Wajo ዋጆ Tube

Wajo ዋጆ Tube Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Wajo ዋጆ Tube, Advertising agency, Hossaina, Shone.

 ?🤔ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች ሁሉ የደህንነት መጠበቂያ ቆብ(Helmate) እንዲያደርጉ የሚያስገድድ አዋጅ  #በሀላባ መውጣቱ አይዘነጋም። ይህን ህግ ለማስከበር አንዳንድ ሰዎችን እስከ 30...
22/11/2025

?🤔

ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች ሁሉ የደህንነት መጠበቂያ ቆብ(Helmate) እንዲያደርጉ የሚያስገድድ አዋጅ #በሀላባ መውጣቱ አይዘነጋም። ይህን ህግ ለማስከበር አንዳንድ ሰዎችን እስከ 3000 በር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት ህጉን ለመተግበር ሲሞከር ነበር ይሁን እንጂ ይህ ህግ መተግበር የነበረው ።ሆኖም ይህ ህግ ለተወሰኑ የሀላባ ነዋሪዎች የወጣ እንጂ ከህግ አስከባሪ(Traffic Police) እየተመለከትን እንገኛለን። ?🤔 ብዙ የህብረተሰቡ አካላት በብዙ መንገድ ቅሬታቸውን በውስጥ መስመር እየለኩልን ሰለሆነ አፋጣኝ ምላሽ ከዞኑ መንገድ እና ትራንስፖርት ቢሮ መልስ ቢሰጥ እና ህጉ የሁሉም ከሆነ በሁሉም ዘንንድ ተግባራዊ ቢደረግ እንላለን!!!
የሀላባ ዞን መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ
የሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት Halaba Zone Prosperity Party Branch Office
የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ ሀላፊ እና የክልሉ ክላስተር አስተባባሪ የሆኑት ዶ/ር መሀመድ ኑሪዬ የተመራው የክልል፣ የዞኑ እና የወረዳ ከፍተኛ ና መካከለኛ ...
15/10/2023

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ ሀላፊ እና የክልሉ ክላስተር አስተባባሪ የሆኑት ዶ/ር መሀመድ ኑሪዬ የተመራው የክልል፣ የዞኑ እና የወረዳ ከፍተኛ ና መካከለኛ አመራሮች በዛሬው ዕለት በዌራ ወረዳ በደኔ ዶሮ መስረታዊ ህብረት ስራ ማህበር የመስክ ምልከታ እያደረጉ ይገኛሉ ።

የዌራ ወረዳ መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

 በሀላባ ዞን በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ላይ የሚገኛው ቡራቲቾ አዳሪ ልዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 12ኛ ክፍል ለመጀመርያ ጊዜ ካስፈተናቸው 60 ተማሪዎች 47 ተማሪዎችን በከፍተኛ ውጤት ያሳለፈ...
12/10/2023


በሀላባ ዞን በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ላይ የሚገኛው ቡራቲቾ አዳሪ ልዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 12ኛ ክፍል ለመጀመርያ ጊዜ ካስፈተናቸው 60 ተማሪዎች 47 ተማሪዎችን በከፍተኛ ውጤት ያሳለፈ መሆኑ ተገለጸ

የሀላባ ቡራቲቾ አዳሪ ትምህርት ቤት በዘንድሮ ዩንቨርስቲ መግቢያ ፈተና ካስፈተናቸው 60 ተማሪዎች 47 ተማሪዎችን 78.3% ማሳለፍ ችሏል።

#ከ400 በላይ ያስመዘገቡ 17 ተማሪዎች ሲሆኑ #ከ350 እስከ 399 ውጤት ያስመዘገቡት 9 ተማሪዎች ናቸው።

በተፈጥሮ ዘርፍ ከተፈተኑት 40 ተማሪዎች ያላለፉት 6 ተማሪዎች ብቻ መሆኑ ተገልጿል።

#በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ጠቅላላ የተፈተኑ ተማሪዎች ቁጥር 20 ሲሆን ከነኚህም ውስጥ
#ከ400 በላይ ውጤት ያስመዘገበው 1 ተማሪ ሲሆን #ከ300-399 ውጤት ያስመዘገቡ 12 ተማሪዎች ናቸው

