በጉራጌ ዞን የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Wolkite
  • በጉራጌ ዞን የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

በጉራጌ ዞን የምሁር አክሊል ወረዳ  የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች  ጽ/ቤት ፈጣንና ወቅታዊ መረጃ ለዜጎች!
(1)

1447ኛው የኢድ አል አደሃ አረፋ በዓል በምሁር አክሊል ወረዳ ሐዋርያት ከተማ በተለያዩ ሀይማኖታዊ ክንዋኔዎች በድምቀት ተከበረ።‎‎ግንቦት19/2018 ዓ.ም‎‎1ሺህ 447ኛው አመተ ሂጅራ የኢ...
27/05/2026

1447ኛው የኢድ አል አደሃ አረፋ በዓል በምሁር አክሊል ወረዳ ሐዋርያት ከተማ በተለያዩ ሀይማኖታዊ ክንዋኔዎች በድምቀት ተከበረ።

‎ግንቦት19/2018 ዓ.ም

‎1ሺህ 447ኛው አመተ ሂጅራ የኢድ-አል አድሃ(አረፋ በዓል በምሁር አክሊል ወረዳ ሐዋርያት ከተማ በጀማኣ የኢድ ሶላት በድምቀት ተከብሮ አልፏል።

‎ ህዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር የተቸገሩትን በመርዳት በመጠያየቅና በመተጋገዝ ሊሆን እንደሚገባ የሐዋርያት ከተማ ዲያኡልሀቅ መስጂድ ኢማም እና የወረዳው እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ሰብሳቢ ኡስታዝ ሙህዲን አህመዲን በሐይማኖታዊ ስርዓቱ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ገልፀዋል።

‎ የአረፋ በዓል ሲከበር በእስልምና እምነት አስተምሮቱ መሰረት ከሚታረደው እርድም ማዕድ በማጋራትና በጋራ የሚከበር መሆኑን ገልፀው ህዝበ ሙስሊሙ በዓሉ በሚያከብርበት ወቅት ምስኪኖችና የተቸገሩ ወገኖች በመርዳት ሊሆን እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።

‎በመሆኑም ህዝበ ሙስሊሙ ከአላህ የታዘዘውን ተግባር በመፈጸም የተቸገሩ ወገኖችን ከማሰብ ባለፈ በማካፈል ሊሆን ይገባልም ብለዋል።

‎የበዓሉ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የኢድአል አደሃ (አረፋ) የኢድ ሶላት በሰላም በድምቀት መከበሩ ተናግረዋል።

‎ህዝበ ሙስሊሙ በበዓሉ ወቅት የመረዳዳት የመተሳሰብ እሴቶችን በማጠናከር ምስኪኖችን በማሰብና በማካፈል መከበር እንዳለበትም ገልፀዋል ሲል የዘገበው የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

‎በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ 1447ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ) በዓል በተለያዩ ሀይማኖታዊ ስነ-ስርአት በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።‎‎ግንቦት 19/2018 ዓ.ምሁር አክሊል‎‎ በምሁ...
27/05/2026

‎በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ 1447ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ) በዓል በተለያዩ ሀይማኖታዊ ስነ-ስርአት በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

‎ግንቦት 19/2018 ዓ.ምሁር አክሊል

‎ በምሁር አክሊል ወረዳ 1447ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ) በዓል በተለያዩ ሀይማኖታዊ ስነ-ስርአት በድምቀት እየተከበረ ነው።

‎በወረዳው በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት አንዱ የአረፋ በዓል ሲሆን የዘንድሮ የ1447ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ) በዓልን በጀመዓ ሶላት እየተከበረ ይገኛል።

ለመላው ሙስሊም ወገኖቻችን እንኳን ለ1447ተኛው የኢደል-ዓድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!ኢድ ሙባረክ!!የምሁር አክሊል ወረዳ  የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት
27/05/2026

ለመላው ሙስሊም ወገኖቻችን እንኳን ለ1447ተኛው የኢደል-ዓድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!

ኢድ ሙባረክ!!

የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት

‎የሞህር አክሊል ወረዳ ቡር አናባሪ አበአጥ ብስራት ገብሩ የእስልምና እምነት ይተሄቴሙ አበሩስ የ1447ኛ የኢድ-አል አደሃ አረፋ ባል የማኛም አሠላንህሙ ለሁተት አብሙም። ‎‎ግልሞት 18/20...
26/05/2026

‎የሞህር አክሊል ወረዳ ቡር አናባሪ አበአጥ ብስራት ገብሩ የእስልምና እምነት ይተሄቴሙ አበሩስ የ1447ኛ የኢድ-አል አደሃ አረፋ ባል የማኛም አሠላንህሙ ለሁተት አብሙም።

‎ግልሞት 18/2018ዓ.ም

‎ያረፋ ባል ተሀይማኖታዊ ባልነትውታ በዘሌ በህዝብዌ መሀል ያበሳን ድማጀ ልቅኤ ቦህንውታ ተእስልምና እምነት ተኸታይዌ ባለፈ ይሺምዌ እምነት ተኸታይ አበሩስ ልቅኤ ይእሮይ ባል የኸነኸማ አበአጥ ብስራት ዝነጊሙም።

‎የኢድ-አል አደሃ አረፋ ባትነት ያከቡሪ ባል ቲኸን የንብረት አእም ያንሰሙ የእምነትዌ ተኸታይ አበሩስ ማድ ይሸሸጅቧ፣ ይለብሺኤም እሺምዌ የባልዌ ይሾየሙ ንብረት ይሸሸጅቧ፣ እርስ በርስ ይትርጃጀቦ ባህልና በተግባር ያተዥቧ ሀይማኖታዊ ባል የኸነኸማ ኦድሙምታነ ዚህ ይመሲ ይሺ ማሟዘንጋ ቲደቢ ይበሳኸማም ተሴሙም።

‎አበአጥ ብስራት ዠበርሙምታ ተዚ ይፍተት ያርወሺኸማ እርስ በርስ ይደመጅቧ ዮተገገዝ ባህልና ቢያተባን አግባብ የመና ቅድመ ዝግጅት ተአያና ፅዳት፣ ያርጅየሙ ዋጋ ቷሰረ ቀረሽም ዮርድ ዋትስናዳ፣ በባል ወእትም እርስ በርስ ቦትሰሴ፣ ባዘና ዮትቀቤ ልማድና ትሺጊዌ በነን ቦትለእ ማህበራዊ መስተጋብርና ከፍ ዋቢ ያነብነኸማ አትምላከትሙም።

‎ቦረዳና በእስልምናው እምነት ተኸታይ አበሩስ ያረፋ ባል ወርያ በኸነ ዘባ ያከቡሪ ባል ቲኸን በሜራ ምክንያት ተቤተሰብኽነሙ ራዕሙም የነበርሙ በትልያየ ከተማም ቦጤ ገኝ ይነብርሙ የምነትዌ ተኸታይ አበሩስ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በዓል ለማክበር ብቻም ሳይሆን ያበሩስኽነሙ የልቅህነሙ ምርአት ዮትቀቤ፣ ደቦህነሙም ኸነ ቦክስ ምክንያት የናፈኧነሙ የኣያህነሙ ሰብ ዮትሴ ያበአነሙ ባል ወኸንውታም ዝነጊሙም።

‎ልዕየዌ የኢድ አል–አድሃ አረፋ ባል የመስዋዕትነት ባል ቦህንውታ ህዝበ ሙስሊምዌ ቴሰስት የደቦ ይሰለቧ ወተገገዝ በተግባር ቲያተዥወ ዘባ ወስጥ ይጠእሺኤን ቤሙምታ ማሟነት ከፍ አበኝም ያተዥቦም ዚህ ይመሲሙ ዓይነትማሟ ዘንጋ በባልዌ ይትኽናወንሙኸማ ጠቀስሙምታ ድጋፍ ያሸነሙ ደቦ ዮደግፍ ሀይማኖታዊም የማመረሰብዌ ዕሴት የኸነዌ ማሟነት ተጨና ቲደቢ ይፈካኸማ እንም በቀያ ቃያውታ ዓረዓያነት ያነን ሜራ ይቾቺኸማ ቡር አናባሪዌ ተሴሙምታ ይንም እስልምና እምነት ይትሄቴሙ አበሩስ የኢድ-አል-አድሃ ያረፋ ባልዌ የሠላም፣የበረከት ይትዋጀጅቦ ባል ይኸነህማ የማሟ ዘንጋ ለሁተትኽነሙ አሠለሙም ቲቢ የጣፈን የሞህር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጥፈት ቤትን።

