ሮሃ ሚዲያ / Roha Media

ሮሃ ሚዲያ / Roha Media Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ሮሃ ሚዲያ / Roha Media, Dubai, Addis Ababa.

 #ስበርዜና #የፈራነው #ደረሰ 📌 የአይኤምኤፍን የ261 ሚሊዮን ዶላር ብድር ተከትሎ መንግስት ሊያሟላቸው የሚገቡ 4 ዋና ዋና ግዴታዎች *የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ቦርድ የ26...
08/06/2026

#ስበርዜና
#የፈራነው
#ደረሰ
📌 የአይኤምኤፍን የ261 ሚሊዮን ዶላር ብድር ተከትሎ መንግስት ሊያሟላቸው የሚገቡ 4 ዋና ዋና ግዴታዎች
*የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ቦርድ የ261 ሚሊዮን ዶላር የብድር ድጋፍ ለኢትዮጵያ እንዲለቀቅ መወሰኑ ይታወቃል። መንግስት ይህንን የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘትና የጀመረውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ በስኬት ለማስቀጠል ሊያሟላቸው የሚገቡ 4 ዋና ዋና ግዴታዎችና ተግባራት ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦

1. የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ሙሉ በሙሉ ነፃ መተው (Exchange Rate Flexibility) 💸

👉የመንግስት ግዴታ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በዶላር እና በብር ምንዛሬ ተመን ላይ ምንም ዓይነት ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት (Intervention) እንዳያደርግ በጥብቅ ተቀምጧል።

📄ተግባራዊነቱ፦ የምንዛሬ ዋጋው ሙሉ በሙሉ በባንኮች እና በገበያው ፍላጎትና አቅርቦት ላይ ብቻ ተመስርቶ እንዲቀጥል ማድረግ።

2. የታክስ አሰባሰብ ስርዓቱን ማጥበቅ እና ገቢን ማሳደግ (Revenue Mobilization) 📈

👉የመንግስት ግዴታ፦ የሀገሪቱን የሀገር ውስጥ ታክስ ከሀገራዊ ምርት (Tax−to−GDPratio) አንጻር በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ።

👉ተግባራዊነቱ፦ አዳዲስ የታክስ ፖሊሲዎችን መተግበር፣ የኤሌክትሮኒክስ የታክስ ስርዓትን ማስፋፋት እና በንግድ ተቋማት ላይ የሚደረገውን የኦዲትና ቁጥጥር ስራ ይበልጥ ማጥበቅ።

3. ቀጥተኛ ያልሆኑ ድጎማዎችን ሙሉ በሙሉ ማስወገድ (Subsidy Removal) ⛽

👉የመንግስት ግዴታ፦ የመንግስትን የበጀት ጉድለት ለመቀነስ የነዳጅ እና ሌሎች አጠቃላይ ድጎማዎችን ደረጃ በደረጃ ማንሳት።

👉ተግባራዊነቱ፦ ለነዳጅ የሚወጣውን የመንግስት ወጪ በመቀነስ፣ የተቆጠበውን ገንዘብ ለልማትና ለዕዳ ክፍያ ማዋል ህገ-ደንቡ በሚያዘው መሰረት መተግበር።

4. የማህበራዊ ደህንነት መረብን (Safety Nets) በበጀት መደገፍ 🤝

📄የመንግስት ግዴታ፦ ከላይ የተጠቀሱት ጥብቅ እርምጃዎች (የድጎማ መነሳትና የምንዛሬ ለውጥ) በዝቅተኛው ማህበረሰብ ላይ የሚያደርሱትን ጫና መከላከል ይኖርበታል።

📄ተግባራዊነቱ፦ መንግስት ከተለቀቀው ብድር እና ከሀገር ውስጥ ገቢው ላይ ከፍተኛውን በጀት ለሴፍቲኔት (PSNP) እና ለድሆች የታለሙ ቀጥተኛ የገንዘብና የምግብ ድጋፎች ላይ ማዋል አለበት።

 #ጥቆማ የአሜሪካ መንግሥት ከአፍሪካ ቪዛ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን መካከል ኢትዮጵያን አልቀነሳትም  | የአሜሪካ መንግሥት በአፍሪካ አህጉሉአንዳ የሚሰጠውን የቪዛ አገልግሎት በከፍተኛ ደረ...
03/06/2026

