27/05/2026
1447ኛው የኢድ አል አደሃ አረፋ በዓል በምሁር አክሊል ወረዳ ሐዋርያት ከተማ በተለያዩ ሀይማኖታዊ ክንዋኔዎች በድምቀት ተከበረ።
ግንቦት19/2018 ዓ.ም
1ሺህ 447ኛው አመተ ሂጅራ የኢድ-አል አድሃ(አረፋ በዓል በምሁር አክሊል ወረዳ ሐዋርያት ከተማ በጀማኣ የኢድ ሶላት በድምቀት ተከብሮ አልፏል።
ህዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር የተቸገሩትን በመርዳት በመጠያየቅና በመተጋገዝ ሊሆን እንደሚገባ የሐዋርያት ከተማ ዲያኡልሀቅ መስጂድ ኢማም እና የወረዳው እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ሰብሳቢ ኡስታዝ ሙህዲን አህመዲን በሐይማኖታዊ ስርዓቱ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ገልፀዋል።
የአረፋ በዓል ሲከበር በእስልምና እምነት አስተምሮቱ መሰረት ከሚታረደው እርድም ማዕድ በማጋራትና በጋራ የሚከበር መሆኑን ገልፀው ህዝበ ሙስሊሙ በዓሉ በሚያከብርበት ወቅት ምስኪኖችና የተቸገሩ ወገኖች በመርዳት ሊሆን እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።
በመሆኑም ህዝበ ሙስሊሙ ከአላህ የታዘዘውን ተግባር በመፈጸም የተቸገሩ ወገኖችን ከማሰብ ባለፈ በማካፈል ሊሆን ይገባልም ብለዋል።
የበዓሉ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የኢድአል አደሃ (አረፋ) የኢድ ሶላት በሰላም በድምቀት መከበሩ ተናግረዋል።
ህዝበ ሙስሊሙ በበዓሉ ወቅት የመረዳዳት የመተሳሰብ እሴቶችን በማጠናከር ምስኪኖችን በማሰብና በማካፈል መከበር እንዳለበትም ገልፀዋል ሲል የዘገበው የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።