በማህበራዊ ዘርፍ ከተፈተኑት 20 ተማሪዎች ያላለፉት 7 ተማሪዎች መሆኑም ተገልጿል።

በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ የተፈተኑ ተማሪዎች ጠቅላላ 40 ሲሆኑ #ከ500 በላይ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ 8 ተማሪዎች ናቸው
ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡት!!
1. ዙመር በዳዊ 591
2. አብድል መጂድ 553
3. ኢንትሳር መሀመድ 531
4. ሙሉ አጋፋሪ 502
5. ብስራት 520
6. ሳሙኤል 516
7. ነጂዋ አብራር 510
8. ኑረዲን አ/ናስር 513

የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ።በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።በዚህም መሠረት ከዛሬ መስከረም 18 ቀን 2016 ከ...
29/09/2023

የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ።

በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

በዚህም መሠረት ከዛሬ መስከረም 18 ቀን 2016 ከሌሊቱ 6 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ የሚሆነው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

- ቤንዚን 👉 በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም

- ነጭ ናፍጣ 👉 በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም

- ነጭ ጋዝ 👉 በሊትር 76 ብር ከ75 ሳንቲም

- የአውሮፕላን ነዳጅ 👉 በሊትር 70 ብር ከ83 ሳንቲም

- ቀላል ጥቁር ናፍጣ 👉 በሊትር 62 ብር ከ36 ሳንቲም

- ከባድ ጥቁር ናፍጣ 👉 በሊትር 61 ብር ከ83 ሳንቲም መሆኑ ተገልጿል፡፡

ምንጭ ፣ንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር

ለደመራ በዓል ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ይፋ ሆኑ! በነገው ዕለት በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የደመራ በዓል ምክንያት ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ...
26/09/2023

ለደመራ በዓል ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ይፋ ሆኑ!

በነገው ዕለት በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የደመራ በዓል ምክንያት ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አድርጓል፡፡

በዚሁ መሠረት ነገ ከረፋዱ 5:00 ጀምሮ እስከ በዓሉ ፍፃሜ ድረስ፡-

• ከኡራዐል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል አደባባይ ላይ

• ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ

• ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ

• ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር ላይ)

• ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት ላይ

• ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ

• ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል ላይ

• ከሃራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት ላይ

• ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ
• ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ እንዲሁም

• ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ፡፡

አሽከርካሪዎች ይህን ተገንዝበው አማራጭ መንገዶችን በመጠቀምና የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚያሳዩአቸው መንገድ በመጓዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።

የመውሊድ በዓል ረቡዕ ይከበራል!!የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት 1498ኛው የነቢዩ ሙሐመድ (ሰዓወ) የመውሊድ በዓል የፊታችን ረቡዕ መስከረም 16/2016 በታላቁ አንዋር መስ...
25/09/2023

የመውሊድ በዓል ረቡዕ ይከበራል!!

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት 1498ኛው የነቢዩ ሙሐመድ (ሰዓወ) የመውሊድ በዓል የፊታችን ረቡዕ መስከረም 16/2016 በታላቁ አንዋር መስጂድ እንደሚከበር አስታውቋል።

ለበዓሉ አከባበር ጠቅላይ ምክር ቤቱ ከታላቁ አንዋር መስጂድ ጋር በቅንጅት ዝግጅት እያደረገ እንደሆነ ተገልጿል።

በዓሉ ረቡዕ ከጠዋት አንስቶ እስከ ቀን 7:00 ሰዓት ድረስ በታላቁ አንዋር መስጂድ እንደሚከበር ተመላክቷል። ሕዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር የተቸገሩትን በመርዳት የተራቡትን በማብላት መሆን እንዳለበትም መልዕክት ተላልፏል።