#ጥቆማ

የአሜሪካ መንግሥት ከአፍሪካ ቪዛ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን መካከል ኢትዮጵያን አልቀነሳትም

| የአሜሪካ መንግሥት በአፍሪካ አህጉሉአንዳ የሚሰጠውን የቪዛ አገልግሎት በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል እየተዘጋጀ ነው።

በዚህ መሠረት በአፍሪካ ውስጥ የቪዛ አገልግሎት የሚሰጡ የአሜሪካ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች ቁጥር ከ50 ወደ 20 ብቻ ለመቀነስ ወስኗል። ይህ ለውጥ በቅርብ ጊዜያት ይጀመራል ተብሏል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ያጸደቁት ይህ አዲስ እቅድ፣ በአፍሪካ 20 ዋና የክልል ማዕከላት (Regional Hubs) በመሾም፣ ሌሎች ቦታዎችን የቪዛ ሙሉ አገልግሎት እንዳይሰጡ ለመዝጋት ያቀደ ነው።

እነዚህ የ20 ዋና ማዕከላት የትኞቹ ናቸው ፦

° አዲስ አበባ (ኢትዮጵያ) 🇪🇹
° አክራ (ጋና) 🇬🇭
° ዳካር (ሴኔጋል) 🇸🇳
° ጅቡቲ (ጅቡቲ) 🇩🇯
° ካምፓላ (ኡጋንዳ) 🇺🇬
° ኪጋሊ (ሩዋንዳ) 🇷🇼
° ኪንሻሳ (ኮንጎ) 🇨🇩
° ላጎስ (ናይጄሪያ) 🇳🇬
° ናይሮቢ (ኬንያ) 🇰🇪
° አቢጃን (አይቮሪ ኮስት) 🇨🇮
° ዳሬሰላም (ታንዛኒያ) 🇹🇿
° ሎሜ (ቶጎ) 🇹🇬
° ሉዋአንዳ (አንጎላ) 🇦🇴
° ማላቦ (ኢኳቶሪያል ጊኒ) 🇬🇶
° ሞንሮቪያ (ላይቤሪያ) 🇱🇷
° ፖርት ሉዊስ (ሞሪሸስ) 🇲🇺
° ፕራያ (ኬፕ ቨርዴ) 🇻🇪
° ያውንዴ (ካሜሩን) 🇨🇲
° ኬፕ ታውን (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
° ጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦

ከእንግዲህ ወዲያ በእነዚህ 20 ማዕከላት ያልተካተቱ ሀገራት ዜጎች የቪዛ ቃለ መጠይቅ፣ የጣት አሻራ እና ሌሎች ሂደቶችን ለማጠናቀቅ በራሳቸው ወጪ ወደ ቅርብ ማዕከል መጓዝ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል ያለው ቲክቫህ ነው።

የጨረባው  ምርጫ  ዴሞክራሲን  አያዋልድ፣  መፍትሔ  አይፈይድ!   (በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት የተሰጠ መግለጫ) ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ከ...
03/06/2026

የጨረባው ምርጫ ዴሞክራሲን አያዋልድ፣ መፍትሔ አይፈይድ!
(በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት የተሰጠ መግለጫ)

ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ከቅድመ ኹኔታዎች አለመሟላትና ከነጉድለቱ፣ መሠረታዊ የኾኑ የሀገር ችግሮች ሊፈቱ የሚችሉት በንግግር፣ በድርድርና በጥልቅ ውይይት መኾን አለበት በሚል ሩቅና አዋጭ እሳቤ፣ የውስብስብ ችግሮች መፍቻ የሀሳብ የበላይነት መኾኑን አስልተን፣ በዚኽ ከደረጃ በታች በኾነ ምርጫ ቀርቶ በእውነተኛ ምርጫም ቢኾን የገዘፈውና የተወሳሰበው ሥርዓት ወለድና መጠነ ሰፊ ችግር ማስወገጃ መንገድ ንግግርና ድርድር ነው በሚል እና ከውጭ ኾኖ ተባለ ከማለት በተጨባጭ ነውሩን ለማጋለጥ እጅግ በተቀዛቀዘ ስሜት በተወሰኑ አስቻይነት አላቸው ባልንባቸው አካባቢዎች ተወስነን ወደምርጫው ገብተናል። በሂደቱ ላይ እንደአቅም የአገዛዙን የነውር ገመና በማጋለጥና መሰል የፖለቲካ የበላይነትን የተጎናጸፍንበት ነው።

