በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡኢ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Bu-I
  • በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡኢ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት

በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡኢ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ''አሰባሳቢ ገዢ ትርክት ለበለፀገች ኢትዮጵያ''!

ብልፅግናን መምረጥ ማለት በከተማችን የተጀመሩ በርካታ የልማት ዕቅዶችና ፕሮግራሞች  ከማጠናቀቅም ባሻገር በሀገር ደረጃ ተወዳዳሪና ሁለንተናዋ ብልፅግና የተረጋገጠላት የኢንዱስትሪ ማእከል የሆነ...
25/05/2026

ብልፅግናን መምረጥ ማለት በከተማችን የተጀመሩ በርካታ የልማት ዕቅዶችና ፕሮግራሞች ከማጠናቀቅም ባሻገር በሀገር ደረጃ ተወዳዳሪና ሁለንተናዋ ብልፅግና የተረጋገጠላት የኢንዱስትሪ ማእከል የሆነች ከተማን መገንባት ማለት ነው!! ክቡር ከንቲባ አቶ በለጠ ጫካ።

ግንቦት17/2018 ዓ/ም
=====ቡኢ======

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡኢ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ቅስቀሳ አካል የሆነዉ የ"ቡና ጠጡ" መርሃ ግብር በከተማው በተለያዩ መንደሮችና በቤተሰብ ደረጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የቡኢ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ በለጠ ጫካ ብልፅግና ፓርቲ ከተመሰረተ ጊዜ ጀምሮ በብዙ ፈተናና ውስብስብ የፀጥታ ችግር ውስጥ ሆኖ ብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ መርን በመከተል በተመረጡ አምስት ዘርፎች ማለትም በቱሪዝሙ፣ በማእድንና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በግብርናው ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ ያስመዘገበ ፓርቲ እንደሆነ በዝርዝር አስረድተዋል።

ክቡር ከንቲባው አክለውም ከተማችን ቡኢ ከተማ አስተዳደርም የብልፅግና ትሩፋት ነች ስንል ቀድሞ በማዘጋጃ ቤት ሲመራ ቆይቶ ከለውጡ መንግስት በኃላ በብልፅግና መንግስት መሪነት የከተማ አስተዳደርነት መዋቅር አግኝቶ የበርካታ የመሰረተ ልማትና የኢንደስትሪ ማእከል መሆኗን በተጨባጭ ስለተረጋገጠባት እንደሆነ አስገንዝበዋል።

ከለውጡ መንግስት በኃላ ዘመን ተሻጋሪና የማህበረሰቡ ችግር ፈቺ የሆኑ በርካታ የልማት ስራዎች በፓርቲው መሪነት ከተፈፀሙት መካከል ለአብነትም በቂ የሆነ የመብራት አቅርቦት ሰብስቴሽን ተጠቃሚ እንድትሆን ማድረጓ ተጠቃሽ ነው ብለዋል።

ከትምህርት ልማት ስራዎች አኳያም በአካባቢው ማህበረሰብና መንግስት በማስተባበር የሶዶ ቡኢ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአዲስ መልክ ገንብቶ ማጠናቀቅ፣ በትምርት ለትውልድ ፕሮግራም የተማሪዎች ምገባና፣ የመማሪያ መፅሀፍትና ግባቶች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገብ ተችሏልም ብለዋል።

በዚህም የማህበረሰቡ የትምህርት ፍላጎትና የከተማዋ ምቹነት መነሻ በማድረግ በኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስተር እየተገነባ ያለው የቡኢ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት የከተማችን አንዱ የእድገትና የብልፅግናዋ ማሳያ ነው ብለዋል።

ከጤና ልማት አኳያም በከተማዋ ምንም ካልነበረበት የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ጣቢያ ከተማው በራሱ አቅም ገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጋችንም አንዱ የፓርቲያችን የብልፅግና የፕሮጀክቶች ጀምሮ የመፈፀም መርህ ማሳያ ነው ሲሉም ገልፀዋል።

ከመሰረተ ልማት አኳያም ማህበረሰቡ ለረዥም ጊዜ ሲቸገሩበት የነበረው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጅክት በፓርቲያችን ልዩ ትኩረትና ድጋፍ ባለፈው በጀት ዓመት አጠናቀን ከተማዋ 24 ሰዓት በቂ የሆነ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ እንድትሆን አድርገናታል ብለዋል።

ከሰላምና ደህንነት አኳያም መላው የከተማችን ማህበረሰብና የፀጥታ አካላት በቅንጅት በመስራት ከተማዋ የሰላም አምባሳደር እንድትሆን በማድረግ 24ሰዓት በሚባል ደረጃ ያለምንም የፀጥታ ችግር ልማቷ እየተፋጠነ ይገኛልም ብለዋል።