📍 በጎንደር ከተማ ከትናንት አንስቶ ብርቱ ዉጊያ እንደተካሄደ የአይን እማኞች እና የፋኖ ቃል አቀባይ ለዶይቸ ቬለ ተናግረዋል።በጎንደር ከተማ በተለይ በቀበሌ 18 ሸዋ ዳቦ በሚባል አካባቢ እስ...
24/09/2023

📍

በጎንደር ከተማ ከትናንት አንስቶ ብርቱ ዉጊያ እንደተካሄደ የአይን እማኞች እና የፋኖ ቃል አቀባይ ለዶይቸ ቬለ ተናግረዋል።

በጎንደር ከተማ በተለይ በቀበሌ 18 ሸዋ ዳቦ በሚባል አካባቢ እስከ እኩለ ቀን የደረሰ ውጊያ ሲደረግ መቆየቱን እና በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት ሳይደርስ እንዳልቀረ እኚሁ የአይን ምስክር ተናግረዋል።« ከሌሊት አስር ሰዓት ጀምሮ በተለይ ሸዋ ዳቦ 18 በሚባል እኔ ባለሁበት አካባቢ በፋኖ እና በመከላከያ 10 ሰዓት ነው የጀመረው። ጥዋት ስነሳ ውጊያ ነው ፤ ወደ ውጭ መውጣትም አልተቻለም። ለአንድ አፍታ ስንወጣ የወደቀም አለ ፤ አንድ የመከላከያ መኪናም የተቃጠለ አለ ። ከዚያ ውጭ የፋኖ ታጣቂዎች ቀበሌ 18 አብዛኛ አካባቢ አሉ። መከላከያም በዙሪያው አለ፤ ተኩሱም እንዳለ ነው። » በከተማ የእንቅስቃሴ መስተጓጎል እንዳለ የነገሩን እኙሁ የከተማዋ ነዋሪ ውጥረቱ አይሎ መቀጠሉን ገልጸዋል።

«18 አሁንም ውጥረት ነው ተኩስ አለ ፤ አልፎ አልፎ የከባድ መሳሪያ ድምጽ ይሰማል። ህዝቡም ያው የተሽከርካሪ እንቅስቃሴም የለም ፤ ቁጭ ብሎ ማየት ነው።» ለደህንነታቸው ሲባል በስም መጠቀስ የማይፈልጉት እና ራሳቸውን የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ ቃል አቀባይ ብለው የሚጠሩት ግለሰብ እንደገለፁት ትናንትና አመሻሽ ጀምሮ «የሁለተኛው የትግሉ ምልዕፍ የመጀመሪያ ዙር የማጥቃት እንቅስቃሴ ተጀምሯል» ብለዋል።

በተያያዘ ዜና የጎንደር ከተማ ኮማንድ ፖስት በዚህ ጉዳይ ላይ መግለጫ አውጥቷል።በመግለጫውም" የፋኖ ታጣቂዎች ዛሬ ሌሊት 10፡00 ላይ ሰርጎ በመግባት አንድ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር መሞከራቸውን እና ድርጊቱን ማክሸፉን አረጋግጧል።(ምንጭ፣ ዶይቸቬለ)

 በባለፈው አመት በጎንደር ከተማ በነበረው ግጭት ምክንያት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ይሰጥ የነበረውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ  ፈተና ያላጠናቀቁ ተማሪዎችን ባለፉት ሁለት ቀናት ወደ ተቋሙ በመግባት ...
22/09/2023



በባለፈው አመት በጎንደር ከተማ በነበረው ግጭት ምክንያት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ይሰጥ የነበረውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያላጠናቀቁ ተማሪዎችን ባለፉት ሁለት ቀናት ወደ ተቋሙ በመግባት ፈተናውን መውሰዳቸው ተገልጿል።