ውጤቱ እና በኹሉም አካባቢዎች የተፈጸሙ ችግሮች ገና ተጠቃለው ያልመጡ ቢኾንም በሂደቱ ከቅድመ ምርጫ፣ የምርጫ ዕለትና የምርጫ ማግስት ኾነን ስናየው ከነግዙፍ እንከኑ፣ ከአሳሳቹ 97% የአስቻይነት ሪፖርትና ትንተና፣ ከኢሕአዴጋዊ የጥርነፋ ውርስ ባህርይ/co-opted/ እና 99.9% የጥቅለላ አባዜና ጉምዥታ ያልተላቀቀ፣ በዓይነቱም ኾነ በድርጊቱ በታሪክ ከሚታወቁት የጨረባ ምርጫዎች ያልተለየ መኾኑ ገሃድ የወጣ ነው። በቅርብ ታሪካችን እንዳየነው ይኽ ልማድ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ፣ እጅግ የተወሳሰበውንም የሀገራችንን ችግር ከድጡ ወደ ማጡ ከመውሰድ የዘለለ ዴሞክራሲን አያዋልድም፣ መፍትሔም አይፈይድም! ውጤቱም ምንም ቢኾን የትኛውም ዕጩ በትብብሩ ስም ምክርቤት እንዳይገባና ቢገባም ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ነው። በዚኹ አጋጣሚ ከነበዛ እንከኑም ቢኾን በጠባቧ ቀዳዳ የቦርዱ ኃላፊዎችንና ውስን ድርጅቶች ላደረጉትና እያደረጉ ላለው ጥረት እውቅና አለን።

ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት አገዛዙ ለዘመኑ በማይመጥንና ከባህርይ አባቱ በወረሰው የጨረባ ምርጫ ራሱን ለንግሥና ከማጨት ወጥቶ የስልጣን ምንጭና ባለቤት ሕዝብ ብቻ መኾኑን ተረድቶ የሕዝብን ድምጽ እስከሚያከብር ትግሉን አጠናክሮ የሚቀጥል ሲኾን በቅርቡ ሕዝብን ያሳተፈ ሰላማዊ ትግል ለማካሄድ የተሟላ መግለጫ የሚሰጥ ይኾናል።

ዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ፣ ዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ እንዲኹም ዓለምአቀፉ ሚዲያ ከሰሞኑ ላደረገው የላቀ አስተዋጽዖ እውቅና እየሰጠን አኹንም እንደጀመረው የኢትዮጵያን ጉዳይ በቅርበት እንዲከታተል፣ ግፎችን እንዲያጋልጥ፣ አገዛዙ ሸብረክ ብሎ ከፖለቲካ ኃይሎች ጋር እስከሚደራደር ምንም ዓይነት እውቅና የመስጠት የሚመስል መልዕክት ከማስተላለፍ እንዲቆጠብ እንጠይቃለን።

ያ ባይኾን በኢትዮጵያውያን ቁስል ላይ እንጨት እንደመስደድ፣ ለንጹሓን እልቂት ቦምብ እንደማቀበል፣ የግፉ አጋፋሪ እና ከኢትዮጵያውያን ጥቅም በተቃራኒ የቆሙ እንደኾነ አድርገን እንቆጥረዋለን።

ፈጣሪ አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!

Via ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት -ለኢትዮጵያ

በምሥራቅ አርሲ ማንነትን (ሃይማኖትን) መሠረት ባደረገ ጥቃት በርካታ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ የሆኑ ዜጎች እስከአሁን ማንነቱ ባልታወቀ አካል እንደተገደሉ እና ቤተክርስቲያን መቃጠ...
03/06/2026

በምሥራቅ አርሲ ማንነትን (ሃይማኖትን) መሠረት ባደረገ ጥቃት በርካታ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ የሆኑ ዜጎች እስከአሁን ማንነቱ ባልታወቀ አካል እንደተገደሉ እና ቤተክርስቲያን መቃጠሉ፣ ከጥቃቱ የሸሹ ዜጎችም ከቀያቸው መሰደዳቸው ከመገናኛ ብዙሃንና ከሀገረስብከቱ የሚወጡ መረጃዎች ያሳያሉ።

ኢዜማ ሁሌም እንሚያስገነዝበው ለዚህ ዐይነቱ ማንነትን መሠረት ያደረገ ጥቃት ምንጬ ፖለቲካችን በማንነት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ነው ብሎ ያምናል።

