22/03/2023
የኩዌት የጨረቃ እይታ ኮሚቴ ዋና ሀላፊ ሙሀመድ ቢን ናጂህ ሐሙስ የረመዳን ጾም ወር እንደሚጀምር አስታወቁ።
በመሆኑም የ1444ኛው የሂጅሪያ (በእስልምና አቆጣጠር) የዘንድሮ የረመዳን ፆም ሀሙስ መጋቢት 23 ቀን እንደሚጀምር ጠቁመዋል።
በዚህ አጋጣሚ የፍትህ ሚንስትር ፣ የገንዘብ እና እስልምና ጉዳዮች ሚኒስትር አብዱላዚዝ መጅድ ለአሚር ሼክ ነዋፍ አህመድ ጃብር አል ሰባህ፣ የኩዌት የፖለቲካ አመራሮች፣ ዜጎች እና ነዋሪዎች እንዲሁም የአረብ እና የሙስሊም ሀገራት መልካም የረመዳን ወር እንዲሆን ተመኝተውላቸዋል ። .
የኩዌት ማዘጋጃ ቤት ዋና ዳይሬክተር አህመድ ማንፉሂ በረመዳን በቀን ውስጥ ምግብ ቤቶች እና ካፌዎች ዝግ ሆነው መቆየት እንዳለባቸው እና ለኢፍጣር ሁለት ሰአት ሲቀረው መክፈት እንደሚችሉ የኩዌት ማዘጋጃ ቤት ዋና ዳይሬክተር አህመድ ማንፉሂ ማክሰኞ አስታወቁ።
እንዲሁም የማዘጋጃ ቤቱ ተቆጣጣሪዎች ከረመዳን መጀመርያ ቀን ጀምሮ የሚፈጸሙ የህግ ጥሰቶችን እንዲከታተሉ መመሪያ የተሰጣቸው ሲሆን ማዘጋጃ ቤቱም ቁጥጥሩ እንደሚያጠናክር ዳይሬክተሩ አክለው ገልፀዋል ።
KUWAIT: Kuwait’s moonsighting committee announced that Thursday will be the start of the holy fasting month of Ramadan. Chairman of the moonsighting committee, Justice Mohammad bin Naji, made the announcement after the committee’s meeting on Tuesday evening. Consequently, Ramadan of the Hijri or...