Addis mereja

Addis mereja Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Addis mereja, Social Media Agency, Wellega, Nek'emte.

08/04/2026

“የታጋሹ ተማሪ”

አንድ ጊዜ ሳሙኤል የተባለ ተማሪ ነበር። እርሱ ትምህርቱን በጣም ይወድ ነበር፣ ግን በክፍሉ ሁልጊዜ የመጨረሻ ይሆን ነበር። ጓደኞቹ ይስቁበት ነበር፣ “አንተ አትችልም” ይሉት ነበር።

ነገር ግን ሳሙኤል አልተወም። በየቀኑ ትንሽ ትንሽ ይማር ነበር፣ ጥያቄዎች ይጠይቅ ነበር፣ ስህተቱንም ይቀበል ነበር።

ጥቂት ወራት ካለፉ በኋላ፣ የፈተና ቀን ደረሰ። ሁሉም ተማሪዎች ተፈተኑ። ውጤቱ ሲወጣ፣ ሁሉንም አስደነቀ—ሳሙኤል ከክፍሉ አንደኛ ሆኖ ነበር!

ጓደኞቹ ተገርመው “እንዴት ቻልክ?” ብለው ጠየቁት።
እርሱም እንዲህ አለ፦ “ትንሽ ትንሽ እርምጃ ትልቅ ለውጥ ያመጣል። እኔ አልተውኩም።”

መልእክት: ትዕግሥት እና ቀጣይ ጥረት ማንኛውንም ሰው ወደ ስኬት ያደርሳል።

የ114 ህጻናትን ልብ መጠገን የቻለው ዶ/ርዶ/ር ሺቢቆም ታምራት በኢትዮኢስታምቡል አጠቃላይ ሆስፒታል ላይ ትልቅ ስራ እየሰራ የሚገኝ ኢትዮጵያ የምትመካበት ታላቅ ባለሙያ ሲሆን ሆስፒታሉ ለህጻ...
31/03/2026

የ114 ህጻናትን ልብ መጠገን የቻለው ዶ/ር

ዶ/ር ሺቢቆም ታምራት በኢትዮኢስታምቡል አጠቃላይ ሆስፒታል ላይ ትልቅ ስራ እየሰራ የሚገኝ ኢትዮጵያ የምትመካበት ታላቅ ባለሙያ ሲሆን ሆስፒታሉ ለህጻናት እየሰጠ በሚገኘው ነጻ የልብ ህክምና የ114 ህጻናትን ልብ በመስራት ታሪክ እየሰራ ይገኛል።

ዶ/ር ሺቢቆም የብዙ ህጻናትን ህይወት እየታደክ ስለሆነ እናመሠግንሀለን🙏

31/03/2026

የውጪ ሀገራት ወሬዎች

#ጀርመን

በጀርመን ከሚኖሩ ስደተኞች 80 በመቶዎቹ ወደ አገራቸው እንደሚሸኙ መራሄ መንግስት ፍሬድሪክ ሜርዝ ተናገሩ፡፡

ሶሪያውያኑ ስደተኞች በመጪዎቹ 3 አመታት ከጀርመን ወደ አገራቸው ይሸኛሉ መባሉን ቢቢሲ ፅፏል፡፡

መራሄ መንግስት ሜርዝ 80 በመቶዎቹ ሶሪያውያን ስደተኞች በ3 አመታት ጊዜ ወደ አገራቸው እንደሚሸኙ እወቁልን ያሉት ከሶሪያው ጊዜያዊ ርዕሰ ብሔር አህመድ አልሻራ ጋር በበርሊን ከተነጋገሩ በኋላ ነው ተብሏል፡፡

ብዙዎቹ ሶሪያውያን ስደተኞች ጀርመን የገቡት በአገራቸው ተቀስቅሶ የነበረው ውስብስብ የእርስ በርስ ጦርነት በተፋፋመበት ወቅት ነበር፡፡

አሁን ስደተኞቹን ከጀርመን መመለስ ይጀመራል ቢባልም ዝርዝሩ ገና አልታወቀም፡፡

ሶሪያ በአሁኑ ወቅት ከ10 ዓመት በፊት ከነበረው በእጅጉ የተሻለ ፀጥታ እንደሚስተዋልባት መረጃው አስታውሷል፡፡

#አሜሪካ

አሜሪካ በኢራን ኢስፋሐን ከተማ በሚገኝ የከፍተኛ ጦር መሳሪያዎች እና ተተኳሾች ማከማቻ የምድር ውስጥ ዋሻ ላይ ከባድ የቦምብ ድብደባ መፈፀሟ ተሰማ፡፡