በተጠቀሰው ስፍራ በተደጋጋሚ የሚደርሰው መሰል ጥቃትን የመከላከል ኃላፊነት የአካባቢው የመንግሥት አስተዳዳር እና የጸጥታ ተቋማት መሆኑ የታወቀ ነው። በዚህ ረገድ የአካባቢው አስተዳደርና የኦሮሚያ ክልል መንግሥት በተደጋጋሚ ተፈትኖ እንደወደቀ ማየት ይቻላል።

ስለሆነም አስፈላጊውን ማጣራት ተደርጎ ኃላፊነት የሚወስዱ አካላትን በመለየት አስተማሪና ሕጋዊ የእርምት እርምጃ መንግሥት እንዲወስድ እናሳስባለን።

በዚህ ኢሰብአዊ ጥቃት ለተገደሉት ዜጎች የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ለሟች ቤተሰቦችና ዘመዶች እንዲሁም ለመላው ኢትዮጵያውያን መጽናናትን እንመኛለን።

በማንነት ላይ የተመሠረተው ፕለቲካችን ጨርሶ አንድ በአንድ ሳያጠፋን መፍትሔ ማበጀት የሁሉም ባለድርሻ አካላት የቤት ሥራ መሆኑንም ኢዜማ ማስገንዘብ ይወዳል።

#ኢዜማ

03/06/2026

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በትውልድ ስፍራቸው ይህ ሁሉ ህዝብ ሲያልቅ ቢያንስ ድርጊቱን ማውገዝ ይጠበቅባቸዋል!

ከትናንት በስቲያ ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን በአሰኮ ወረዳ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች እና ቤተክርስቲያናት ላይ ተነጣጥሮ በታጣቂዎች ተሰነዘረ መጠነ ሰፊ እና አሰቃቂ የተባለ ጥቃት እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይወት ማለፉን፣ ቁጥራቸው ምናልባትም ከ280 በላይ የሆኑ ሰዎች ደግሞ የደረሱበት ባለመታወቁ እና በስልክ ሊገኙ ስላልቻሉ ተገለው ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት እንዳላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች በስልክ አሳውቀውኛል።

የሸኔ ታጣቂዎች ጥቃቱን እንደፈፀሙት የሚናገሩት ነዋሪዎቹ ከዚህ በፊትም ከሰባት ግዜ በላይ 'ጠለታ ገብርኤል' በሚባል አካባቢ ጥቃት አድርሰው እንደነበር ተናግረዋል።

የአሁኑን ለየት የሚያደርገው ታጣቂዎቹ ከመርቲ ወረዳ፣ ከፈንታሌ እና ከከረዩ እንዲሁም ከኢቱ አካባቢ የነበሩ ሁሉ ተሰባስበው በግምት ሶስት ሺህ ሆነው አሰኮ ወረዳና አካባቢው በመምጣት ቢዮ ቀበሌ፣ ጠለታ ገብርኤል፣ ኩፍቴና መዳህኒአለም እና አካባቢውን በአሁኑ ሰዓት ሙሉ በሙሉ አቃጥለዋል የሚሉት በለቅሶ እና በድንጋጤ በመጯጯህ የሚናገሩት ነዋሪዎች ናቸው።

በእሬቻ ሚካኤል፣ በሱንቴ ማርያም፣ በሌንጫ ኦዳ፣ በኳስ ድሬ፣ በአርባ ቀላ፣ በወራንቡስ እና በተለያዩ ቦታዎች አሁን ድረስ ጥቃቱ ተስፋፍቶ ይገኛል የሚሉት ነዋሪዎቹ እስካሁን አንድም የመንግስት ሀይል ወደ ስፍራው እንዳልገባ እና ታጣቂዎቹ አካባቢው ላይ ከበባ በማድረግ ሰው እንኳን እንዳያመልጥ አድርገው ጭፍጨፋ እየፈፀሙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ይህ አካባቢ የከንቲባ አዳነች ትውልድ ስፍራ ነው፣ ምናልባትም ከሟቾቹ መሀል አንዳንዶቹን ሊያውቁ ወይም አብረው ተምረው፣ ሰርተው ይሆናል። ታድያ ሌላው አለም ላይ እንደምናየው በፍጥነት የጥቃቱ ቦታ ላይ ሄዶ ህዝብን ማረጋጋት እና ማፅናናት በአካባቢው በቀጠለው ጥቃት ምክንያት አልተቻለም እንበልና... በትውልድ ስፍራቸው እንዲህ አይነት ዘግናኝ ጥቃት ሲፈፀም 'ነፍስ ይማር' ለማለት እና ድርጊቱን ለማውገዝ ምነው ተሳናቸው? ሌሎች ባለስልጣናት እና የፀጥታ አካላትስ?

