12/05/2026
በወላይታ ሶዶ ከተማ ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲን የይምረጡ ቅስቀሳ በአራዳ ክፍለ ከተማ፥ጉሩሞ ላዲሳ ቀበሌ ተካሂዷል
ወላይታ ሶዶ፦ ግንቦት 4/2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ ለሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲን የይምረጡ ቅስቀሳ በአራዳ ክፍለ ከተማ፥ጉሩሞ ላዲሳ ቀበሌ ተካሂዷል ።
በመርሃግብር ላይ የተገኙት ዶክተር ፍሬዉ ሞገስ የሶዶ ዙሪያ 1 ምርጫ ክልል ዕጩ ተወዳዳሪ እንደተናገሩት ብልጽግና ፓርቲ ትላንትናንና ዛሬን ያስተሳሰረ ፣ የኢትዮጵያ ተስፋን በማይናወጥ ጽኑ መሠረት የጣለ ፣የሴት እህቶቻችን የዉሳኔ ሰጭነት አድማስን ያሰፋ፣ለወጣቱ ትዉልድ ብሩህና በሁሉም ዘርፍ የበለፀገች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ቀን ከሌት አየሰራ የሚገኝ ፓርቲ ነዉ ብለዋል።
በሃሳብ ልዩነት ሀገርን ማፍረስ አይቻልም ያሉት ኃላፊ ችግሮችን በውይይትና በመግባባት በመፍታት በፓርቲው መሪነትና በህዝቡ የነቃ ተሳትፎ የብልጽግና ጉዞአችንን አዉን እናደርጋለን ስሉ ተናግረዋል።
ብልጽግና ፓርቲ የህዝብን ችግር በቅርበት እየፈታ ያለና የተጠየቁትንም ሆነ ያልተጠየቁትን ምላሽ የሚሰጥ ፓርቲ መሆኑ በመድረኩ ገልጸዉ በቅስቀሳ ፕሮግራሙ ላይ በነቅስ የተሳተፉ አባላትንም ሆነ ደጋፊዎችን አመስግነዋል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ እና የሶዶ ዙሪያ 1 ምርጫ ክልል ዕጩ ተወዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ዘገየ ጳዉሎስ በበኩላቸው እንደተናገሩት ብልጽግና መንግስታችን በአለም አቀፍ ደረጃ የታወቀ፣በአፍሪካ ግዙፍ የሆነና በኢትዮጵያ እንደ ሀገር የተመሰከረለት በአጭር ግዜ ዉስጥ አለምን እያስደመመ የሚገኝ ተጨባጭ ለዉጦችን እያስመዘገበ ያለ ፓርቲ ነዉ ብለዋል
“እንደ አከባቢያችን የተለያዩ የዘመናት የህዝባችን ጥያቀዎች ምላሽ እያገኙ ያሉት በብልጽግና ፓርቲ ነዉ ያሉት ረዳት ፕሮፌሰር ቀሪዎቹ የመልማት ጥያቄዎቻችን ምላሽ የሚያገኙትም በዚሁ በብልጽግና ፓርቲ ነዉ እኛ ለፓርቲያችን ታማኝ እንሁን ስሉ አሳስበዋል።
ብልጽግና ፓርቲ በተግባር የተፈተሸና ውጤታማ ፖሊሲ ያለው ፓርቲ ነዉ ካሉ በኋላ ፓርቲያችን ከየትኛውም ጊዜ በላይ ለሴቶችና ለወጣት ትኩረት የሰጠ፣ የኢትዮጵያን ታርክ እየቀየረ ያለ፣በአጭር ግዜ ዉስጥ የኢትዮጵያን ከፊታ ለማረጋገጥ እየተጋ ያለ ፓርቲ ግንቦት 24 እንዲመርጡ ጥሪውን አስተላልፏል ።
የአራዳ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዝናቡ ተክሌ በበኩላቸው ፓርቲያችን ብልጽግና ጠይቀን የሚመልስ፣ በክፉም በደጉም ከጎናችን ያልተለየ አለኝታነቱን እያሳየና ዘርፈብዙ የሆኑ ልማቶችን በአካባቢያችን እየሰራ ያለ ፓርቲ ነዉ ካሉ በኋላ የተጀመሩ የልማት ስራዎች እንድጠናቀቁ፣የተሻሉ መሰረተ ልማቶች እንድስፋፉና በሁሉም መስክ የበለጸገች ኢትዮጵያን እዉን ለማድረግ ምርጫችን ብልጽግና ይሁን ብለዋል።