ማከማቻው የሚገኝበት ዋሻ በምሽግ ደርማሽ ቦምብ መመታቱን ዎል ስትሪት ጆርናል ፅፏል፡፡

የኢስፋሐኑ የታላላቅ የጦር መሳሪያዎች ማከማቻ ተመትቷል ስለመባሉ ከኢራን ሹሞች በኩል የተሰማ አስተያየት የለም፡፡

በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ በኢራን ተተኩሷል በተባለ የሚሳየል ስብሰባሪ በ4 ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል፡፡

በዛው በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ የኩዌትን ሰንደቅ ዓላማ የምታውለበልብ የነዳጅ መጫኛ መርከብ በኢራን ድሮን ተመትታ በእሳት ተያይዛ እንደበር ተሰምቷል፡፡

ኢራን ወደ ኢሚሬትስ ጥቃት መሰንዘሯን እንደቀጠለች ተነግሯል፡፡

የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ባለስልጣናት ጋር በብርቱ እየተነጋገርን ነው ቢሉም የኢራን ሹሞች ሐሰት ነው ማለታቸውን ቢቢሲ ፅፏል፡፡

#ናይጀርያ

በናይጀርያ ፕላቱ ግዛት ጆስ ከተማ ከትናንት አንስቶ የ48 ሰዓታት የሰዓት እላፊ ስራ ላይ ዋለ፡፡

በከተማዋ የ48 ሰዓታት የሰዓት እላፊ ስራ ላይ የዋለው ታጣቂዎች በአንድ መጠጥ ቤት ላይ ባደረሱት የእሩምታ ተኩስ ጥቃት 12 ሰዎችን መግደላቸውን ተከትሎ እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡

ጥቃቱ ቀደም ሲል ተገድለዋል ለተባሉ 10 ሰዎች በቀል ነው ተብሏል፡፡

ከተማዋ ለወትሮውም ከፍተኛ የፀጥታ መደፍረስ ከሚታይባቸው አንዷ እንደሆነች ተጠቅሷል፡፡

የፕላቱ ግዛት አስተዳደር ወንጀል ፈፃሚዎቹ ተይዘው በአፋጣኝ ለህግ እንዲቀርቡ ማዘዙ ተሰምቷል፡፡

በጆስ ከተማ መጠጥ ቤት ድንገት ደራሹ ጥቃት ከመፈፀሙ አስቀድሞ በየማህበራዊ ድረ ገፅ ዛቻ ሲሰነዘር እንደነበር መረጃው አስታውሷል፡፡

#አሜሪካ

የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ በዛቻ ላይ ዛቻ እያነባበሩባት ነው፡፡

ትራምፕ ኢራን ፈጥና ካልተስማማች ሁሉንም የውሃ ማጣሪያዎቿን አወድማለሁ ማለታቸውን አልጀዚራ ፅፏል፡፡

የውሃ ማጠራቀሚያዎቹ በሙሉ አይቀሩኝም ብለዋል የአሜሪካው ፕሬዘዳንት፡፡

ቀደም ሲል ትራምፕ ኢራን የሆርሙዝን የባህር መተላለፊያ ሰርጥ ካልከፈተች የኤሌክትሪክ አውታሮቿ አይተርፉኝም ሲሉ ሰንብተዋል፡፡

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮም ኢራን ሆርሙዝን በዚያም ሆነ በዚህ መክፈቷ አይቀርም ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡

በአንድ በኩል በኢራን ላይ ማስጠንቀቂያቸውን የሚያግተለትሉት ትራምፕ በሌላ በኩል ከኢራን ጋር የሚካሄደው ንግግር ታላቅ እርምጃ እያሳየ ነው ብለዋል፡፡

የኢራን ሹሞች ከአሜሪካ ባለስልጣናት ጋር የተደረገ አንዳችም ንግግር የለም ሲሉ ቆይተዋል፡፡

የሆርሙዝ ሰርጥ (Strait of Hormuz) አሁን የግጭቱ ማዕከል ሆኗል፤ ተንታኞች እንደሚገምቱት ትራምፕ ወደ መጠነ ሰፊ ጦርነት ሳይገቡ “ቆራጥ ድል” (Decisive victory) ለመቀዳ...
26/03/2026

