Eve Marko

Eve Marko Yes

እንኳን ለ2016 አዲስ ዓመት አደረሳችሁ‼️በፈጣሪ ቸርነት 2015ን አልፈን ወደ አዲሱ ዘመን ደርሰናል። ኢትዮጵያ በውጣ ውረድ ውስጥ እያሸነፈች ተጉዛለች። ጽኑ መርሕ፣ ብርቱ ሕዝብና የማይሸነ...
11/09/2023

እንኳን ለ2016 አዲስ ዓመት አደረሳችሁ‼️

በፈጣሪ ቸርነት 2015ን አልፈን ወደ አዲሱ ዘመን ደርሰናል። ኢትዮጵያ በውጣ ውረድ ውስጥ እያሸነፈች ተጉዛለች።

ጽኑ መርሕ፣ ብርቱ ሕዝብና የማይሸነፍ አምላክ ስላለን እዚህ ደርሰናል።

ብዙ ነገሮችን አሳክተናል፤ አያሌ ፈተናዎችን በድል ተወጥተናል፤ እልፍ መሰናክሎች ቢደረደሩም ጠንካራ መሰረት ሆነውን አልፈዋል።

የተሳኩልን ሁሉ የኅብረ ብሔራዊ አንድነታችን ውጤቶች ናቸው።

የተፈተንባቸው ደግሞ በመለያየት የተነሣ የመጡ ናቸው። በቀጣዩ ዓመት ፈተናዎቻችን እጅግ ቀንሰው፤ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ከአልማዝ ጠንክሮ፤ የኢትዮጵያን ሰላምና ደኅንነት በጽኑ መሠረት ላይ እናጸናዋለን።

ልማትና ብልጽግናዋን ወደሚመጥናት ደረጃ እናሻግረዋለን።

አዲሱ ዓመት የኢትዮጵያ ብልጽግና ዓመት እንዲሆን እመኛለሁ።

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!

ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ጳጉሜን 6 ቀን 2015 ዓ.ም

አንተ ሰልረዳኝ ሁሉን አለፈኩ የኔ ጌታ በሕይውተ ዘመን ሁሉ ላከበር አደል ሰለሰጣኝ አመሰግናለሁ:: ሁሉ ባንት ይ ቻላል የኔ ጌታ !!!
24/07/2023

አንተ ሰልረዳኝ ሁሉን አለፈኩ የኔ ጌታ በሕይውተ ዘመን ሁሉ ላከበር አደል ሰለሰጣኝ አመሰግናለሁ:: ሁሉ ባንት ይ ቻላል የኔ ጌታ !!!

16/07/2023
25/12/2022

መጽሐፍ ቅዱስን በዮኒዚም ትርጓሜ ስንፈታቸው
***
ባሻዬ ናማ እስኪ

መጽሐፍ ቅዱስን ገለጥ ስታደርገው....አውን እጅህ ላይ ያለውን ስልሳ ስድስቱ መጽሐፍ ቅዱስን ለማንባብ ስትከፍተው በሥጋ ንባብ አስደንጋጭ ነገር ግን በሃቅ እና በመንፈስ ሚዛን ላይ ትክክል የሆኑ እንዲህ አይነት ቃላትን ታገኛለህ።
***

“ዲቃላ ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ አይግባ፤ እስከ አሥር ትውልድ ድረስ ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ አይግባ።....ዘዳ23፥2"

ይህን ቃል መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ሳይሆን ገድለ መርቆርዮስ ወይም ገደለ ተክለሃይማኖት ላይ ተገኝቶ ቢሆንስ? የስንት ሳምንት ኦርቶዶክሱን የመስደብያ የስብከት እንጅራህ ይሆን ነበር?
+++

ሌላም እስኪ እንመልከት ...

“ለጥፋት ለቀረበው ሰው ብርቱ መጠጥ ስጡት፥ ነፍሱ ለመረረውም የወይን ጠጅ ስጡት፣ይጠጣ ድህነቱንም ይርሳ፥ ጕስቍልናውንም ከእንግዲህ ወዲህ አያስብ።...ምሳሌ 31፥6-7"

ይህ በጠቢቡ ስለምን እጅ በኩል የተጻፈ የእግዚአብሔር ቃል ነው። ከመጽሐፍ ቅዱስ ይልቅ በኦርቶዶክስ አንደኛው የጸሎት፣የታምራት፣የገድላት መጽሐፍ ላይ ብታገኘውስ? ህዝቡ ሰካራም የሆነው እንዲህ አይነት የስካር መንፈስ የያዙ መጽሐፍትን እየተሻሹ ነው ... ኡ ኡ ። ይህ ጣዖት አምላኪነት ነው ትለን ነበር አ?