የሀገሪቱ የመከላከያ፣ የፖሊስ፣ የሚሊሻ፣ የአየር ሀይል እና ሌሎች ሀይሎችስ ለሰዓታት ሳይሆን ለቀናት እስካሁኑ ሰዓት ድረስ እየተፈፀመ ያለ ጥቃትን ለመከላከል ለምን አልቻሉም?

የዚህ ሀገር ነገር አንዳንዴ ያደክማል... ህዝቡ ድረሱልን ብሎ የሚጮኸው መንግስት ላይ ሳይሆን ሚድያ ላይ፣ ሚድያው መረጃ ለህዝብ ሲያደርስ ተመልሶ በህዝብ እና መንግስት የሚሰደበው እና የሚሳደደው ራሱ ሚድያው።

ለማንኛውም ለእኔ ይህን በመፃፌ ቀለል ይለኛል። በለቅሶ፣ በድንጋጤ እና በመጯጯህ ያናገርኳቸው ዜጎች ሁኔታ ግን መቼም ከአዕምሮ የማይፋቅ አሳዛኝ ክስተት ነው።

ያሳዝናል፣ ነፍስ ይማር!

Via meseret media

በምሥራቅ አርሲ የተፈጸመው ጥቃት፡ 13 ንጹሐን ተገደሉ፣ ታሪካዊት ቤተክርስቲያን ተቃጠለችአርሲ፡ በአርሲ ሀገረ ስብከት በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች በግንቦት ወር መጨረሻ በተፈጸመ ጥቃት የ13 ...
02/06/2026

በምሥራቅ አርሲ የተፈጸመው ጥቃት፡ 13 ንጹሐን ተገደሉ፣ ታሪካዊት ቤተክርስቲያን ተቃጠለች

አርሲ፡ በአርሲ ሀገረ ስብከት በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች በግንቦት ወር መጨረሻ በተፈጸመ ጥቃት የ13 ዜጎች ሕይወት ማለፉን የአርሲና የሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ አስታወቁ።

እንደ ሀገረ ስብከቱ መረጃ ከሆነ፣ ጥቃቱ የተፈጸመው ከአሰኮ፣ ሺርካ እና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች ሲሆን፣ በደረሰው ጥቃት ከ280 በላይ ምዕመናን ከቀያቸው መፈናቀላቸው ታውቋል።

በተፈጸመው ግፍ የአካባቢው ነዋሪዎች መኖሪያ ቤቶች በእሳት መውደማቸውና ንብረቶቻቸው መዘረፉ ተገልጿል።

የ101 ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ጋይቷል::

የካራ ኩፍተና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በዘረፋ የተጎዳ ሲሆን፣ ምዕመናን የቤተክርስቲያኒቱን ጽላት ይዘው ለመሰደድ መገደዳቸው ታውቋል።

ከጥቃቱ የተረፉት ወገኖች ምንም አይነት ንብረት ሳይዙ ሜዳ ላይ መውደቃቸው የደረሰው ሰብዓዊ ቀውስ ምን ያህል የከፋ መሆኑን ያሳያል።

በጥቃቱ ሕይወታቸው ያለፈው ወገኖች ስም ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

1. አቶ ደምረው አበራ (70)
2. አቶ ከፈለኝ ልክየለው (56)
3. አቶ ሐይሉ ንጉሴ (70)
4. አቶ እሸቴ ዳመና (42)
5. አቶ አበባየሁ ዳኜ (42)
6. አቶ ሰሙ አባይነህ (70)
7. አቶ አማረ በላይነህ (80)
8. አቶ ተሬ ደሴ (25)
9. ወጣት ገነነ ጥላሁን (ሺርካ)
10. ወጣት ሙርቴሳ ጥላሁን (ሺርካ)
11. አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ (ሆንቆሎ ዋቤ)
12. አቶ በቀለ ኃይለሚካኤል (ሆንቆሎ ዋቤ)
13. አንድ የመንግስት ሚሊሻ

ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ በተፈጸመው አሳዛኝ ድርጊት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን በመግለጽ፣ ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝተዋል። "ስለ አንተ ሁልጊዜም ተገድለናል፣ እንደሚታረዱም በጎች ሆነናል።"

"መዝሙር 43፡22) በሚል ጥቅስ የተገለጸው ይህ ዘገባ፣ ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ እና የዜጎችን ደህንነት ለማረጋገጥ የሚመለከተው አካል ፈጣን ምላሽ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።

Via የአርሲ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በጣና ሐይቅ ላይ በደረሰ የጀልባ መገልበጥ አደጋ የሰው ሕይወት አለፈ  I ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም. በጣና ሐይቅ ላይ ተጓዦችን ይዛ ትጓዝ የነበረች ጀልባ በደረሰባት ድንገተኛ የመስመጥ...
21/05/2026

በጣና ሐይቅ ላይ በደረሰ የጀልባ መገልበጥ አደጋ የሰው ሕይወት አለፈ

I ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም. በጣና ሐይቅ ላይ ተጓዦችን ይዛ ትጓዝ የነበረች ጀልባ በደረሰባት ድንገተኛ የመስመጥ አደጋ የሰዎች ሕይወት ማለፉ ተነገረ። ተጓዦቹ የቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ዓመታዊ በዓል ለማክበር ወደ ገዳሙ በመጓዝ ላይ የነበሩ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች መሆናቸው ታውቋል።

በኬንያ በነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ምክንያት በተነሳው ተቃውሞ አራት ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም. -በነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ምክንያት በበርካታ የኬንያ ከተሞች በተቀሰቀሰው ተቃው...
19/05/2026

በኬንያ በነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ምክንያት በተነሳው ተቃውሞ አራት ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ

ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም. -በነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ምክንያት በበርካታ የኬንያ ከተሞች በተቀሰቀሰው ተቃውሞ የአራት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

በሚኒስቴሩ መግለጫ መሠረት ከ30 በላይ ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት ደርሷል ። ፖሊስ በአንዳንድ አካባቢዎች ተቃዋሚዎችን ለመበተን የአስለቃሽ ጋዝ የተኮሰ ሲሆን፥ ተቃዋሚዎች በበኩላቸው ቁልፍ መንገዶችን ለመዝጋት ጎማዎችን አቃጥለዋል።

የኬንያ የኢነርጂ እና የነዳጅ ቁጥጥር ባለሥልጣን ባለፈው ሳምንት የችርቻሮ ነዳጅ ዋጋን በ23.5 በመቶ ማሳደጉ ይታወሳል። የሀገሪቱ የትራንስፖርትና የኢነርጂ ሚኒስትሮች ከሕዝብ ትራንስፖርት ባለሥልጣናት ጋር ያደረጉት ውይይትም እስካሁን እቅባጭ ውጤት አላስገኘም።

ዘገባው የሮይተርስ ነው

 : እነ ጌታቸው ረዳ አድስ ምክር ቤት መሰረቱ!በህወሓት ጫና ከትግራይ የሸሹ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ክልሉን መልሶ ለመቆጣጠር ያስችለናል ያሉትን ምክር ቤት ዛሬ በአዲስ አበባ መሥርተዋል።እንደ ጌ...
17/05/2026

: እነ ጌታቸው ረዳ አድስ ምክር ቤት መሰረቱ!

በህወሓት ጫና ከትግራይ የሸሹ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ክልሉን መልሶ ለመቆጣጠር ያስችለናል ያሉትን ምክር ቤት ዛሬ በአዲስ አበባ መሥርተዋል።

እንደ ጌታቸው ረዳ እና ጀነራል ጻድቃን ገብረተንሳኤ ያሉ የህወሓት ተቃዋሚዎች የመሰረቱት፣ "የትግራይ ሰላምና ለውጥ ምክር ቤት" የተሰኘ ተቋም ነው። ምክር ቤቱ የተመሰረተው በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሰውን ሓራ መሬት ወይም የትግራይ ለውጥ ኃይል ታጣቂ ቡድን አዛዥ ጀኔራሎች አቅፎ መሆኑ ታውቋል።

በአዲስ አበባ ከተማ መመስረቱ የተነገረለት የለውጥ ኃይሎች ምክር ቤት፣ ህወሓትን አስወግዶ ትግራይን ለመቆጣጠር የሚሠራ ነው ተብሏል። በህወሓት ግፊት ከትግራይ የወጡት የፖለቲካ ኃይሎች እና አፋር ክልል የመሸገው ታጣቂ ቡድን በቀጣይ ስለሚኖራቸው የጋራ ትግል ሲመክሩ መሰንበቻውን ተገልጿል።

Address

Dubai
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሮሃ ሚዲያ / Roha Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share