የሆርሙዝ ሰርጥ (Strait of Hormuz) አሁን የግጭቱ ማዕከል ሆኗል፤ ተንታኞች እንደሚገምቱት ትራምፕ ወደ መጠነ ሰፊ ጦርነት ሳይገቡ “ቆራጥ ድል” (Decisive victory) ለመቀዳጀት ሲሉ፤ ለዓይን የሚማርክና አደጋው አነስተኛ የሆነ ወታደራዊ እርምጃ ሊፈልጉ ይችላሉ።

ለዚህም ዋነኛው አማራጭ የካርክ ደሴትን (Kharg Island) በመቆጣጠር ድል ማወጅና የተኩስ አቁም ጥሪ ማቅረብ ነው።

ነገር ግን አንድ ችግር አለ፤ ኢራን ይህን በጭራሽ አትቀበለውም። ካርክ ደሴት ከኢራን የነዳጅ ኤክስፖርት 90 በመቶውን (90%) የምትሸፍን በመሆኗ፤ ደሴቲቱን መያዝ ለትራምፕ ድል ቢሆንም ለኢራን ኢኮኖሚ ግን ፍጹም ውድመት (Devastation) ነው።

ይህንን ግዛት ይዞ ለመቆየት መሞከር ሁኔታውን በፍጥነት ወደ ተወሳሰበና አስከፊ ደረጃ ሊያሸጋግረው ይችላል።

“ፈጣን ድል” የመሰለው ዕቅድ ወደ ከፍተኛ የሕዝብ ፊት ውድቀት (Public failure) ሊቀየር ይችላል። ምንጭ፦ አልጀዚራ (Al Jazeera)

🇨🇩🇷🇼 ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ሩዋንዳ የኢኮኖሚ ውህደት ማዕቀፍ ለመጀመር ተስማሙ 🤝 ሀገራቱ ሰኔ 27 ቀን በፈረሙት የሰላም ስምምነት መሠረት፤ የቀጣናዊ ኢኮኖሚ ውህደት ማዕቀፍ መር...
02/08/2025

🇨🇩🇷🇼 ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ሩዋንዳ የኢኮኖሚ ውህደት ማዕቀፍ ለመጀመር ተስማሙ

🤝 ሀገራቱ ሰኔ 27 ቀን በፈረሙት የሰላም ስምምነት መሠረት፤ የቀጣናዊ ኢኮኖሚ ውህደት ማዕቀፍ መርሆዎች ላይ መገባባታቸውን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ገልጿል፡፡

🔸 ሀገራቱ በኃይል፣ በመሠረተ ልማት፣ በማዕድን ቁፋሮ፣ በብሔራዊ ፓርክ አስተዳደር፣ በቱሪዝም እና በሕብረተሰብ ጤና በመተባበር በምሥራቅ እና በመካከለኛው አፍሪካ ቀጣና የኢኮኖሚ እድገትን ያፋጥናሉ ሲል መግለጫው አመላክቷል፡፡

የሰላም ስምምነቱ ትግበራ ተቆጣጣሪ የጋራ ኮሚቴ የመጀመሪያ ስብሰባን ተከትሎ ባወጣው መገለጫ፤ "የደህንነት እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማስቀጠል ትርጉም ያላቸው እርምጃዎችን እየወሰዱ ነው" ብሏል፡፡

በሳምንቱ ዋሽንግተን ላይ የተደረጉ ስብሰባዎች ዓላማዎች፦

🟠 በደህንነት ጉዳዮች ቅንጅትን ማጠናከር፣
🟠 የረጅም ጊዜ መረጋጋት እና ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ፣
🟠 በቀጣናው ያለውን "የላቀ ኢኮኖሚያዊ አቅም" ማውጣት፡፡

የወባ በሽታበደቡብ የሀገሪቱ ክፍል የወባ በሽታ ወረርሽኝ በሚመስል መልኩ በጣም ብዙ ሰው እየሞተ ነው። በወላይታ ብቻ በቀን ከ40-50 ሰው እየሞተ መሆኑን የህክምና ባለሙያዎች ገልፀውልኛል። ...
20/10/2024

