29/08/2025
ሩበን አሞሪም ነገ በፕሪምዬር ሊጉ 3ኛ ሳምንት በሜዳችን በርንሌይን ከምንገጥምበት ጨዋታ በፊት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
አሞሪም ቦታቸውን ማስጠበቅ ስለሚፈልጉ ተጫዋቾች
" በዚህ ጊዜ እድል የማይሰጣቸው ተጫዋቾች እንደሚያዝኑ እረዳለሁ ነገር ግን ሁሉም ተጫዋች ለመጫወት አንድ አይነት እድል ነው ያለው ፣ ያንን ቦታ ለማግኘት በየሳምንቱ መፋለም አለባቸው።
አሞሪም ስለ ቡድኑ ሁኔታ :-
"አሁን ላይ በቡድኑ እጅጉን አዝኛለሁ ፣ ምክንያቱም የቅድመ ውድድር ዘመን ጨዋታዎች ላይ ጥሩ ቡድን ያለኝ መስሎኝ ነበር "
" ተለዋዋጭነት የሌለው እና ቀጣይነት ያለ ጨዋታ መጫወት አለብን እና የነገው ጨዋታ አዲስ ጨዋታ እንደመሆኑ መጠን ትኩረታችንን እዛው ላይ ነው"
አሞሪም በግሉ ስላለበት ሁኔታ :-
" አንዳንድ ጊዜ ቡድኑን ለቅቄ ለመውጣት አስባለው ፣ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ለ20 አመታት ብቆይ እላለሁ "
"አንዳንድ ጊዜ ከተጫዋቾቼ ጋር መሆን እፈልጋለሁ ፣ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ከእነሱ ጋር መሆን አልፈልግም"
" እንደዚህ አይነት ባህርይ ማስቀረት መቻል አለብኝ ።"
አሞሪም ስለ ኮቢ ማይኖ
"ኮቢ እዚህ በቡድኑ እንዲቆይ እፈልጋለሁ ፣ እሱ በቦታው መፋለም ይፈልጋል "
"ብዙ ልምድ ያላቸው ሰዎች የምሰጣቸው አስተያየቶች ወጥ እንዲሆኑ እና በጣም እርጋታ እንዲኖረኝ ይፈልጋሉ ፣ እኔ ግን እንደዛ አይደለሁም።"
አሞሪም ስላለፈው የፕሪምየር ሊግ ጨዋታ
" ለ30 ደቂቃዎች ያክል መጥፎ የሚባል ጨዋታ ተጫውተን መጥፎ አፈጻጸም ይዘን ወተናል "
"በእንደዚህ አይነት ጨዋታዎች እንደዚህ አይነት አቋም ማሳየት የሚያሳዝን ነው እና አሁን ሙሉ ትኩረታችንን ወደ ነገው ጨዋታ ለማዞር እንገደዳለን"
አሞሪም ከካራፓዎ ሽንፈት በኋላ ስለነበራቸው ሁኔታዎች
"በጊዜው በጣም ተናድጄ እና ተበሳጭቼ ነበር እና ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላወኩም ነበር "
"ብዙ ልምድ ያላቸው ሰዎች የምሰጣቸው አስተያየቶች ወጥ እንዲሆኑ እና በጣም እርጋታ እንዲኖረኝ ይፈልጋሉ፣ እኔ ግን እንደዛ አይደለሁም።"
አሞሪም ስለ አንዳንድ ሽንፈቶች
"አንዳንዴ ከሽንፈቱ የሚከብደው ነገር ውጤቱ አይደለም፣ ጨዋታውን የተሸነፍንበት ወይም አቻ የወጣንበት መንገድ ነው፣ ለኳስ መፋለም እና መሮጥ አለመቻሉ ነው።"
!
ሩበን አሞሪም ዛሬ ከሰአቱን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለ አንዳንድ ተጫዋቾች የጉዳት ሁኔታ አብራርተዋል።
ሩበን አሞሪም ባሳለፍነው ሳምንት ሞሮኳዊው ኢንተርናሽናል ኑሲየር ማዝራዊ በዚህ ሳምንት የመመለስ እድል እንዳለው የተናገሩ ቢሆንም
ተጫዋቹ ለነገው ጨዋታ ብቁ ነው ወይም አይደለም ለሚለው ጥያቄ መልስ አልሰጡም ፣ ይሁን እንጂ ማዝራዊ ጥሩ የሚባል ለውጥ እንዳሳየ እና ከጉዳቱ እያገገመ እንደሆነ አስታወቀዋል ።
በሌላ በኩል አሞሪም ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ ካጋጠመው የጉልበት ጉዳት ጥሩ በሚባል ደርጃ እያገገመ እንደሆነ እና ጥሩ ስሜት እየተሰማው እንዳለ አስታውቀዋል።
ባሳለፍነው የካራባዎ ዋንጫ ጨዋታ እረፍት ተሰቷቸው የነበረው ሉክ ሾው እና ሌኒ ዮሮ በነገው እለት ወደ ጨዋታ እንደሚመለሱ ይጠበቃል።