ከኢንቨስትመንት አኳያም ከተማዋ ካላት ከማእከላዊ ገበያ ቅርበትና ከሞጆ ደረቅ ወደብ ቅርበት ብሎም ካለውም ተጨባጭ የመንግድ፣የውሃ፣የመብራትና ሌሎችም መሰረተ ልማቶች ምቹነት እንዲሁም ካለን ከመንግስት ቅቡልነት ልዩ ትኩረት ተደርጎ በክልሉ ተሞክሮ የሚሆኑ ግዙፍ የውጭ ቀጥተኛ የኢንቨስትመንት ማእከል እንድትሆን አድርገናታል ብለዋል።

በቀጣይም በከተማዋ የተጀመሩት በርካታ የልማት ስራዎች ማለትም የኮሪደር ልማት ስራ፣ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት፣ የመንገድ፣ የብራትና የውሃ መሰረተ ልማት አጠናክረን ለማስቀጠልና የከተማችን ሁለንተናዋ ብልፅግናን ለማረጋገጥና በክልሉ ይበልጥ የተሞክሮ ማእከል ለማድረግ አንድና አንድ ያለን አማራጭ ከገዢው መንግስት ጎን በመቆም ምርጫችን ብልፅግና ማድረግ እንዳለብን ሲሉ አሳስበዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የቡኢ ከተማ አማካሪ ምክርቤት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ ንጉሴ ተክሌ፣ የቡኢ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ደበበ አዳነ፣የምስራቅ ጉራጌ ዞን ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ም/ኃላፊ አቶ አሰፋ ፈይሳ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ምክትልና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አዳነ ተሰማን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ ጠቅላላ አመራሮችና የሆስፒታል ሰፈር ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

ዘገባው የቡኢ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ለተጨማሪ መረጃ
የፌስቡክ ገፃችን 👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100068066105775

#የቴሌግራም ፔጃችን👇
https://t.me/BueeGovermentcomunication35

#የቲክቶክ-ፔጃችን👇
https://www.tiktok.com/?_t=8rUU1rZG5aS&

#ኢንስታግራም https://www.instagram.com/bueegovrncommunication35?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

#የዋትሳፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VayIqyN6mYPDqXJHKL3t

#ዩትዩብ
https://youtube.com/?si=ScPXI4i65LSi9V6p

#የቲዊተር (X)👇
https://x.com/BueeGovrnComm35?t=FvbB7Xk926nDj7_qXadSWg&s=35

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን

ሻምፒዮኑ አርሰናል ዋንጫውን ተረከበ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ22 ዓመታት በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን የሆነው አርሰናል በዛሬው ዕለት ዋንጫውን ተረክ...
24/05/2026

ሻምፒዮኑ አርሰናል ዋንጫውን ተረከበ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ22 ዓመታት በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን የሆነው አርሰናል በዛሬው ዕለት ዋንጫውን ተረክቧል፡፡

ባለፉት ሦስት የውድድር ዓመታት በሊጉ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አርሰናል÷ በዚህ ዓመት አንድ ጨዋታ እየቀረው ሻምፒዮን መሆኑን ማረጋገጡ ይታወሳል፡፡

በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመራው የሰሜን ለንደኑ ክለብ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ የሊጉን የመጨረሻ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ከክሪስታል ፓላስ ጋር በማድረግ 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

በጨዋታው የአርሰናልን ግቦች ጄሱስ እና ማዱኬ ሲያስቆጥሩ ማቴታ የክሪስታል ፓላስን ግብ ከመረብ አሳርፏል።

በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የቡድን ግንባታ ሒደት ከ22 ዓመታት በኋላ ከሊጉ ዋንጫ ጋር የተገናኙት መድፈኞቹ ዛሬ ምሽት በሴልኸረስት ፓርክ ነው ዋንጫውን በክብር የተቀበሉት፡፡

 '' በሚል መሪ ቃል የከተማ አስተዳደሩ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ከከተማው ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት  በጋራ የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ አካሄደ፡፡ግንቦት 16/2018ዓ/ም======ቡኢ===...
24/05/2026

'' በሚል መሪ ቃል የከተማ አስተዳደሩ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ከከተማው ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት በጋራ የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ አካሄደ፡፡

ግንቦት 16/2018ዓ/ም
======ቡኢ======

በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡኢ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ከከተማው ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት በጋራ በመሆን ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የምርጫ ቅስቀሳ አካሂዷል፡፡

የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉት የቡኢ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ በለጠ ጫካ ባለፉት ስምንት የለውጥ አመታት በከተማ አስተዳደሩ በትምህርት፣ በጤና፣ በውሃ፣ በመንገድ፣ በኢንቨስትመንት በሰላምና ደህንነት እና ሌሎችም የብልጽግና ፓርቲ ጀምሮ የመፈፀም መርህን መሰረት በማድረግ የከተማው ደረጃ ከፍ የሚያደርጉና መሰረታዊ የሚባሉ የማህበረሰቡ ችግር ፈቺ የሆኑ የልማት ስራዎች መፈፀማቸውን በዝርዝር አቅርበዋል።