በአጠቃላይ በፀጥታ ችግር ፈተናውን መፈተናውን ማጠናቀቅ ሳይችሉ ቀርተው የነበሩ 11 ሺህ 851 ተማሪዎች መስከረም 10/2016 ዓ.ም እና መስከረም 11/2016 ዓ.ም ወደ ዩኒቨርሲቲው ገብተው ፈተናውን ወስደዋል።

ተማሪዎቹ የኬሚሰትሪ፣ ባዮሎጂ እና የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር ትምህርት ፈተና እንደወሰዱ ተጠቁሟል።

ተፈታኝ ተማሪዎች ለክልሉ ሚዲያ (አሚኮ) በሰጡት ቃል ፤ ትምህርት ሚኒስቴር ፈተናው በፍጥነት አርሞ ውጤቱ ከሌሎች ተማሪዎች ጋር ይፋ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል።

በሀገር አቀፍ ፈተናዎች አገልግሎት የፈተና ጣቢያ ኃላፊ ሄነው የተመደቡ አቶ ወንድወሠን ሽፈራው ፤ የተማሪዎች ፈተና ቶሎ ታርሞ ውጤቱ ይፋ እንደሚደረግ ከትምህርት ሚኒስቴር በኩል መረጃ እንዳላቸው ገልጸዋል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎትም ፤ የተማሪዎቹ ፈተና በፍጥነት ታርሞ ውጤቱ ይፋ እንደሚደረግ አሳውቋል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና #ውጤት በፀጥታ እና በሌሎች ምክንያቶች ፈተናቸውን ያልወሰዱ ተማሪዎች ፈተናቸውን ከወሰዱ በኃላ እንደሚገለፅ ማሳወቁ ይታወሳል።

አገልግሎቱ ከዚህ ቀደም እንዳሳወቀው ከሆነ አሁን ፈተናቸውን የተፈተኑ ተፈታኞች ከመጀመሪያው ዙር ፈተና ተፈታኞች ጋር አንድ ላይ ውጤታቸው ይገለጻል።

በቅርቡ የአገልግሎቱ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ ማንጠግቦሽ አዳምጤ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ፈተናውን የማረም ሥራ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረው ምናልባትም እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስ ውጤቱ ይፋ ሊደረግ እንደሚችል አሳውቀዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብሄረሰቦች ምክር ቤት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ናስር ያሲን በመሆን ተሹመዋል።መልካም የሥራ ዘመን ይሁንልህ!!
16/09/2023

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብሄረሰቦች ምክር ቤት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ናስር ያሲን በመሆን ተሹመዋል።

መልካም የሥራ ዘመን ይሁንልህ!!

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ2016 የውድድር ዘመን ጥቅምት 17 ይጀምራል።የ2016 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የሚጀምርበትን ቀን እና ሌሎች ተያያዥ መረጃዎችን የኢትዮጵያ እግር ኳስ...
15/09/2023

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ2016 የውድድር ዘመን ጥቅምት 17 ይጀምራል።

የ2016 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የሚጀምርበትን ቀን እና ሌሎች ተያያዥ መረጃዎችን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ውድድር ዳይሬክቶሬት ለተሳታፊ ክለቦች አሳውቋል።

በዚህም መሰረት የዕጣ ማውጣት መርሐ ግብር ጥቅምት 3 ከተካሄደ በኋላ ውድድሩ ጥቅምት 17 እንደሚጀምር የተገለፀ ሲሆን ክለቦች ምዝገባቸውን እስከ መስከረም 11 ድረስ እንዲሁም የሚጠበቅባቸውን የዳኞችና ታዛቢዎች ክፍያ እስከ መስከረም 30 እንዲያጠናቅቁ አሳስቦ ክፍያ ያላጠናቀቀ ክለብ በእጣ ማውጣቱ ስነ ስርዓት ላይ የማይሳተፍ መሆኑ ተገልጿል።

Address

Hossaina
Shone

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wajo ዋጆ Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share