ሀገራችን ኢትዮጵያን ከድህነት ለማውጣት መንግስት ዘርፈ ብዙ ጥረቶች እያደረገ ይገኛል፦ አቶ ብስራት ገብሩግንቦት 18/2018ዓ.ም (ምሁር አክሊል ሐዋርያት) በክልሉ ግብርና ቢሮ አማካኝነት የ...
26/05/2026

ሀገራችን ኢትዮጵያን ከድህነት ለማውጣት መንግስት ዘርፈ ብዙ ጥረቶች እያደረገ ይገኛል፦ አቶ ብስራት ገብሩ

ግንቦት 18/2018ዓ.ም (ምሁር አክሊል ሐዋርያት)

በክልሉ ግብርና ቢሮ አማካኝነት የማምረት አቅም ባላቸውና በተመረጡ ወረዳዎች ተግባራዊ በሚደረገው የጃክ ፍሩት ልማት ኢንሼቲቭ፣ ወረዳው የጃክ ፍሩት ችግኝ 10ሺ ገደማ ችግኞች የተረከበውን የማዛመት ስራ ተጀመረ።

መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ከሚሰራባቸው ዘርፎች ድህነትን መቀነስ አንዱ ሲሆን ድህነትን ለማሸነፍ የተለያዩ ዘዴዎች ተጠቅሞ እየሰራ እንደሚገኝ በጃክ ፍሩት ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የምሁር አክሊል ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብስራት ገብሩ ተናግረዋል።

በወረዳችን በግብርናው ዘርፍ ከመንግሥት የሚወርዱ ኢኒሼቲቮች በየጊዜው ተቀብሎ ውጤታማ ለማድረግ ሰፊ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝና ማህበረሰቡም በየዘርፉ ተጠቃሚ ሆኖ ለገበያ አቅራቢያ እንዲሆን ሁሉን አቀፍ ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል።

መንግስት በተለያየ ጊዜ የሚያወርዳቸው ኢኒሼቲቮች የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሲሆን አሁን ላይ በተለያዩ ቦታ የተጀመረው የጃክ ፍሩት ተክል ውጤታማ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል።

የማህበረሰቡ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ በርካታ ተግባራቶች እየተከናወኑ እንደሚገኝ የምሁር አክሊል ወረዳ ግብርና ፅ/ት ቤት ኃላፊ አቶ መኑር ጀማል ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በተመረጡ ቀበሌዎች የጉድጓድ ዝግጅት እንዲሁም በመንግስት ችግኝ ጣቢያዎች ላይ የመደብ ዝግጅት ስራ በአግባቡ እየተከናወነ እንደሚገኝና ዛሬ ላይ በደንገዝ ቀበሌ በዋረ በተት ጀፎረ ላይ የተከላ ፕሮግራም እና ለማህበረሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ ተሰርቷል።

የጃክ ፍሩት ልማት በአግሮፎሬስትሪ ስርዓት ከቡና፣ ሙዝ እና አቮካዶ ጋር ተቀናጅቶ በመልማት የአፈር መሸርሸርን የመከላከል፣ የአፈር እርጥበትን የመጠበቅ፣ ካርቦን በመያዝ የአየር ንብረት ለውጥን የመቀነስና ጥላ በመስጠት የአካባቢ ሙቀትን የመቆጣጠር ሰፊ የተፈጥሮ ጥበቃ ጠቀሜታ እንዳለው ተመላክቷል።

የወረዳው የግብርና ልማት ጽ/ቤት ባለሙያ የሆኑት አቶ አክሊሉ ፍቅሬ እንደገለጹት የጃክ ፍሩት ከተተከለ ከ3 እስከ 5 ዓመታት ውስጥ ምርት መስጠት የሚጀምር፣ ለረጅም ጊዜ የገቢ ምንጭ መሆን የሚችልና ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ነው።