በለውጡ አመታት ወጣቶች በሁሉም መስክ ተሳታፊ በማድረግ በሀገር ደረጃ ብሎም በከተማችን የተሰሩ ስራዎች የወጣቱ ሚና ከፍተኛ እንደነበረ የጠቀሱት የቡኢ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ በለጠ ጫካ በሀገራችን ሊታዩ እና ሊመሰከሩ የሚችሉ ስራዎች መሰራታቸውን አስታውቀዋል፡፡

ወጣቶችን በኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መስክ ተጠቃሚ ለማድረግ ብልጽግና ፓርቲ ዘርፈ ብዙ ስራዎች አቅዶ እያከናወነ ይገኛልም ብለዋል።

የዘንድሮው 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ካለፉት ምርጫዎች የተለየ የዲሞክራሲ ልምምድ የሚደረግበት እና ዲሞክራሲን ለማጽናት መሰረት የሚጣልበት ምርጫ መሆኑንም ክቡር ከንቲባው ገልጸዋል፡፡

ወጣቶች የሀገር እውነተኛ ሀብት እንደመሆናቸው መጠን በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ሀገሬ ምን አደረገችልኝ ሳይሆን እኔ ለሀገሬ ምን አደረኩላት በሚል መርህ የተጀመረችዋን ኢትዮጵያ ማስቀጠል እንዳለባቸው መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

የቡኢ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪው አቶ ደበበ አዳነ በበኩላቸው በዛሬው እለት የተገናኘነው ታላቅ የጋራ ፕሮጀክታችን የሆነው ሀገረ መንግስት የምንመሰረትበት ወሳኝ ወቀት ላይ እንገኛለን ብለዋል።

ወጣቶች ሰላማዊ መንገድን በመምረጥና በምርጫ የሚመሰረት መንግስት ለማጽናት እውቀታቸውን ጉልበታቸውን እና የማስተባበር ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ መልእክት አስተላልፈዋል ፡፡

አያይዘውም ዋና የመንግስት ተጠሪው የነገይቷ ታላቋን ኢትዮጵያ ለመመስረት በጋራ ድምፃችን ለብልፅግና ፓርቲ በመስጠት ወጣቱ የሀገር ተረካቢ ብቻ ሳይሆን ባለቤትነቱን ማረጋገጥ አለበት ብለዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ብሩክታይት ፀጋዬ ፣የምስራቅ ጉራጌ ዞን ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ም/ኃላፊ አቶ አሰፋ ፈይሳ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ምክትልና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አዳነ ተሰማ ፣ የቡኢ ከተማ አማካሪ ምክርቤት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ ንጉሴ ተክሌን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ ጠቅላላ አመራሮች፣ ወጣቶችና ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተገኝተዋል።

ዘገባው የቡኢ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ለተጨማሪ መረጃ
የፌስቡክ ገፃችን 👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100068066105775

#የቴሌግራም ፔጃችን👇
https://t.me/BueeGovermentcomunication35

#የቲክቶክ-ፔጃችን👇
https://www.tiktok.com/?_t=8rUU1rZG5aS&

#ኢንስታግራም https://www.instagram.com/bueegovrncommunication35?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

#የዋትሳፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VayIqyN6mYPDqXJHKL3t

#ዩትዩብ
https://youtube.com/?si=ScPXI4i65LSi9V6p

#የቲዊተር (X)👇
https://x.com/BueeGovrnComm35?t=FvbB7Xk926nDj7_qXadSWg&s=35

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቢሮ በሶዶ ወረዳ ከዩኒሴፍ መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም ጋር በመተባበር ለSTEP ት/ቤቶች በባህሪ ግንዛቤ ጥናት ላይ የተመሰረተ የሴት ልጆችና የአካል ጉዳተኞች ሕጻ...
24/05/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቢሮ በሶዶ ወረዳ ከዩኒሴፍ መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም ጋር በመተባበር ለSTEP ት/ቤቶች በባህሪ ግንዛቤ ጥናት ላይ የተመሰረተ የሴት ልጆችና የአካል ጉዳተኞች ሕጻናት ትምህርት ላይ ለተከታታይ ሁለት ቀናት ለማህበረሰብ ክፍል ሲሰጥ የነበረው ውይይት አዘል ስልጠና ተጠናቀቀ።