+++
ባሻዬ

እባብ አዳኝ ነው የሚል ሐሳብ ያለው ንባብ ላሳይህ እስኪ..

“ሙሴም የናሱን እባብ ሠርቶ በዓላማ ላይ ሰቀለ፤ እባብም የነደፈችው ሰው ሁሉ የናሱን እባብ ባየ ጊዜ ዳነ። ዘኍ21፥9" "

እባብ እያዪ ህዝቡ ዳኑ። ይህን ቃል በደንብ አድርገህ ደጋግመህ አንብበው ።

ይህ ቃል በታምረ ማርያም ላይ ቢኖርስ? እባብ አዳኝ የሆነበት የጥልቁ መንፈስ አሰራር ያለበት መቅደስ ውስጥ መኖር ጣዖት አምላኪነት ተብሎብን አዳራሽ ሙሉ መንጋ ይጮኸብን ነበር።ግን መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ብቻ ነው ያለው።
+++

“ደንቆሮዎች፥ ሉቃ11፥40//“ውሾች ፣ፊል 3፥2//“ጋለሞታ 1ኛ ቆሮ 6፥15// ወዘተ ተብለው የተጻፉ ቃላት ገድላት ላይ ቢገኙ,...

የዘንዶው የስድብ አፍ የተሰጣቸው ተብሎልን የ2 ወር የአዳራሽ ስብከት ማሞቂያ እንሆን ነበር

+++
ስለኢየሱስ በተጻፈው ሐሳብ ላይ

“በምድር ላይ ሰላምን ለማምጣት የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ሰይፍን እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም። ማቴ 10፥34"

የሚለው የወንጌል ልሳን ከመጽሐፍ ቅዱስ ይልቅ በአዋልድ መጽሐፍት ከሆኑት በአንዱ ላይ ቢኖርስ? የሰላሙን አለቃ ጠብ ጫሪ አደረጉት፣አዳኙን ገዳይ ነው አሉት፣ ተብሎልን በፍጩት እና በጩኸት በቀለጠ ኡኡታ ጆሯችን ይደማ ነበር።
+++
ስለኢየሱስ ክብር በሚያትተው የመጽሐፍ ክፍል ላይ

“ከመላእክት ይልቅ በጥቂት አንሶ የነበረውን ኢየሱስ... ዕብ 2፥9"

የሚለውን ሐሳብ ታምረ ማርያም ውስጥ ቢገኝ ምን አይነት ፉጩት እና ሁከት እንደሚፈጠር አስባችሁታል?

ኢየሱስን ከመላእክት አሳንሰው፣ክርስቶስን ከገብርኤል ከሚካኤል በታች አድርገው ተብሎ ሰማይ ሰንጣቂ ጩኸት ይሰማ ነበር።
+++
መርቆርዮስ ቀይ ባህርን ለሁለት ከፈለ፣ተክልዬ ጸሐይን በገባዖ አቆመ፣ቅዱስ ያሬድ ከእንስሳ ጋር ቃል በቃል አወራ፣ የሚሉ ሐሳቦች ገድላት ላይ ቢገኙ የምንዱባዮችን ጩኸት አስባቹታል...

ከፊደል ጋር በግርድፉ መጋጨት የመንፈስ ሞት ያስከትላል። እንኳን ገድላትን ይቅርና መጽሐፍ ቅዱስ በግርድፍ የቃል ዐረፍተ ነገር ልፍታው ብትል መገኛህ እንጦሮንጦስ ነው። ምክንያት ካልከኝ

“ፊደል ይገድላልና መንፈስ ግን ሕይወትን ይሰጣል።”
— 2ኛ ቆሮ 3፥6 የሚል የእግዚአብሔር ህግ ስላለ።

እግዚአብሔር ይመስገን !

Kune Demelash kassaye -Arba Minch

Address

Tulu Dimtu

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Eve Marko posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Eve Marko:

Share