ይህን ኢኒሼቲቭ በተገቢው ተረድቶ መስራት ከተቻለ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ፣ ለእናቶችና ህፃናት የተሻለ የተመጣጣኝ ምግብ አቅርቦትን ይሰጣል።

ዘሩን ተደራሽ ለማድረግ በችግኝ ጣቢያዎች፣ በአርሶ አደር ማሳ እንዲሁም በሌሎችም ቦታዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራ ጠቁመዋል።

በመጨረሻም አቶ አክሊለ እንዴት መተከል እንዳለበት በስፍራው ለተገኙ አጠር ያለ የተግባር ስልጠና አሳይተው በስፍራው ከተገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር የተከላ መረሀ ግብር የተካሄደ ሲሆን በማስጀመሪያ መረሀ ግብሩ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ አለምይርጋ ወ/ሥላሴ፣ እንዲሁም ሌሎችም የክልልና የዞን አመራሮች ተገኝተዋል።

ለብልፅግና ፓርቲ  የድጋፍ ሰልፍ በመስቀል አደባባይ እየተካሄደ ነው**********************ለብልፅግና ፓርቲ ድጋፋቸውን ለመግለፅ ከተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች የተውጣጡ የህብረተሰብ...
26/05/2026

ለብልፅግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ በመስቀል አደባባይ እየተካሄደ ነው
**********************
ለብልፅግና ፓርቲ ድጋፋቸውን ለመግለፅ ከተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች በመስቀል አደባባይ ተሰባስበዋል።

በአሁኑ ሰዓት እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ የድጋፍ ሰልፍ ላይ የከተማዋ ነዋሪዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው።

ነዋሪዎቹ ብልፅግና ፓርቲ የገባውን ቃል ወደ ተግባር በመቀየር ላስመዘገባቸው ስኬቶች ያላቸውን አጋርነት እና ድጋፍ በተለያዩ መልዕክቶችና መፈክሮች እያንጸባረቁ ይገኛሉ።

በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ሂደት አስተዋፅኦ ለሚያደርጉ የፀጥታ አካላት የስልጠና መድረክ ተካሄደ፡፡ ግንቦት 17/2018 ዓ.ም (ምሁር አክሊል) 7ኛውን ዙ...
25/05/2026

በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ሂደት አስተዋፅኦ ለሚያደርጉ የፀጥታ አካላት የስልጠና መድረክ ተካሄደ፡፡

ግንቦት 17/2018 ዓ.ም (ምሁር አክሊል)

7ኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃ እና ተዓማኒ በሆነ መልኩ ለማካሄድ በወረዳ ደረጃ ለፀጥታ አካላት የተዘጋጀ የስልጠና መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የምሁር አክሊል ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አበራ ክፍሌ በስልጠና መድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሠላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ በመቀናጀት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

ስልጠናው በምርጫ ወቅት ሊያጋጥሙ የሚችሉ የፀጥታ ስጋቶችን ቀድሞ ለመከላከል ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልፀው ምርጫው ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፀጥታ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

ሁሉም የወረዳው የፀጥታ አባል በህግና በስነ-ምግባር ታንጾ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንዳለበትም አሳስበዋል።

የምሁር አክሊል ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ታመነ ፍቅሬ የተሰጠንን ሚና ለይተን በመረዳት ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ደህንነቱ የተጠበቀ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ መስራት ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል።

በቅድመ ምርጫ፣ ምርጫና ድህረ ምርጫ ወቅት የሚኖሩ ስጋቶችን በመለየትና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመናበብ ኃላፊነትን መወጣት ይገባል ያሉት ኃላፊው የምርጫውን ሂደት ተአማኒነት ለማረጋገጥ የህዝብ ተሳትፎና የፀጥታው መዋቅር ቅንጅት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።

ስልጠናው ተገቢውን ዝግጅት ለማድረግና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለውን ጠቀሜታ በመረዳት የፀጥታ አካላት ከማንኛውም ወገንተኝነት ነፃ ሆነው ህዝባዊ አደራቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የምሁር አክሊል ወረዳ የፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኢንስፔክተር ተከስተ ትግስቱ በበኩላቸው የወረዳው የፀጥታ ኃይል የምርጫ ሂደቱን ህጎችና ደንቦች በመረዳት፣ እንዲሁም ሊያጋጥሙ የሚችሉ የፀጥታ ስጋቶችን አስቀድሞ ለመከላከል በትኩረት መስራት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

ለሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ተገቢውን የፀጥታ ዕቅድ በማዘጋጀት ለስኬቱ ሁሉም የፀጥታ አካል የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆንና ምርጫው ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

በመድረኩ ያገኙት ግንዛቤ በምርጫ ወቅት ስራቸውን በብቃት ለመወጣት እንደሚያግዛቸው የገለፁት የስልጠናው መድረክ ተሳታፊዎች ሰላምን ለማስከበርና ማህበረሰቡ የመምረጥ መብቱን ያለምንም ስጋት እንዲጠቀም ለማስቻል በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

በመጨረሻም የተካሄደው የፀጥታ አካላት ስልጠና ለ7ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊነት ጠንካራ መሰረት የጣለ መሆኑ ተመላክቷል።

በመድረኩም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ም/ኃላፊ አቶ አሰፋ አካሉ፣ የማኔጅመንት አባላት እንዲሁም የፀጥታ አካላት ተገኝተዋል።

መረጃው የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው።

በምሁር አክሊል እና በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የእግር ኳስ ቡድኖች መካከል ሲደረግ የቆየው የእግር-ኳስ ውድድር በዛሬው ዕለት ፍፃሜውን አገኘ።ግንቦት 16/2018 ዓ.ም (ምሁር አክሊል)በ...
24/05/2026

በምሁር አክሊል እና በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የእግር ኳስ ቡድኖች መካከል ሲደረግ የቆየው የእግር-ኳስ ውድድር በዛሬው ዕለት ፍፃሜውን አገኘ።

ግንቦት 16/2018 ዓ.ም (ምሁር አክሊል)

በ10 ቡድኖች መካከል በምሁር አክሊል ወረዳ መዝወር ሲካሄድ የቆየው ውድድሩ በምሁር አክሊል ወረዳው "ዊነርና" በገደባኖ ጉታዘር ወለኔው "ለቻቻልነ" የእግር ኳስ ቡድኖች መካከል በተደረገ የዋንጫ ጨዋታ በ"ለቻቻልነ" የ2ለ1 አሸናፊነት ፍፃሜውን አግኝቷል።

በፍፃሜው መርሀ-ግብር የተገኙት የምሁር አክሊል ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብስራት ገብሩ ስፖርታዊ ውድድሩ የርስ በርስ ትስስርን ለማጠናከር ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ገልፀው በቀጣይም መሰል ውድድሮች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

አቶ ብስራት አክለውም ስፖርታዊ ውድድሮች ወጣቶች ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውንና ትኩረታቸውን በበጎ ተግባር ላይ እንዲያውሉ በማድረግ ጤናን ከመጠበቅና ከሱሶች ከመታደግ ረገድ ጠቀሜታቸው የላቀ መሆኑን ገልፀዋል።

ውድድሩ ህብረተሰብን በማገናኘት፣ ወጣቶችን በማብቃት ረገድ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልፀው ተሰጥኦዎች የሚወጡበት ዕድል የሚፈጠረው ከመሰል ውድድሮች በመሆኑ፣ ወጣቶች ብቃታቸውን በማሻሻል ወደ ከፍተኛ እግር ኳስ ደረጃ የሚሸጋገሩበት መሰላል መሆን እንደሚችልም አመላክተዋል።

የምሁር አክሊል ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ት ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ኤብዶ በበኩላቸው በሁለቱ ወረዳዎች መካከል የተደረገው ይህ ውድድር በሁለቱ ጎረቤት ህዝቦች መካከል ያለውን መቀራረብ፣ መከባበር እና የወንድማማችነት ስሜት ይበልጥ ያጠናከረ መሆኑን ተናግረዋል።

ኃላፊው አክለውም ወጣቶች አዘውትረው ልምምድና ውድድር ሲያደርጉ የአካልና የአእምሮ ጤንነታቸው የተጠበቀ እንደሚሆንና ይህም ከሱስና ከተለያዩ አልባሌ ድርጊቶች ርቀው ስነ-ምግባር ያላቸው ስኬታማ ዜጎች እንዲሆኑ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግም አስገንዝበዋል።

