የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit

የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit public and government service
(3)

24/06/2026

#ፋና #ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ የባሕር በር ታሪካዊ መብትና የፍትህ ጥያቄ******************የኢትዮጵያ ሥልጣኔ ከባህር በሮቿ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው ሲሆን፣ ለቀይ ባህር በቀረበች ቁጥር የከፍታ ዘመኗ...
24/06/2026

የኢትዮጵያ የባሕር በር ታሪካዊ መብትና የፍትህ ጥያቄ
******************

የኢትዮጵያ ሥልጣኔ ከባህር በሮቿ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው ሲሆን፣ ለቀይ ባህር በቀረበች ቁጥር የከፍታ ዘመኗን ስታረጋግጥ ቆይታለች።

የኢትዮጵያ የህልውና ጥያቄ የሆነው የባህር በር ጉዳይ የሌላ ሀገር ግዛት የመውሰድ ጉዳይ አይደለም፤ በፍትሀዊነት መብቷን የመጠየቅ እንጂ፡፡ ለዚህ ማሳያ ደግሞ ከዲፕሎማሲ አንፃር አስፈላጊ አለም አቀፍ ድርጅቶች የተለያዩ መርሆችን አስቀምጠዋል።

በ1982 የፀደቀው የተባበሩት መንግስታት የባህር ሕግ ስምምነት (UNCLOS) የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ወደ ባህር የመድረስና የትራንዚት መብት እንዳላቸው ያስቀምጣል። ሆኖም ይህ መብት በጎረቤት ሀገራት ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት በማክበር እንዲፈጸም ይደነግጋል።

የአፍሪካ ህብረት በበኩሉ የአፍሪካ ሀገራት ሉዓላዊነትና ድንበር መከበርን እያጎላ በተመሳሳይ ጊዜ የክልል ትስስር፣ የንግድ ትብብር እና የጋራ ልማት እንዲጠናከር ያበረታታል።

የመንግስታቱ የልማት ድርጅት (UNCTAD) ደግሞ የባህር በር አልባ ሀገራት ከፍተኛ የመጓጓዣ ወጪ እንደሚሸከሙና ይህም የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነታቸውን እንደሚጎዳ ይገልጻል።

የዓለም ባንክም በምሥራቅ አፍሪካ የወደብ ተደራሽነት፣ የባቡር መስመሮች እና የንግድ ኮሪደሮች መጠናከር የክልሉን ኢኮኖሚ እድገት እንደሚያፋጥን ያሳያል።

ኢትዮጵያ ለወደብ አገልግሎት፣ ለትራንስፖርት እና ለሎጂስቲክስ በየዓመቱ ቢሊዮን ዶላሮችን የምታወጣ ሲሆን፤ የሕዝብ ቁጥሯ እየጨመረ እና ኢኮኖሚዋ እየሰፋ ባለበት ሁኔታ ደግሞ ይህ ወጪ የበለጠ እየጨመረ ይሄዳል።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከ95 በመቶ በላይ የውጭ ንግዷን በጅቡቲ ወደብ በኩል ታከናውናለች። ይህም በአንድ መስመር ላይ ያለ ከፍተኛ ጥገኝነት ነው።

ከ130 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ በዓለም ላይ በሕዝብ ብዛት ትልቋ የባህር በር አልባ ሀገር ናት። የራሷ ወደብ ሳይኖራት ለውጭ ንግድ እና ለሎጂስቲክስ አገልግሎት በጎረቤት ሀገራት ወደቦች ላይ ተመርኩዛ ቆይታለች።

ይህም በየዓመቱ ቢሊዮን ዶላሮች የሚያስወጣ ከመሆኑም በላይ የንግድ፣ የኢኮኖሚ፣ የብሔራዊ ደህንነት እና የቀጠናዊ መረጋጋት ጉዳይ ሆኖ ቀጥሏል።