የወባ በሽታ

በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል የወባ በሽታ ወረርሽኝ በሚመስል መልኩ በጣም ብዙ ሰው እየሞተ ነው። በወላይታ ብቻ በቀን ከ40-50 ሰው እየሞተ መሆኑን የህክምና ባለሙያዎች ገልፀውልኛል። ይህ ቁጥር በቀን የሚሞተውን በትክክል ላይገልፅ ይችላል፣ምክንያቱም በሽታው ከቁጥጥር ውጪ እየሆነ ስለመጣ በተለይ በገጠራማው ክፍል በርካታ ሰዎች ሊሞቱ እንደሚችሉ ጠቁመዋል። የህክምና ቁሳቁስ እና የመድኃኒት አቅርቦት እጥረት በመፈጠሩ የሞት ቁጥሩ እንዲጨምር አድርጓል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በስልጤ፣በከምባታ፣ በጉራጌ ዞኖች እንዲሁም በምስራቅ ወለጋ እና ዙርያው ወረርሽኙ ተባብሷል ብለዋል።
የክልሉ ጤና ቢሮ በበኩሉ ከ1.2ሚሊዮን በላይ አጎበር ለማሰራጨት እየሰራሁ ነው ብሏል።

በአንድ ሳምንት ብቻ ከ51 ሺህ በላይ የወባ ህሙማን ቁጥር ተመዝግቧል " - የአማራ ክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

በአማራ ክልል በአንድ ሳምንት ብቻ ከ51 ሺህ 650 በላይ የወባ ህሙማን ቁጥር መመዝቡን የአማራ ክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

በክልሉ 40 ወረዳዎች 72 በመቶ የሚሆነው የወባ ስርጭት እንደሚሸፍኑም የኢንስቲትዩቱ የወባ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ዳምጤ ላንክር የገለፁ ሲሆን የበሽታው ስርጭት አሳሳቢ በመሆኑ ልዩ ትኩረት እንደሚያስፈልገው አስረድተዋል።

የወባ በሽታ ስርጭት በክልሉ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ እንደሚገኝ የገለፁት አስተባባሪው የ2017 በጀት ዓመት በባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 65.8 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ጠቁመዋል።

EBS TV Vs ኮንታ ዞንከኮንታ ዞን አስተዳደር የተላለፈ መልዕክትስለ አካባቢያችን በተሳሳተና ተገቢነት በሌለ አኳሃን በተለያዩ ሚዲያ አውታሮች የሚደረጉ አሉታዊ ድርጊቶች እንዲቆሙና እንዲታረ...
15/10/2024

EBS TV Vs ኮንታ ዞን

ከኮንታ ዞን አስተዳደር የተላለፈ መልዕክት

ስለ አካባቢያችን በተሳሳተና ተገቢነት በሌለ አኳሃን በተለያዩ ሚዲያ አውታሮች የሚደረጉ አሉታዊ ድርጊቶች እንዲቆሙና እንዲታረሙ ከኮንታ ዞን አስተዳደር የተላለፈ መልዕክት

የኮንታ ዞን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ውስጥ ከሚገኙ ዞኖች አንዱ ሲሆን ዞኑ ከአዲስ አበባ በጅማ በኩል 450 ኪ.ሜ ርቀት ሲኖረው በሰሜን በኩል ከኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን፣ በምስራቅ ከዳዉሮ ዞን፣ በምዕራብ ከከፋ ዞን እና በደቡብ በኩል ደግሞ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ጋር ይዋሰናል፡፡

ኮንታ ከሀገራችን ከሁሉም አካባቢዎች በተለያየ አጋጣሚ የመጡ ብሄር ብሄረሰቦች ያለአንዳች ልዩነት ለዘመናት በሰላምና በፍቅር ተከባብረው በጋራ የሚኖሩባትና ሰርተው ያተረፉባት፣ ኖረው ወልደው የከበሩባት የብዙኃን እናት ናት፡፡

የኮንታ ማህበረሰብ እንግዳ ተቀባይ የሆነ ቸር፣ደግና የዋህ ህዝብ መሆኑን እግር ጥሏቸው ለአንድ ቀን እንኳን ደርሰው የተመለሱ አካላት የሚመሰክሩት እውነታ ነው፡፡

ህዝቡ ሰላም ወዳድ የሆነ፣ከራሱ በላይ ለሌላው ሰላምና ደህንነት አብዝቶ የሚጨነቅ፣ ገራገር የመልካም እሴት ተምሳሌት የሆነ ህዝብ ነው፡፡

አካባቢያችን ኮንታ እንደ ሌሎቹ የሀገራችን አካባቢዎች ሁሉ የበርካታ ባህላዊ፣ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ሀብቶች የሚገኙበትና በሀገር መሪ አንደበት ጭምር "ኮንታ በምድር ላይ ከስዕል ውጭ ገነት የሚታይበት ምድር"መሆኑ ተመስክሮ ከአካባቢው ተፈጥሮ ጋር የሚሄዱ ትላልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች እየተገነባ ያለ አካባቢ ናት፡፡

ከማህበረሰባችን መልካም እሴትና ከአካባቢያችን ተፈጥሮ ሀብት ክምችት መነሻ የሀገር መሪዎች የትኩረት ማዕከል በመሆን የገበታ ለሀገር አካል የሆነው የኮይሻ ገበታ ለሀገር ፕሮጀክት፣ የጨበራ ዝሆን ዳና ሎጅ የሚገኝበት፣ የጨበራ ጩርጩራ ብሄራዊ ፓርክና በውስጡ የአፍሪካ ግዙፉ ዝሆን መገኛ፣ ከህዳሴ ግድብ ቀጥሎ ከፍተኛ የሆነና ሲጠናቀቅ 1,860 ሜጋ ዋት ማመንጨት የሚችል የኮይሻ ኃ/ኤ/ፓ/ ግድብ ያለበት አረንጓዴና ለምነት ከአመት አመት የማይለየው ውብ አካባቢ ነው፡፡

ኮንታ ስካይ ላይት የመሳሰሉ ትላልቅ የሆቴል ድርጅቶች የሚገኙበትና የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ዓመቱን ሙሉ የሚመላለሱበት የቱሪስት መዳረሻ የሆነ ከባቢ ነው፡፡

ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአንድ የአካባቢያችን አርሶ አደር በቃላት አገላለጽ ጉድለት መነሻ የተላለፈው መልዕክት በተሳሳተ መንገድ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ወጥቶ ብዙዎች ሲቀባበሉ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

ይህ ግለሰብ በጫካ ውስጥ ያገኛቸውን የሀገር ውስጥ ጎብኚዎችን መንገድ እንዳይጠፋባቸውና ዝሆንና ሌሎች የዱር እንስሳትን ማግኘት የሚችሉበትን ትክክለኛ አቅጣጫ ቃላት እያጠረው በየዋህነት "በዚህ ከሄዳችሁ ኮንታ ትገባላችሁ" ያለውን ንግግር ከአውድ ውጪ በመውሰድ ተገቢነት በሌለውና በተሳሳተ መንገድ በማሰራጨት የአካባቢያችንና የህዝባችን መልካም ስም እንዲጎድፍና አካባቢው በመጥፎ እንዲቀረጽ ምክንያት እየሆነ መሆኑን ታዝበናል፡፡

የዚህ ግለሰብ የዋህነት የተሞላው ንግግርና አገላለጽ በኢትዮጵያዊ ጨዋ ባህልና አስተሳሰብ በመልካምነትና በአውንታ ተወስዶ መገለጽ ሲገባው ስለአካባቢው በቂ መረጃ በሌላቸው አካላት ዘንድ ጥርጣሬን ፈጥሯል፡፡
አሁንም በተሳሳተ ትርክት የመጥፎ ነገር ምሳሌ ሆኖ በተለያየ ማህበራዊ ሚዲያ አውታሮች ሲገለጽ ይስተዋላል፡፡

ከሁሉ በላይ የሚያሳዝነው በመላው ዓለም ተደራሽነት ያላቸው እንደነ ኢ.ቢ.ኤስ(ebs) የመሳሰሉ ትላልቅ ሚዲያዎችና አንዳንድ ማስታወቂያ የሚሰሩ ድርጅቶች ጭምር ይህን የግለሰቡን አገላለጽ የሚዲያ በማይገባ መንገድ ሲጠቀሙበት ይስተዋላል እሄ ስህተት ነው

15/10/2024

በባህር ዳር ከተማ ሙሉዓለም አዳራሽ ፊት ለፊት አምሳል ምትኬ የባህል ምሽት ላይ ቃጠሎ መነሳቱ ተነግሯል።

Address

Wellega
Nek'emte

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis mereja posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share