ግንቦት 16/2018ዓ/ም

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቢሮ በምስራቅ ጉራጌ ዞን በሶዶ ወረዳ ከዩኒሴፍ መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም ጋር በመተባበር ለSTEP ት/ቤቶች በባህሪ ግንዛቤ ጥናት ላይ የተመሰረተ የሴት ልጆች፣ የአካል ጉዳተኞች ሕጻናት ትምህርት ላይ ለተከታታይ ሁለት ቀናት ለማህበረሰብ ክፍል ሲሰጥ የነበረው ውይይት አዘል ስልጠና ተጠናቋል።

የሶዶ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አትቶ ታደለ ብርሃኔ እንደገለፁት እንደ ወረዳ ዩኒሴፍ ፕሮግራም በልዩነት ድጋፍ እያደረገ መሆኑ እና ለተለያዩ ተቋማት ሀብቶች በመደገፍ የሚያደርገው እንቅስቃሴ ይበል የሚያሰኝ መሆኑ ገልጸዋል።

ስልጠናው በተቋማት ሁለንትናዊ ለውጥ እንዲታዩና እንዲመዘገቡ የማህበረሰብ ክፍል የበኩሉን መወጣት እንዳለበት አንስተው አካል ጉዳተኞች፣ሴቶችና ሕጻናት ላይ የሚደርሱ ጥቃትትን በመከላከል ረገድ እስከታች ድረስ ተወርዶ የማህበረሰብ ክፍል የማወያየትና የመፍትሔ አካል የመፍጠር ስራ በትኩረት ይሰራል በማለት ሰልጣኙ ትኩረት ሰጥቶ እንዲከታተል መልዕክታቸው አስተላልፈዋል።

የሶዶ ወረዳ የዩኒሴፍ ፕሮግራም የሱፐርቪዥን ቡድን መሪ የሆኑት አቶ አበራ ተካልኝ የማህበረሰብ ውይይት አጠቃላይ እይታን፣ዋና ዋና አለማዎች፣የባህሪ ግንዛቤ በመመልከት ረገድ፣የሴቶች፣የሕጻናትና የአካል ጉዳተኞች የሚገጥሟቸው ችግሮቾ፣የማህበረሰብ ውይይት ሂደት፣ጥበቃና ስሜታዊ ደህንነት፣የአካታችነት መመሪያዎች/መለኪያዎች ላይ እና ሌሎችም በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ስልጠና ስጥተዋል።

አጠቃላይ ከአካቶ ስራ ጋር በተያያዘ በአካል ጉዳተኞች፣ሴቶችና ሕጻናት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች ላይ ሰፊ ማብራሪያ በመስጠት የሰለጠነው አካል እስከ ታች ወርዶ የማህበረሰብ ክፍል እንደሚያሰለጥን ጥብቅ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ተሳታፊ አካላት በስልጠናው ሰፋ ጭብጥ እንዳገኙ ገልጸው ታች ላይ በመውረድ ችግሮች ለይቶ የማህበረሰቡ ክፍል እንደሚያሰለጥኑ በማንሳት ጠቃሚ ዜጋ በመፍጠር የሀገር ሉዐላዊነት ማረጋገጥ እንደሚቻል አንስተዋል።

ከመድረኩ የተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ በመስጠት ስልጠናው ተጠቃሏል።

በስልጠናው የት/ት ጽ/ቤት ኃላፊ፣ባለሙያዎች ፣የዩኒሴፍ አስተባባሪ አካላት፣ከማህበረሰብ ክፍል የተወጣጡ አርሶ አደሮች ፣ሴቶች፣ወጣቶች እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

ዘገባው የሶዶ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

የለውጡ መንግስት ብልፅግና ፓርቲ የተረሳው ከተሞኔት ለኑሮ ምቹ ተስማሚ እንዲሆን እየሰራ ነው፦ የርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ ዶ/ር ንጉሴ አስረስ ግንቦት 16/2018 የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋ...
24/05/2026

የለውጡ መንግስት ብልፅግና ፓርቲ የተረሳው ከተሞኔት ለኑሮ ምቹ ተስማሚ እንዲሆን እየሰራ ነው፦ የርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ ዶ/ር ንጉሴ አስረስ

ግንቦት 16/2018

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በተገኙበት የመስቃን ወረዳ የዶቢ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት ይፋዊ የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄዷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ ዶ/ር ንጉሴ አስረስ በመድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ከተሜነት የዕድገት መሰረት፣ የስልጣኔና የቴክኖሎጂ ሞተር በመሆኑ የለውጡ መንግስት ብልጽግና ለከተሜነት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ ስኬታማ ውጤቶች ማስመዝገብ መቻሉን ገልፀዋል።

ከተሜነት የስልጣኔና የቴክኖሎጂ መሰረት በመሆኑ ለብልፅግና ጉዞ ወሳኝ ነው ለዚህም ብልፅግና ፓርቲ የተረሳው ከተሞኔት ለኑሮ ምቹ ተስማሚ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑ ገልፀዋል።

ከተሞኔትን ከገጠር በማስተሳሰር በማሰናሰል የህብረተሰብ ተጠቃሚነት የሚረጋገጥባቸው ሁኔታዎች በመልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከተሞችን ማልማት ያስፈልጋል ብለዋል።

ሰባተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ሰላማዊና ነፃ ዲሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን
የለውጡ መንግስት ከተሞች በፕላን በመምራትና በማስተዳድር ለነዋሪዎቿ ምቹና ቀልጣፋ አገልገሎት ለመስጠት እንዲችሉ እየተሰራ እንደሆነ አንስተዋል።

መሰረተ ልማት በተገቢው የተሟላ እንዲሆን አስፈላጊውን ስራ በመስራት በፕላን መምራትና ማስተዳደር እንደሚገባ የገለፁት ዋና አስተዳዳሪው የከተሞች ምቹነትና ተስማማሚነት በማሳደግ የፈርጅ ለውጥ እንዲያመጡ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊና የከተሞች ፕላን ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይነህ አየለ የለውጡ መንግስት ባለፉት ዓመታት በተሰሩ ስራዎች ከተሞች የሚታወቁበትን ኃላ ቀርነት በማስወገድ ስኬታማ ተግባራት እየተሰራ መሆኑ ገልፀው ከተሞች በማስፋፋት፣ ለነዋሪዎቿ ምቹ ለኢንደስትሪና ለኢንቨስትመንት ማዕከል እንዲሆን ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ፈጣን ዕድገት አምጥቷል ሲሉ ተናግረዋል።

የዶቢ ታዳጊ መዘጋጃ ቤት አስፈላጊውን የምዘና መስፈርት በማሟላት የፈርጅ አምስት ከተማ በማግኘት ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጥ እውቅና ያገኘ ሲሆን ከተማዋን ለማሳደግ ሁሉም ባለድርሻ የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ውልጫፎ በበኩላቸው ባለፉት ስምንት ዓመታት በወረዳው የለውጡ መንግስት የሚያወረዳቸው ኢኒሼቲቮችን ውጤታማ በማድረግ የህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን ገልፀዋል።

ወረዳው በተፈጥሮ ፀጋ የታደለ ለቱሪዝም፣ለኢንቨስትመንት፣በውሃ ሀብት እምቅ ያለው ከመሆኑም በለይ በግብርና ዘርፍ ምርታማ በመሆን ለውጭ ገበያ የተለያዩ ምርቶችን እያቀረበ መሆኑ አንስተዋል።

ከተሞች በፍርጅ ጥናት በማጥናት ገጠርና ከተማን በሰናሰል ለህብረተሰቡ በቅርበት አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት እየተሰራ ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው የዶቢ ታዲጊ ማዘጋጃ ቤት አምስተኛ ታዳጊ መዘጋጃ ቤት በመሆን በመመስረቱ እንኳን ደስ አላቹህ ብለው ማዘጋጃ ቤቱ ለማልማትና ለማሳደግ ህብረተሰቡ የበኩሉን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

የመስቃን ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ማበዛሽ አህመድ እንዳሉት የዶቢ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት በወረዳው አምስተኛው ማዘጋጃ ቤት መሆኑን ገልፀው ሁሉም የአካባቢው ማህበረሰብ በፕላን መሰረት እንዲመራና ማዘጋጃ ቤቱ ለማልማት ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

በመጨረሻም የገቢ መሰብሰቢያ መርሃ ግብር የተካሄደ ሲሆን በአይነት፣ በጥሬ ገንዘብ እና ቃል የተገባ 28 ሚሊየን ብር እና ለማዘጋጃው የሚሆን 20 ሄ/ር መሬት በመሰብሰብ የእለቱ ፕሮግራም ለባለ ድርሻ አካላት እውቅና በመስጠት ተጠናቋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በተገኙበት በመስቃን ወረዳ የዶቢ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት ይፋዊ የምስረታና የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው።      ...
24/05/2026

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በተገኙበት በመስቃን ወረዳ የዶቢ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት ይፋዊ የምስረታና የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው።

ግንቦት 16/2018 (ቡታጅራ)

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በተገኙበት በመስቃን ወረዳ የዶቢ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት ይፋዊ የምስረታና የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ ዶ/ር ንጉሴ አስረስ፣ የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊና የከተሞች ፕላን ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይነህ አየለ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ መሰለ ጫካ ፣የምስራቅ ጉራጌ ዞን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ክብርት አለምፀሃይ ሽፈራው ፣የመስቃን ወረዳ ዋና አሰተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሀመድ ውልጫፎ ፣ የመስቃን ወረዳ ምክር ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ሁሴን ኤርሞሎ፣ የመስቃን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ መሀመድ ሳኒ ጨምሮ የክልል ፣የዞን አስተባባሪና አጠቃላይ አመራሮች ፣ የወረዳና ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የአካባቢው ማህበረሰብና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

