈፀሙት መካከል ለአብነትም በቂ የሆነ የመብራት አቅርቦት ሰብስቴሽን ተጠቃሚ እንድትሆን ማድረጓ ተጠቃሽ ነው ብለዋል።
ከትምህርት ልማት ስራዎች አኳያም በአካባቢው ማህበረሰብና መንግስት በማስተባበር የሶዶ ቡኢ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአዲስ መልክ ገንብቶ ማጠናቀቅ፣ በትምርት ለትውልድ ፕሮግራም የተማሪዎች ምገባና፣ የመማሪያ መፅሀፍትና ግባቶች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገብ ተችሏልም ብለዋል።
በዚህም የማህበረሰቡ የትምህርት ፍላጎትና የከተማዋ ምቹነት መነሻ በማድረግ በኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስተር እየተገነባ ያለው የቡኢ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት የከተማችን አንዱ የእድገትና የብልፅግናዋ ማሳያ ነው ብለዋል።
ከጤና ልማት አኳያም በከተማዋ ምንም ካልነበረበት የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ጣቢያ ከተማው በራሱ አቅም ገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጋችንም አንዱ የፓርቲያችን የብልፅግና የፕሮጀክቶች ጀምሮ የመፈፀም መርህ ማሳያ ነው ሲሉም ገልፀዋል።
ከመሰረተ ልማት አኳያም ማህበረሰቡ ለረዥም ጊዜ ሲቸገሩበት የነበረው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጅክት በፓርቲያችን ልዩ ትኩረትና ድጋፍ ባለፈው በጀት ዓመት አጠናቀን ከተማዋ 24 ሰዓት በቂ የሆነ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ እንድትሆን አድርገናታል ብለዋል።
ከሰላምና ደህንነት አኳያም መላው የከተማችን ማህበረሰብና የፀጥታ አካላት በቅንጅት በመስራት ከተማዋ የሰላም አምባሳደር እንድትሆን በማድረግ 24ሰዓት በሚባል ደረጃ ያለምንም የፀጥታ ችግር ልማቷ እየተፋጠነ ይገኛልም ብለዋል።
ከኢንቨስትመንት አኳያም ከተማዋ ካላት ከማእከላዊ ገበያ ቅርበትና ከሞጆ ደረቅ ወደብ ቅርበት ብሎም ካለውም ተጨባጭ የመንግድ፣የውሃ፣የመብራትና ሌሎችም መሰረተ ልማቶች ምቹነት እንዲሁም ካለን ከመንግስት ቅቡልነት ልዩ ትኩረት ተደርጎ በክልሉ ተሞክሮ የሚሆኑ ግዙፍ የውጭ ቀጥተኛ የኢንቨስትመንት ማእከል እንድትሆን አድርገናታል ብለዋል።
በቀጣይም በከተማዋ የተጀመሩት በርካታ የልማት ስራዎች ማለትም የኮሪደር ልማት ስራ፣ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት፣ የመንገድ፣ የብራትና የውሃ መሰረተ ልማት አጠናክረን ለማስቀጠልና የከተማችን ሁለንተናዋ ብልፅግናን ለማረጋገጥና በክልሉ ይበልጥ የተሞክሮ ማእከል ለማድረግ አንድና አንድ ያለን አማራጭ ከገዢው መንግስት ጎን በመቆም ምርጫችን ብልፅግና ማድረግ እንዳለብን ሲሉ አሳስበዋል።
በፕሮግራሙ ላይ የቡኢ ከተማ አማካሪ ምክርቤት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ ንጉሴ ተክሌ፣ የቡኢ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ደበበ አዳነ፣የምስራቅ ጉራጌ ዞን ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ም/ኃላፊ አቶ አሰፋ ፈይሳ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ምክትልና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አዳነ ተሰማን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ ጠቅላላ አመራሮችና የሆስፒታል ሰፈር ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘገባው የቡኢ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።
ለተጨማሪ መረጃ
የፌስቡክ ገፃችን 👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100068066105775
#የቴሌግራም ፔጃችን👇
https://t.me/BueeGovermentcomunication35
#የቲክቶክ-ፔጃችን👇
https://www.tiktok.com/?_t=8rUU1rZG5aS&
#ኢንስታግራም https://www.instagram.com/bueegovrncommunication35?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==
#የዋትሳፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VayIqyN6mYPDqXJHKL3t
#ዩትዩብ
https://youtube.com/?si=ScPXI4i65LSi9V6p
#የቲዊተር (X)👇
https://x.com/BueeGovrnComm35?t=FvbB7Xk926nDj7_qXadSWg&s=35
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን