17/03/2026
" "
ሁላችንም የባለ አሻራዎቻችን አደራ አለብን፤ ሲያመልጡን የሚቆጩን ጀግኖች እንዲኖሩን አንሻምና ላነፁት ታሪክ፥ ላስቀመጡልን ቅርስ፥ ላተረፉልን ስም፥ ለተጠራንበት የወል ስም ዛሬ ላይ እናወድሳቸው🙏🙏🙏
ሁሉም ዘመን የየራሱ ባለ አሻራ አለው፤ በታሪክ አጋጣሚ ብዙ የምናወድሳቸውና በቁማቸው ቀን የምናመሰግናቸው ብዙ ባለ አሻራዎች አሉን።
ቼቼ ጳውሎስና ሉ ፕሮሞሽን በጋራ በመሆን የፊታችን እሁድ መጋቢት 13/2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት በከተማችን ስመ-ጥር አዳራሽ ሴንትራል ሆቴል ዐ5 ለከተማችን ሐዋሳ በሙዚቃውና በእግርኳሱ ዘርፍ አሻራቸውን ማኖር የቻሉ ጀግኖችን ልናወድስ እነሆ ቀጠሮ ይዘናል።
ይህ መወድሰ-ጀግና ፕሮግራማችን ተከታታይነት ያለው ሲሆን እንደ መጀመሪያ ዙር በከተማችን አልፎም በሃገራችን ሰልሶም በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ሐዋሳችንን በጉልህ ማስጠራት የቻሉ የሁለት ዘርፍ ማለትም የሙዚቃውና የእግርኳሱ ሌጀንዶችን ይዘክራል።
በዕለቱ ታላላቅ የመንግስት ባለስልጣናት፥ የድንገተ-ፈንጠዚያ እንግዳ (surprise guest), የሃገር ሽማግሌዎች፥ ታዋቂ ቲክቶከሮችና የሲዳማ ባህላዊ ምግቦች ይቀርባሉ።
በሙዚቃው
👉ድምፃዊ ቶኪቻው
👉ድምፃዊ ማሚላና
👉ድምፃዊ ኪቺኒ ይገኙበታል
በእግርኳሱ ዘርፍ
👉አዳነ ግርማ
👉ሽመልስ በቀለ
👉ሲሳይ ባንጫ እኚህን ጀግኖቻችንን እናወድሳለን❤❤❤
የሚሰራን ማወደስ ለመፃኢው ትውልድ መንገድ ጠራጊ ነውና በአዎንታዊነት ተሞልተን ሐዋሳችን ላይ በአይነኬ አሻራቸው ምስል ከሳች የሆነ ታሪክ የሰሩ ብዙዎች አሉና በቀናነት ተሞልተን በተሰላ የጊዜ ረድፍ ሁሉንም ለማወደስ ጊዜና ዕድል ይስጠን🙏🙏🙏
ለብዙሃን እንዲደርስ ሼር በማድረግ አብራችሁን አመስግኑ🙏🙏🙏
" የምስጋና መሰናዶ ስለሆነ መግቢያ በነፃ መሆኑን ልንገልፅ እንወዳለን"
#ሐዋሳ
#ቶኪቻው #ማሚላ #ኪቺኒ
#ሲዳማ