Afro Soccer Ethiopia / አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ

Afro Soccer Ethiopia / አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ የኢትዮጵያን ቀደምት ከዋክብት እያነገስን ፤ ታሪካቸውን ለመጪዎቹ እናሻግራለን ✅ ክብር ለቀደምት ተጫዋቾቻችንን
(1)

06/25/2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የምንጊዜም ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ማነው?

ይህ ተጫዋች ማነው? 👉ሲጫወት ያያችሁት ትውስታችሁን አካፍሉን(ለምስሉ ጥራት ይቅርታ 🙏)🎁ኮከቦቻችን በዘመናት እርዝማኔ ተሸፍነው እንዳይረሱ እናስታውሳቸው 🎁የኢትዮጵያን ቀደምት ከዋክብት እያነ...
06/24/2026

ይህ ተጫዋች ማነው?

👉ሲጫወት ያያችሁት ትውስታችሁን አካፍሉን

(ለምስሉ ጥራት ይቅርታ 🙏)

🎁ኮከቦቻችን በዘመናት እርዝማኔ ተሸፍነው እንዳይረሱ እናስታውሳቸው 🎁

የኢትዮጵያን ቀደምት ከዋክብት እያነገስን ታሪካቸውን ለመጪዎቹ እናሻግራለን ✅
🎁🎁🎁አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ🎁🎁🎁
🎁🎁🎁 የኢትዮጵያ ሌጀንዶች ቤት 🎁🎁🎁

ማንን ታታውሳላችሁ ?👉እነዚህ ተጫዋቾች እነማናቸው? ሲጫወቱ ያያችኋቸው ትውስታችሁን አካፍሉን (ለምስሉ ጥራት ይቅርታ 🙏)🎁ኮከቦቻችን በዘመናት እርዝማኔ ተሸፍነው እንዳይረሱ እናስታውሳቸው 🎁የ...
06/23/2026

ማንን ታታውሳላችሁ ?

👉እነዚህ ተጫዋቾች እነማናቸው? ሲጫወቱ ያያችኋቸው ትውስታችሁን አካፍሉን

(ለምስሉ ጥራት ይቅርታ 🙏)

🎁ኮከቦቻችን በዘመናት እርዝማኔ ተሸፍነው እንዳይረሱ እናስታውሳቸው 🎁

የኢትዮጵያን ቀደምት ከዋክብት እያነገስን ታሪካቸውን ለመጪዎቹ እናሻግራለን ✅
🎁🎁🎁አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ🎁🎁🎁
🎁🎁🎁 የኢትዮጵያ ሌጀንዶች ቤት 🎁🎁🎁

06/23/2026

ጎሏን ያስቆጠረው የቡናው ኮከብ ማነው?

#ኢትዮጵያ Ethiopian Football Federation አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና - አደገኞቹ

አብዱረዛቅ አብዲ ፡ ናይጄሪያ ✅ያልተዘመረለት ኮከብጅማ ከክቡር ይድነቃቸው ተሰማ ቀጥላ ለኢትዬጵያ እግርኳስ ያበረከተችልን ፈርጥ አብዱረዛቅን ነው ። አጋሮ ተወልዶ በሰባት አመቱ አዲስ አበባ ...
06/23/2026

አብዱረዛቅ አብዲ ፡ ናይጄሪያ

✅ያልተዘመረለት ኮከብ
ጅማ ከክቡር ይድነቃቸው ተሰማ ቀጥላ ለኢትዬጵያ እግርኳስ ያበረከተችልን ፈርጥ አብዱረዛቅን ነው ። አጋሮ ተወልዶ በሰባት አመቱ አዲስ አበባ የመጣው አብዲረዛቅ ኳስ መጫወት የጀመረው በሰፈር ውስጥ አስፓልት ላይ ነው ። ይህ የልጅነቱን ደስታ ለማጣጣም ያዘወተረው ተግባር የመንገደኛን ሁሉ ቀልብ ይሰብ ጀመር ። በአስደናቂ የኳስ ችሎታው ተስበው አብረውት ለመጫወት ከሩቅ ጭምር የሚመጡ እኩዮቹ ቁጥራቸው ተበራከተ ። እናም ከጠባቡ አስፓልት ይልቅ ሚካኤል ሜዳ ማዘውተሪያቸው ሆነ። አሁን ተመልካቹ በዛ ፤ አድናቂው ተበራከተ ። ምተሀተኛ እግሮቹ በሚያሳዩት ጥበብ ከተደመሙት መካከል እግርጥሎት ከስፍራው የተገኘ አንድ የቡና መልማይ ነበር ፤ ያየውን ማመን ያቃተው ይህ መልማይ በቀጣይ ቀን በጥዋት የብላቴናውን ቤት አጠያይቆ ሄዶ አንኳኳ.....በወቅቱ ቡና ቢ ተተኪ ተጫዋቾችን አወዳድሮ ለመውሰድ ከ300 በላይ ታዳጊዎችን መዝግቧል ። እናም ሌላ ተወዳዳሪ አይፈልግም። ሆኖም አብዲረዛቅ በድንገት ባየው መልማይ ከፍተኛ ጥረት ተመዘገበ። በውድድሩ ቀን ግን አንጋፋዎቹ አሰልጣኞች 10 ደቂቃ ብቻ አይተውት በ1ኛነት መረጡት ።ብላቴናው የቡና ንብረት ሆነ።