በርካታ ቁጥር ያላቸው የስፖርት አፍቃሪያን፣ የሁለቱም ቡድን ደጋፊዎች በተገኙበት የተካሄደው ውድድሩ፣ ለአሸናፊ፣ 2ኛ እንዲሁም 3ኛ ላጠናቀቁ ቡድኖች፣ ለኮከብ ግብ አስቆጣሪና ግብ ጠባቂ በተደረገ የዋንጫና የገንዘብ ሽልማት ስነ-ስርዓት ተጠናቋል።

በፍፃሜው መርሃ-ግብርም የምሁር አክሊል ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሰይፈ ይልማ፣ የምሁር አክሊል ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አበራ ክፍሌ፣ የምሁር አክሊል ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ምትኩ ገብሬ፣ እንዲሁም ሌሎች የወረዳው አመራሮች ተገኝተዋል።

መረጃው የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው።

የሙስሊሞች ሁሉ የልብ ትርታ፤ ወደ ቅዱሱ ስፍራ ካዕባ የሚደረግ የሕይወት ዘመን ታላቅ ጉዞ*******************በዓለም ዙሪያ ለሚኖሩ ሙስሊሞች ሁሉ ይህ ስፍራ የቅዱስ ሕልማቸው ማዕከል...
24/05/2026

የሙስሊሞች ሁሉ የልብ ትርታ፤ ወደ ቅዱሱ ስፍራ ካዕባ የሚደረግ የሕይወት ዘመን ታላቅ ጉዞ
*******************

በዓለም ዙሪያ ለሚኖሩ ሙስሊሞች ሁሉ ይህ ስፍራ የቅዱስ ሕልማቸው ማዕከል፣ የናፍቆታቸው ጥግ ነው። ካዕባ... የአላህ ቤት።

በየዓመቱ በርካታ ሙዕሚኖች፣ ከሁሉም የዓለም ማዕዘናት ሀገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ፣ ምድራዊ ልዩነቶችን ሁሉ ወደ ጎን ትተው ወደዚህ የተቀደሰ ስፍራ ይተማሉ። ይህ ለሰጋጅ ሁሉ የሕይወት ዘመን ታላቅ እና ተናፋቂ ጉዞ ነው።

ይህ ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ የሚጀምረው ፍጹም በሆነ እኩልነት ነው። ንጉሥም ይሁን ምስኪን፣ ባለሀብትም ይሁን ድሃ... ሁሉም ምድራዊ ጌጣጌጦችን አውልቀው ነጭ ኢሕራም በመልበስ በአላህ ፊት አንድ ይሆናሉ።

በአረፋት ቀን፣ የአላህ ምሕረትና እዝነት እንደ በረከት ዝናብ በሚዘንብበት በዚያ ታላቅ ዕለት፣ ሙዕሚኖች በፍጹም ተስፋና በዕንባ ፈሳሽ ፈጣሪያቸውን ይማጸናሉ።

ፀሐይ ስትጠልቅ ደግሞ ወደ ሙዝደሊፋ ያመራሉ፤ በባዶ መሬት ላይ፣ ከከዋክብት ስር አብረው በማደር ፍጹም ትሕትናንና አምላካዊ ፍቅርን በተግባር ያሳያሉ።

በሦስተኛው ቀን 'ጃማራት' በተባለው ስፍራ ላይ ጠጠር በመወርወር፣ በውስጣቸው ያለውን ክፉ ምኞትና የሰይጣንን ተንኮል በጽናት ይዋጋሉ።

በመቀጠል ወንዶች ጸጉራቸውን ይላጫሉ፤ ይህም ከአሮጌውና ከኃጢአት ሕይወት ወጥቶ ወደ አዲስ፣ ንጹሕና ብሩህ መንፈሳዊ ሕይወት የመሸጋገር ትልቅ ማብሰሪያ ነው።

በመጨረሻም 'ጠዋፍ አል-ዊዳዕ' ወይም የስንብት ጠዋፍ በማድረግ ከአላህ ጋር አዲስ የእምነት ቃል ኪዳን ያስራሉ።

ወደየሀገራቸውና ወደ ውድ ቤተሰቦቻቸው የሚመለሱት ወንጀላቸው የተማረላቸው፣ ልባቸው በብርሃን የሞላ እና አዲስ መንፈስ የለበሱ ሐጂዎች ናቸው።

የአረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ ተጓዦች በትራንስፖርት እጦት ላላስፈላጊ ወጪ እንዳይዳረጉ መንግስት አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጉን ተገለፀ።ግንቦት 15/2018(ወልቂጤ) የጉራጌ ዞን ትራንስፖ...
23/05/2026

የአረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ ተጓዦች በትራንስፖርት እጦት ላላስፈላጊ ወጪ እንዳይዳረጉ መንግስት አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጉን ተገለፀ።

ግንቦት 15/2018(ወልቂጤ) የጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ እና የወልቂጤ ከተማ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽህፈት ቤት ከፖሊስ መዋቅሮች የማኔጅመንት አባላት ጋር የአረፋ በዓል በማስመልከት በመንገድ ደህነትና በትራፊክ ቁጥጥር ላይ ያተኮረ ውይይት አካሄዱ።

የጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ የህያ ሱልጣን እንደተናገሩት የአረፋ በዓልን ለማክበር ወደ ጉራጌ ዞን ለሚመጡ እንግዶች ምንም ዓይነት የትራንስፖርት ችግር እንዳይገጥማቸው መንግስት የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎችን ማመቻቸቱን ገልፀዋል።

ተሽከካሪዎቹ በሶስት መነሻ ጣቢያዎች ወደ 21 መዳረሻዎች/መስመሮች ያሏቸው ሲሆን ከታሪፉ 50 በመቶ ጭማሪ መደረጉን ገልፀዋል።

ከ21መዳረሻዎች ያልተካተቱ የጠጠር መንገዶች የውስጥ ምደባ በማድረግ ለመሸፈን ዝግጅት እየተደረገ በመሆኑ ተጓዦች የተሽከርካሪ ችግር እንደማይገጥማቸው እና ይልቁንም ተረጋግተው በተዘጋጁ ተሽከርካሪዎች ብቻ እንዲሳፈሩ አሳስቧል።

በአ/አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ደላሎች ኮንተራት እናደርሳለን በሚል ብር 5000 እና ከዚያ በላይ እየመዘገቡ ለመዝረፍ እየሞከሩ መሆኑን ደርሰንበታል ያሉት ኃላፊው እንዲህ አይነቱ ዘረፋ መንግስት በቸልታ የሚያልፈው እንዳልሆነ እና ዘራፊዎች ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን በህግ የምንጠይቅ መሆኑን ተረድተው ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ከወዲሁ እናሳስባለን ብሏል ።

ተሳፋሪዎች ከተጠቀሱ ሶስቱ መነሻ ጣበያዎች ባሻገር ወደ አንድ መዳረሻ ቁጥራቸው ከ60 በላይ እና ከዚያም በላይ ቢሆን ወደ ሚቀርባቸው አካባቢ ተሽከርካሪ መመደብ የሚቻል መሆኑን በዚሁ አጋጣሚ በመግለጽ የበዓሉ ታዳሚዎች ከዘራፊዎች እራሳቸውን እንዲጠብቁ በጥብቅ አሳስቧል።

ከመናሀሪያ ውጭ የሚሰጡ የትራንስፖርት አገልግሎቶች በጥንቃቄ መመራት እንዳለባቸው የገለፁት ኃላፊው፤ የቁጥጥር ስራው ማስተናበርን ትኩረት ያደረገ ይሆናል ብሏል።

ከዚህ በተጨማሪም ፍትሃዊና ወቅቱን ያገናዘበ የነዳጅ አጠቃቀም ሊኖር እንደሚገባ አቶ የህያ አሳስበዋል።

በሌላ በኩል፣ የበዓሉ ታዳሚዎች በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የተመዘገቡ ተጓዦች ከግንቦት 24 /2018 ከምርጫው ቀን አስቀድመው ወደ ተመዘገቡበት አካባቢ መመለስ እንዳለባቸው ያሳሰቡ ሲሆን ፤ ግንቦት 23/2018 የምርጫ ካርድ ለያዙ ተመላሾች ልዩ የባስ አገልግሎት የተዘጋጀ መሆኑን በመግለጽ መራጮች በተጠቀሰው ቀን ከንጋቱ 12:00 ጀምሮ በቀጣይ በሚገለጹ መነሻ ጣበያዎች ካርዳቸውን ይዘው ዝግጁ ሆነው እንዲጠብቁ አቶ የህያ ጥሪያቸውን አስተላልፏል።