የባህር በር ማለት አንድ ሀገር ከዓለም አቀፍ የባህር ንግድ መስመሮች ጋር በቀጥታ የምትገናኝበት መዳረሻ ነው።

ዛሬ ከዓለም አቀፍ ንግድ 80 በመቶ በላይ በባህር መንገድ የሚከናወን በመሆኑ፣ ወደብ ለሀገራት የኢኮኖሚ መተንፈሻ በር ተደርጎ ይታያል።

የባህር ማጓጓዣ የአለም ኢኮኖሚ ፍፁም የጀርባ አጥንት ሲሆን፣ በየአመቱ ከ11 ቢሊዮን ቶን በላይ ጥሬ እቃዎች፣ ሃይል እና የፍጆታ እቃዎች ይንቀሳቀሳል።

ውቅያኖሶች 70% የሚሆነውን የምድርን ገጽ ስለሚሸፍኑ መርከቦች ከባድ እና ግዙፍ ጭነትን ረጅም ርቀት ለማንቀሳቀስ በጣም ወጪ ቆጣቢ እና ቀልጣፋ መንገድ ይሰጣሉ።

ኢትዮጵያ የባህር ባለቤት ስትሆን ተጠቃሚዋ እሷ ብቻ አትሆንም። የጎረቤት ሀገራት ወደቦች ተጨማሪ ገቢ ያገኛሉ፤ ንግድ ይስፋፋል፤ መሠረተ ልማት ይጠናከራል፤ የቀጠናው የኢኮኖሚ ትስስርም ይጨምራል።

ይህም የዜሮ ድምር ጨዋታ ሳይሆን ሁሉም ተጠቃሚ የሚሆኑበት የጋራ ልማት እድል ነው።

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ፖለቲካ አይደለም፤ የመላው ኢትዮጵያዊ የህልውና ጉዳይ እንጂ። ይህ ጥያቄ በጦርነት ሳይሆን በዲፕሎማሲ፣ በህግ እና በጋራ ጥቅም መርህ ሊመለስ የሚችል ነው።

በልዩ እሸቱ

24/06/2026

#በምስራቅ መስቃን ወረዳ በፌደራል ተቋማት ደረጃ በበጎ ፈቃድ የተገነቡ መኖሪያ ቤቶች የተጠቃሚው ቤተሰቦች በ
ማስረከብ መርሐ ግብር ላይ ለመጡ እንግዶች ዱዓ ሲያደርጉ።

በምስራቅ መስቃን ወረዳ በፌድራል ተቋማት ደረጃ በበጎ ፈቃድ የተገነቡ መኖሪያ ቤቶች ለተጠቃሚ ቤተሰቦች የማስረከብ መርሐ ግብር ተካሄደ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ሰኔ 17፣2018 ዓ...
24/06/2026

በምስራቅ መስቃን ወረዳ በፌድራል ተቋማት ደረጃ በበጎ ፈቃድ የተገነቡ መኖሪያ ቤቶች ለተጠቃሚ ቤተሰቦች የማስረከብ መርሐ ግብር ተካሄደ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰኔ 17፣2018 ዓ/ም {እንሴኖ}

በፌድራል የሠላምና ፍትህ ተቋማት ትብብር በምስራቅ ጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ በክረምት በበጎ ፍቃድ የተገነቡ 9 መኖሪያ ቤቶች ለተጠቃሚ ቤተሰቦች የማስረከብ መርሀ ግብር ተካሄደ።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ ዶ/ር መሀመድ ሰብራላ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት በዛሬው መርሃ ግብር ለተገኙ እንግዶች እንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው፣የፓርቲያችን የሰው ተኮር የሆነው የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በወረዳችን ለዘጠኝ መኖሪያ ቤት ለሌላቸው ለችግር ተጋላጨ ለሆኑ ዜጎች በአዲስ መልክ ገንብቶ ማስረከቡ ለፌድራል ተቋማት ምስጋና አቅርበዋል።