በቡኢ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ አካል የሆነዉ የ"ቡና ጠጡ" ፕሮግራም በሁሉም ቤተሰብና መንደሮች አሁንም  ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።ግንቦት 16/2018 ዓ/ምበምስራቅ...
24/05/2026

በቡኢ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ አካል የሆነዉ የ"ቡና ጠጡ" ፕሮግራም በሁሉም ቤተሰብና መንደሮች አሁንም ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

ግንቦት 16/2018 ዓ/ም

በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡኢ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ቅስቀሳ አካል የሆነዉ የ"ቡና ጠጡ" መርሃ ግብር በከተማው በተለያዩ መንደሮችና በቤተሰብ ደረጃ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

ይህ በብልጽግና ህብረት እና በቤተሰብ ደረጃ የተከናወነው የሚገኘው የቡና ጠጡ መርሃ ግብር፤ ፓርቲው ባለፉት ዓመታት ያስመዘገባቸውን የልማትና የሰላም ስኬቶች ለህብረተሰቡ ለማስተዋወቅ ያለመ እንደሆነም ተመላክቷል።

በዛሬው ዕለትም በከተማ አስተዳደሩ በመብራት ሀይል ሠፈር የምርጫ ቅስቀሳና የቡና ጠጡ ፕሮግራም ተካሂዷል።

በፕሮግራሙ የፓርቲው አመራሮችና ደጋፊዎች በየአደረጃጀቶቹ በመገኘት የፓርቲውን የምርጫ ምልክት (የስንዴ ነዶ) እና ዕጩ ተወዳዳሪዎችን የማስተዋወቅ ስራ ሰርተዋል።

በዚህም "ኑ ቡና ጠጡ" መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉ የከተማዋ ነዋሪዎችና የፓርቲው አባላት ለፓርቲው ያላቸውን ድጋፍ የገለጹ ሲሆን፣ በቀጣይም ለሀገር ብልጽግናና ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ከፓርቲው ጎን እንደሚቆሙ አረጋግጠዋል።

የቡኢ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘላለም ባህሩ የቡኢ ከተማ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደምሰው ተሰራ፣ የቡኢ ከተማ አስተዳደር የብልፅግና ኢንስቴክሽን እና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ፅ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ባሉ የቡኢ ከተማ አስተዳደር አማካሪ ም/ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ንጉሴ ተክሌ እና ሌሎችም የአመራር አካላት ተገኝተዋል።

ዘገባው የቡኢ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ለተጨማሪ መረጃ
የፌስቡክ ገፃችን 👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100068066105775

#የቴሌግራም ፔጃችን👇
https://t.me/BueeGovermentcomunication35

#የቲክቶክ-ፔጃችን👇
https://www.tiktok.com/?_t=8rUU1rZG5aS&

#ኢንስታግራም https://www.instagram.com/bueegovrncommunication35?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

#የዋትሳፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VayIqyN6mYPDqXJHKL3t

#ዩትዩብ
https://youtube.com/?si=ScPXI4i65LSi9V6p

#የቲዊተር (X)👇
https://x.com/BueeGovrnComm35?t=FvbB7Xk926nDj7_qXadSWg&s=35

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን

8 ቀናት ብቻ ቀርተውታል7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ 8 ቀናት ብቻ ቀርተውታልድምፅዎ ወሳኝ ነው! ግንቦት 24 መሪዎን ለመምረጥ ዝግጁ ኖት?Ethiopian Broadcasting Corporatio...
24/05/2026

8 ቀናት ብቻ ቀርተውታል

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ 8 ቀናት ብቻ ቀርተውታል

ድምፅዎ ወሳኝ ነው! ግንቦት 24 መሪዎን ለመምረጥ ዝግጁ ኖት?

Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ምርጫ #ዴሞክራሲ #በምርጫብ #ኢትዮጵያ #ምርጫ #ዴሞክራሲ #በምርጫብቻ

በመምህር ደረጄ ፋንታ አስተባባሪነት የተገነባው የተማሪዎች መፀዳጃ ቤት ተመረቀ!!!ግንቦት 15/2018 ዓ.ምበደቡብ ሶዶ ወረዳ የዳሙ 3 ቁጥር 1 ትምህርት ቤት ለተማሪዎች የሚያገለግል ዘመናዊ...
23/05/2026

በመምህር ደረጄ ፋንታ አስተባባሪነት የተገነባው የተማሪዎች መፀዳጃ ቤት ተመረቀ!!!