✅ ቡና B

ክለቡ ከነበረበት ክፍተት አንፃር ሳይሆን ታዳጊው አብዱረዛቅ ካለው እጅግ አስገራሚ ብቃት አንፃር ከB ወደ A ለማደግ 6 ወር ብቻ ነው የፈጀበት ። ይህ ፈጣን እድገቱ ያለውን የእግርኳስ ክህሎት ከፍታ ያሳየ ነበር ።

✅ቡና A
አብዲረዛቅ ዋናውን ቡድን ለመዋሀድም ጊዜ አልፈጀም ፤ በተለይ የመኝታ ክፍል የተጋራቸው የወቅቱ ኮከቦች መንግስቱ ቦጋለ እና ፀጋዬ ፈንታሁን በሚሰጡት ምክር እና ማበረታቻ ሞራሉን እና በራስ መተማመኑን ገንብቶ በሜዳ ላይ ሙሉ ብቃቱን ማሳየት ጀመረ ፤ በየጨዋታው ድንቅ ክህሎቱን በማሳየት በቡናዎች ልብ ውስጥ ተንሰራፋ .....
✅ስኬቶቹ
👉ከቡና ጋር 2 ዋንጫ አንስቷል፡
ይድነቃቸው ዋንጫ እና የጥሎ ማለፍ ዋንጫ
✅ጎሎቹ
👉አማካዩ አብዲረዛቅ ከተመልካች ልብ የማይጠፉ ጎሎችን አስቆጥሯል ።
⚽በአሸናፊዎች አሸናፊ ጨዋታ ኤርትራ ጫማ ላይ ያስቆጠራት
⚽መድን ላይ ከአብዲ ሰኢድ ጋር በደብል ፓስ አልፎ ያስቆጠራትን ጨምሮ ሁለት ጎሎች
⚽በጊዮርጊስ ላይ ከጥላ ፎቅ አካባቢ ከረዥም ርቀት የሞከራት እና የጎል አግዳሚ የመለሰበት
⚽ፍፁም ቅጣት ምቶቹ....መቸም ከማይረሳ ጥም ቆራጭ ብቃቱ መሀል ተጠቃሹ ነው
✅የቡድን አጋሮቹ
👉አብዱረዛቅ አብሯቸው ከተጫወታቸው ቀደምት ሌጀንዶች ተርታ ሙሉጌታ ወልደየስ ፤ ሚሊዮን በጋሻው ፤ ጥላሁን መንገሻ ፤ ካሳዬ አራጌ ፤አብዲ ሰኢድ ተጠቃሽ ናቸው ።
✅ሌሎች ክለቦች
👉አብዱረዛቅ ከቡና በተጨማሪ ለባንክ እና ለአየር መንገድ ተጫውቷል
✅ ብሔራዊ ቡድን ግልጋሎት
👉ይህ የዛን ዘመን ፈርጥ በሚያሳዝን ሁኔታ ብሔራዊ ቡድኑን አላገለገለም ፤ ምክንያቱም ባባቱ የማሊ ዜግነት ስላለው እና ፓስፖርቱም በማሊ ስለሆነ
✅ኳስ ለምን ቶሎ አቆመ?
👉በጨዋታ በደረሰበት ጉዳት ሁለት ጊዜ ቀዶ ጥገና ያደረገው አብዲረዛቅ በዶክተሮች ለበርካታ ጊዜ እንዳይጫወት ቢነገረውም የኳስ ፍቅር አላስችል ብሎት ብዙ አመታት ተጫውቷል ። በስተመጨረሻም በዚሁ ጉዳት ምክንያት ከነ ሙሉ ብቃቱ ጫማ ሰቀለ ።
✅ጫማ ከሰቀለ በኋላ
አብዲረዛቅ ጫማ ከሰቀለ በኋላ ኑሮውን ለንደን አድርጓል ።ወደፊትም በአሰልጣኝነት ለመምጣት አስፈላጊ ኮርሶችን በመውሰድ ላይ ነው ።
✅ስለ ኢትዮጵያ እግር ኳስ እድገት የሰጠው አስተያየት ፡ " እግርኳሳችን እንዲያድግ በተለይ ታዳጊዎች ላይ መስራት ያስፈልጋል ፤ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችም ሊበዙ ይገባል "
❓ይህ ሌጀንድ ሲጫወት ያያችሁት ትውስታችሁን አጋሩን

🎁ኮከቦቻችን በዘመናት እርዝማኔ ተሸፍነው እንዳይረሱ እናስታውሳቸው 🎁

የኢትዮጵያን ቀደምት ከዋክብት እያነገስን አዲሶቹን እያሳደግን ታሪካቸውን ለመጪዎቹ እናሻግራለን ✅
🎁🎁🎁አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ🎁🎁🎁
🎁🎁🎁 የኢትዮጵያ ሌጀንዶች ቤት 🎁🎁🎁

Subscribe to get exclusive benefits:
https://www.facebook.com/100064088501389/subscribenow

Address

Alexandria, VA

Telephone

+251704149670

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Afro Soccer Ethiopia / አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Afro Soccer Ethiopia / አፍሮ ሶከር ኢትዮጵያ:

Share

Category