የፌድራል ፍትህ ሚኒስትር ሀና አርዓያ ስላሴን በርክክብ መርሃ ግብር ወቅት እንደገለፁት በጎ ፍቃድ ተቋማት በክርምት ወቅት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየፈፀመ ይገኛል ያሉ ሲሆን አሁን በዚህ አካባቢ በአዲስ መልክ የተገነቡት ቤቶች ለዘመናት ችግራችንን ፈቶላቸዋል ሲሉ ገልፀዋል።

በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ከተከናወኑ የልማት ሥራዎች መካከል የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች አዲስ ግንባታ ሥራ አንዱ ሲሆን በዚህም ብዙዎች ተጠቃሚ ሆነዋል ሲሉ ሚኒስትር ገልፀዋል።

መኖርያ ቤት የሌላቸው በደሳሳ ጎጇቸው ለጸሐይና ዝናብ ተጋልጠው ለሚኖሩ ዜጎች ተቋሙ ደራሽ መሆኑ አስታውሰዋል፡፡

የፌድራል ተቋማቱ በክርምት በጎ ፍቃድ በርካታ ስራዎች መከናወኑ ገልፀው በቀጣይነት ባለው መልኩ እንደሚከናወን ገልፀዋል፡፡

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው እንደገለፁት የፌደራል ተቋማት በክርምቱ ለተጠቃሚዎች የተደረገው ጎጇቸው ለዝናብ፣ለጸሐይና ለመጥፎ ሽታ ተጋልጠው በችግር ውስጥ ይኖሩ እንደነበር ገልጸው፣ በአሁኑ ወቅት በበጎ ፍቃደኛ ቤታቸው በአዲስ መልክ ተሰርቶ መረከባቸውን ተናግረዋል።

የበጎ ፍቃድ ተጠቃሚዎች እንደተናገሩት የተደረገልን ድጋፍ ጠያቂና ደጋፊ ወገን እንዳለኝ ያክል ተሰምቶኛል ያሉት ተጠቃሚዎች፣በዚህም ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

"ከሰው እኩል በደስታ መኖር ጀምሬያለሁ" ያሉት ወይዘሮ እጅጋየሁ "የበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ የነበረብንን ችግር ከመፍታት ባለፈ የዘመናት ከሰው እኩል አድርጎናል" ብለዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ የፌድራል ፍትህ ሚኒስትር ሀና አርዓያ ስላሴን ጨምሮ የፌድራል የሰላምና የፍትህ ተቋማት፣የክልል፣የዞን፣የወረዳ አመራሮች፣የሀገር ሸማግሌዎች፣
የሀይማኖት አባቶች፣ወጣቶች፣
የአካባቢው ማህበረሰብ እና ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል።

ዘገባው የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው።

"ሀገርን መገንባት የጋራ ኃላፊነት ነው። መንግሥት ብቻውን ሊያደርገው አይችልም፤ ገበያው ብቻውን ሊያከናውነው አይችልም፤ ማኅበረሰባችንም ቢሆን ብቻውን ሊወጣው አይችልም። ዕድገት የሁላችንንም ...
24/06/2026

"ሀገርን መገንባት የጋራ ኃላፊነት ነው። መንግሥት ብቻውን ሊያደርገው አይችልም፤ ገበያው ብቻውን ሊያከናውነው አይችልም፤ ማኅበረሰባችንም ቢሆን ብቻውን ሊወጣው አይችልም። ዕድገት የሁላችንንም ተሳትፎ ይጠይቃል።"

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው አዲስ መረጃ ዛሬ ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምሮ ለሕዝብ ይፋ ሊደረግ ነውሰኔ 17/2018የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውንና እጅግ ወሳኝ የሆነውን...
24/06/2026

በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው አዲስ መረጃ ዛሬ ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምሮ ለሕዝብ ይፋ ሊደረግ ነው

ሰኔ 17/2018

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውንና እጅግ ወሳኝ የሆነውን አዲስ መረጃ ዛሬ ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምሮ ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡

ኮሚሽኑ የሚያስተላልፈው ይህ አዲስ መረጃ በኢትዮጵያ በሚገኙ ሁሉም መገናኛ ብዙሃን አማካኝነት በቀጥታ ስርጭት ለሕብረተሰቡ ተደራሽ እንደሚደረግ ታውቋል፡፡

መላው የሀገራችን ሕዝብና ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ይህንን ታሪካዊና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን የኮሚሽኑን መግለጫና አዲስ መረጃ ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምሮ በመገናኛ ብዙሃን በቀጥታ ስርጭት እንዲከታተሉ ጥሪ ቀርቧል፡፡

AMN

24/06/2026

በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው አዲስ መረጃ ዛሬ ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምሮ ለሕዝብ ይፋ ሊደረግ ነው
*******************************

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውንና እጅግ ወሳኝ የሆነውን አዲስ መረጃ ዛሬ ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምሮ ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡

ኮሚሽኑ የሚያስተላልፈው ይህ አዲስ መረጃ በኢትዮጵያ በሚገኙ ሁሉም መገናኛ ብዙሃን አማካኝነት በቀጥታ ስርጭት ለሕብረተሰቡ ተደራሽ እንደሚደረግ ታውቋል፡፡

መላው የሀገራችን ሕዝብና ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ይህንን ታሪካዊና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን የኮሚሽኑን መግለጫና አዲስ መረጃ ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምሮ በመገናኛ ብዙሃን በቀጥታ ስርጭት እንዲከታተሉ ጥሪ ቀርቧል፡፡

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የ2018 ዓም ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም አስጀመሩ ሰኔ 17/2018የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በከም...
24/06/2026

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የ2018 ዓም ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም አስጀመሩ

ሰኔ 17/2018
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በከምባታ ዞን ዱራሜ ከተማ በዶክተር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ ሆስፒታል ግቢ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አስጀምረዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት በክልሉ ከ530 ሚሊየን በላይ ችግኞች ለተከላ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።

እስከ ሐምሌ 25/2018 ባሉት ቀናት በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ተግባራዊ ይሆናል ብለዋል።

የአረንጓዴ አሻራ ሀገርን ከሚለውጡ ፕሮግራሞች መካከል አንዱ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ይህም በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚከሰቱ ችግሮችን ለመቅረፍ የላቀ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።

የአረንጓዴ አሻራ ለምግብነት፣ለመድሀኒትነት፣ለቁሳቁስ መስሪያነት እና ለሌሎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እየተተከሉ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለያዩ ጊዜያት እየተተከሉ ያሉ ችግኞች የጽድቀት መጠን እየጨመረ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቅሰዋል።

የክልሉ ህዝብ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ላይ በንቃት እየተሳተፈ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህም የከርሰ ምድር እና የገጸ ምድር የውሃ አካላት መጨመር ስለመስተዋሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል።

የክልሉ ህዝብ እስከ ሐምሌ 30/2018 በዘመቻ ለሚካሔደው የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ አቅርበዋል።

በችግኝ ተከላ ፕሮግራሙ የክልል፣ የዞን እና የልዩ ወረዳ ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል በማለት የዘገበው የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት የ2018 ዓም የመኸር ወቅት የተቀናጀ የግብርና ስራዎች የንቅናቄ መድረክ እየተካሔደ ነው።ሰኔ 17/2018በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብ...
24/06/2026

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት የ2018 ዓም የመኸር ወቅት የተቀናጀ የግብርና ስራዎች የንቅናቄ መድረክ እየተካሔደ ነው።

ሰኔ 17/2018
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ሴክተር የ2018 ዓም የመኸር ወቅት የተቀናጀ የግብርና ስራዎች የንቅናቄ መድረክ እየተካሔደ ይገኛል።

የተቀናጀ ግብርና ትጋት ለላቀ ምርታማነት በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሔደ ያለው የመኸር ወቅት የግብርናው ሴክተር የንቅናቄ መድረክ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ጉልህ ሚና እንዳለው ተጠቁሟል።

23/06/2026

Address

Butajira

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit:

Share