ግንቦት 15/2018 ዓ.ም

በደቡብ ሶዶ ወረዳ የዳሙ 3 ቁጥር 1 ትምህርት ቤት ለተማሪዎች የሚያገለግል ዘመናዊ መፀዳጃ ቤት በመምህር ደረጄ ፋንታ አስተባባሪነት ተገንብቶ በዛሬው ዕለት የወረዳው አመራሮችና በባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተመርቋል።

መምህር ደረጄ ፋንታ ከወረዳው አስተዳደር ጋር በመግባባት በትምህርት ቤቱ የወንዶችና የሴት ተማሪዎች መፀዳጃ ቤት እጥረት መኖሩን በመገንዘብ 500 ሺህ ብር ከውጭ ዜጋ በማስተባበር እና ከአካባቢው ማህበረሰብ ከ300 ሺህ ብር በላይ በጥቅሉ ከ800 ሺ ብር በላይ ወጪ በማድረግ 8 ክፍሎች ያሉት አንድ የመፀዳጃ ብሎክ በማስገንባት ለትምህርት ቤቱ አስረክበዋል።

በተጨማሪም ወጣት ጴጥሮስ እንዳለ ከአካባቢው ማህበረሰብ በጋራ በመሆን ያስገነቡት የቅድመ መደበኛ ክፍል የምረቃው አካል ተደርጓል ።

መምህር ደረጄ ፋንታ በማህበረሰቡ ውስጥ ችግር ፈቺ የበጎ አድራጎት ስራዎችን በመስራት የሚታወቁ ሲሆን፣ በደቡብ ሶዶ ወረዳ ይህን አይነት በጎ ተግባር ሲያከናውኑ የመጀመሪያቸው እንዳልሆነም ተገልጿል።

በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ መስፍን አድማሱ ለተደረገው ችግር ፈቺ የበጎ አድራጎት ስራ መምህር ደረጄ ፋንታን አመስግነው፣ ስራው እንዲሳካ አስተዋፅኦ ላደረጉ የቀበሌው አስተዳደር፣ የትምህርት ቤቱ አመራርና የአካባቢው ማህበረሰብንም ጨምረው አመስግነዋል ።

አቶ መስፍን አድማሱ በንግግራቸው አቶ ደረጄ ፋንታ በሶዶ ምድር በተለያዩ ትምህርት ቤቶች የትምህርት ልማት ስራዎችን በመደገፍ የሚታወቁ ትጉ የልማት ሰው መሆናቸውን ጠቅሰው፣ በዳሙ 3 ቁጥር 2 ቤተ መፃህፍት፣ በሲቢስቶ እና በዛሬው የመፀዳጃ ቤት ግንባታ ላይ ያሳዩት አስተዋፅኦ የሚያስመሰግን መሆኑን ገልጸዋል።

በመጨረሻም በትምህርት ቤቱ ውስጥ 86 ቅድመ መደበኛ ተማሪዎች እየተማሩ መሆናቸውን በመጠቆም፣ የአካባቢው ማህበረሰብ፣ ባለሀብቶችና የትምህርት አመራሩ ለተማሪዎች የተሻለ የትምህርት አካባቢ ለመፍጠር ተጨማሪ የክፍል ግንባታ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርዋል።

የደቡብ ሶዶ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የትምህርት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ እንዳለ ቡልቡላ በበኩላቸው፣ ትምህርት ቤቱ ከተመሰረተ ጀምሮ በመንግስት ከሚመደበው ውስን በጀት በተጨማሪ የዳሙ 3 ማህበረሰብ ከፍተኛ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

“ትምህርት ለትውልድ” በሚል ንቅናቄ ባለፉት 3 እና 4 ዓመታት በርካታ የትምህርት ልማት ስራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰው፣ የዳሙ 3 ቁጥር 1 ትምህርት ቤት ለሌሎች ትምህርት ቤቶች ሞዴል የሚሆን ስራ እየሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል።

በተጨማሪም ዳሙ 3 ቀበሌ የተሻለ የትምህርት አመራር፣ ንቁ ማህበረሰብና የቀበሌ አመራር ያለበት ቀበሌ በመሆኑ የተማሪዎች ውጤት በተከታታይ እየተሻሻለ መምጣቱን ገልጸዋል።

“ዋና አላማችን ለተማሪዎች ምቹና ፅዱ የትምህርት አካባቢ በመፍጠር ከቤታቸው በተሻለ ሁኔታ ትምህርትን እንዲወዱ ማድረግ ነው” ያሉት ሀላፊው፣ ለዚህም የመማሪያ ክፍሎችን ፅዱና ለመማር ምቹ ማድረግ ቀዳሚ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።

በደቡብ ሶዶ ወረዳ የዳሙ 3 ቀበሌ አስተዳዳሪ አቶ ሽፈራው በበኩላቸው፣ የዳሙ 3 ቁጥር 1 ትምህርት ቤት ከተመሰረተ ጀምሮ የቀበሌው ህዝብ ከመንግስት ጎን በመቆም የትምህርት ስራው እንዲቀጥልና እንዲሻሻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ መሆኑን መስክረዋል ።