የጉራጌ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ገና ደገሙ በበኩላቸው፣ ተጓዦች ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም መጓዝ እንዲችሉ የመንገድ ደህንነት ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል።

ከአዲስ አበባ ወደ ዞኑ የሚገቡ የህዝብ ማመላለሻዎች አላስፈላጊ ቁጥጥር እንዳይደረግ ከቀቤና ልዩ ወረዳ የፖሊስ መዋቅር ጋር በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።

የትራንስፖርት አገልግሎቱ ለማፋጠን የአካባቢ ተሽከርካሪዎች ጭምር የሚሰማሩ በመሆኑ አሽከርካሪዎች ነዳጅን ኃላፊነት በተሞላበት አኳኋን መጠቀም ይኖርባቸዋል ሲሉ ገልፀዋል።

አያይዘውም ኮማንደር ገና የመንገድ ደህንነትን ለማስጠበቅ ከሚንቀሳቀሱ የመንገድ ደህንነትና የትራፊክ ፖሊስ ውጭ አንፀባራቂ ልብስ መልበስ በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ የኮተ ቀበሌ የብልፅግና ፓርቲ አባላት የምርጫ ቅስቀሳና የቡና ጠጡ ፕሮግራም ተካሄደ።ግንቦት 15/2018 ዓ.ም  ምሁር አክሊልበምሁር አክሊል ወረዳ ብልጽግና ...
23/05/2026

በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ የኮተ ቀበሌ የብልፅግና ፓርቲ አባላት የምርጫ ቅስቀሳና የቡና ጠጡ ፕሮግራም ተካሄደ።

ግንቦት 15/2018 ዓ.ም ምሁር አክሊል

በምሁር አክሊል ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ቅስቀሳ አካል የሆነዉ የ"ቡና ጠጡ" መርሃ ግብር በወረዳው የኮተ ቀበሌ በድምቀት ተካሂዷል።

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የምሁር አክሊል ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብስራት ገብሩ ብልፅግና ፓርቲ በርካታ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ በሀገሪቱ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን ገልፀዋል።

ዘላቂ ልማትና ሰላምን ለማስቀጠል ሕዝቡ ለፓርቲው ድምፁን እንዲሰጥ እና ብልጽግና ፓርቲ ኢትዮጵያን ተምሳሌት ለማድረግና ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት እየተጋ ያለ ፓርቲ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ህብረተሰቡ የመቻቻል፣የአንድነት ፣የአብሮነትና የሉዓላዊነታችን ማረጋገጫ የሆነው እና የመወዳደሪያ ምልክቱ የስንዴ ነዶ ብልፅግና ፓርቲ እንዲመርጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በምሁር አክሊል ወረዳ እዣ-2 ምርጫ ጣቢያ ብልፅግናን የወከሉ እጩ ተወዳዳሪዎች በበኩላቸዉ ብልፅግና ፓርቲ ግልፅ ፖሊሲ እና ስትራቴጂ በመንደፍ የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ እየሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ማምጣታቸውን የገለፁት እጩዎቹ እነዚህ ተግባራት ቀጣይነት እንዲኖራቸው ብልጽግናን መምረጥ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑንም ተናግረዋል።

የምርጫ ቀን ግንቦት 24/2018ዓ/ም መሆኑን አመላክተው በእጃቸው የያዙትን ካርድ ለብልፅግና ፓርቲ በመስጠት ጠንካራ ሀገር እንዲመሰርቱ ጥሪ አቅርበዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች የተጀመረውን ሀገራዊ ልማት እና ሠላም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል ሲል የዘገበው የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

Address

Hawariyat
Wolkite

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በጉራጌ ዞን የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to በጉራጌ ዞን የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት:

Share

Category