እንዲሁም ማህበረሰቡ በዳሙ 3 ቁጥር 2 ትምህርት ቤትና በቅድመ መደበኛ ትምህርት ላይም ተመሳሳይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በመጨረሻም የዳሙ 3 ቁጥር 1 ትምህርት ቤት ለረጅም ጊዜ አንገብጋቢ ችግር የነበረው ደረጃውን የጠበቀ የተማሪዎች መፀዳጃ ቤት በመገንባት ችግሩ እንዲቀረፍ ላደረጉት አቶ ደረጄ ፋንታ፣ ለትምህርት አመራሩና ለወረዳው አስተዳደር ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።

በመጨረሻም ትምርት ቤቱ የመነንግስት ኢኒሼቲቭ የሆነው ትምህርት ቤቶች ዲጂታላይዝ ለማድረግ ተማሪዎች የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የተሰራው ስራ ምልከታ ተደርጓል።

ዘገባው የደቡብ ሶዶ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው።

23/05/2026

ድምፆን ዋጋ አልባ የሚያደርጉ ምክንያቶች

በቡኢ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ አካል የሆነዉ የ"ቡና ጠጡ" ፕሮግራም በሁሉም ቤተሰብና መንደሮች አሁንም  ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።ግንቦት 15/2018 ዓ/ምበምስራቅ...
23/05/2026

በቡኢ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ አካል የሆነዉ የ"ቡና ጠጡ" ፕሮግራም በሁሉም ቤተሰብና መንደሮች አሁንም ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

ግንቦት 15/2018 ዓ/ም

በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡኢ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ቅስቀሳ አካል የሆነዉ የ"ቡና ጠጡ" መርሃ ግብር በከተማው በተለያዩ መንደሮችና በቤተሰብ ደረጃ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

ይህ በብልጽግና ህብረት እና በቤተሰብ ደረጃ የተከናወነው የሚገኘው የቡና ጠጡ መርሃ ግብር፤ ፓርቲው ባለፉት ዓመታት ያስመዘገባቸውን የልማትና የሰላም ስኬቶች ለህብረተሰቡ ለማስተዋወቅ ያለመ እንደሆነም ተመላክቷል።

በዛሬው ዕለትም በከተማ አስተዳደሩ በሰላም እና በንጋት ሠፈር የምርጫ ቅስቀሳና የቡና ጠጡ ፕሮግራም ተካሂዷል።

በፕሮግራሙ የፓርቲው አመራሮችና ደጋፊዎች በየአደረጃጀቶቹ በመገኘት የፓርቲውን የምርጫ ምልክት (የስንዴ ነዶ) እና ዕጩ ተወዳዳሪዎችን የማስተዋወቅ ስራ ሰርተዋል።

በዚህም "ኑ ቡና ጠጡ" መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉ የከተማዋ ነዋሪዎችና የፓርቲው አባላት ለፓርቲው ያላቸውን ድጋፍ የገለጹ ሲሆን፣ በቀጣይም ለሀገር ብልጽግናና ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ከፓርቲው ጎን እንደሚቆሙ አረጋግጠዋል።

የቡኢ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ በለጠ ጫካ ፣ምስራቅ ጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ብሩክታይት ፀጋዬ ፣ የቡኢ ከተማ አስተዳደር ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደበበ አዳነ ፣የቡኢ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘላለም ባህሩ ፣የምስራቅ ጉራጌ ዞን የብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ምክትል ኃላፊ አቶ አሰፋ ፈይሳ ፣የምስራቅ ጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ምክትልና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አዳነ ተሰማ ፣የቡኢ ከተማ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደምሰው ተሰራ፣ የቡኢ ከተማ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ሳቢራት ታጁዲን እና ሌሎችም የአመራር አካላት ተገኝተዋል።

ዘገባው የቡኢ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ለተጨማሪ መረጃ
የፌስቡክ ገፃችን 👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100068066105775

#የቴሌግራም ፔጃችን👇
https://t.me/BueeGovermentcomunication35

#የቲክቶክ-ፔጃችን👇
https://www.tiktok.com/?_t=8rUU1rZG5aS&

#ኢንስታግራም https://www.instagram.com/bueegovrncommunication35?igsh=YzljYTk1ODg3Zg==

#የዋትሳፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VayIqyN6mYPDqXJHKL3t

#ዩትዩብ
https://youtube.com/?si=ScPXI4i65LSi9V6p

#የቲዊተር (X)👇
https://x.com/BueeGovrnComm35?t=FvbB7Xk926nDj7_qXadSWg&s=35

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን

Address

Bu-I

Telephone

+251468830761

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡኢ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share